Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የአገር መከላከያ ምግበና ግብረአበሮቹ የሚመሩት “ዘመቻ አንድነት” በኪሳራ መጠናቀቁን አስታወቀ
News

የአገር መከላከያ ምግበና ግብረአበሮቹ የሚመሩት “ዘመቻ አንድነት” በኪሳራ መጠናቀቁን አስታወቀ

Ethioreview newsEthioreview news—March 21, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

“በደቡብ ጎንደር፣ በምዕራብ ጎንደር፣ በሰሜን ጎጃም፣ በምስራቅ ጎጃም፣ በምዕራብ ጎጃም እንዲሁም በሰሜን ወሎ የምግበ ሀይለ ተላላኪ ፅንፈኞች በለኮሱት እሳት ተለብልበዋል” ሲል የአገር መከላከያ ሰራዊት አስታወቀ።

በቀድሞ በብርጋዲየር ጄኔራል፣ የአሁኑ የትግራይ ታጣቂዎች መሪ ምግበ ሀይለና ግብረ አበሮቹ አደራጅነትና አይዞህ ባይነት “ዘመቻ አንድነት” በሚል ስያሜ የተጀመረው ትንኮሳ መቋጨቱን የአገር መከላከያ ያስታወቀው የደረሰውን ጉዳት በመዘርዘር ነው። በተለያዩ የአማራ ክልል የዞን ወረዳዎች ትንኮሳ ለመፈፀም የሞከረው ራሱን ፋኖ ብሎ የሚጠራው ፅንፈኛው ቡድን በሞኝነት በገባበት ጦርነት መደምሰሱን መግለጫው አስታውቋል። ከመከላከያ ማህበራዊ ገጽ የተወሰደው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል።

ብርጋዲየር ጄኔራል ምግበ ሃይሌ እድሜ ልኩን በታሪኩ ግጭት እየጠመቀ የትግራይን ሕዝብ ወደ ጦርነት በማስገባት ያለ ምንም ወታደራዊ ዕውቀት ወጣቱን ወደ እሳት አሥገብቶ የማስፈጀት ታሪክ ያለው ፀረ ሠላምና ፀረ ልማት አራማጅ ነው።

ውጊያ ከብዶት የሸሸውን ወጣት ለምን ሸሸህ በሚል ሰበብ በጅምላ የመረሸን ልምድ ያለው ያለ ዕውቀት የትግራይን ወጣቶች ደም ሲመጥ የቆየ መሆኑ ሳያንሠው አሁን ላይም በሞኙ የፅንፈኛው መሪዎች ነን ባዮች አማካኝነት የሠላም ፈላጊውን የአማራን ወጣት ህይወት ለመቅጠፍ እንቅስቃሴ የጀመረ መሆኑ ታውቋል።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ባለፈው ጊዜ በነበረው የሰሜኑ ጦርነት በመቶ ሺህ የሚቆጠር የትግራይ ወጣትን እየረሸነ እያሥረሸነ የፈጀ የጥቁር ታሪክ ፀሃፊነቱ ሳያንስ አሁን ላይም መሠል ድርጊት ለመፈፀም እየተንቀሳቀሰ ነው።

ምዕራብ ትግራይን አስመልሳለሁ በሚል እሳቤ ሁለት ጊዜ የፌዴራል መንግስት ሠራዊትን ለማጥቃት ሞክሮ በአሥር ሺህ የሚቆጠሩ ወጣቶችን ያሥበላ ዉጊያ እምቢ ሲለው የራሱን ታጣቂዎች ረሽኖና ገድሎ ውጊያው ሳይሳካለት አከርካሪው ተመትቶ ሸሽቷል።

ምግቤ ሃይሌ ዘረፋና ሌብነት የተካነበት መደበኛ ሥራው ነው ። በአሁኑ ጊዜ የትግራይን ወርቅ እየዘረፈ በኤርትራ በኩል አድርጎ እየሸጠ ይገኛል። በኢህአዴግ ዘመን በዘረፋና ሌብነት ታዋቂ የነበረ ብቻ ሳይሆን በሰረቀውና በዘረፈው ገንዘብ አዲስ አበባ ላይ ፎቆችን የደረደረ አለፍ ሲልም ዱባይ ላይ ፎቆችን ለመሥራት በቅርብ ጊዜ የተዋዋለ ሥለመሆኑ በሶሻል ሚዲያ ሲነገር ቆይቷል።

በጦርነት ከቀቀለው ወጣት በተጨማሪ የረሸናቸው በብዙ ሺህዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች በመኖራቸው ትግራይ ሰላም እንድትሆን ከቶውንም አይፈቅድም። ምክንያቱም ደግሞ የትግራይ ሕዝብ ልጆቹን ይጠይቀኛል የሚል ስጋት አንደኛው ሲሆን ሌላኛው ደግሞ እያደረገ ያለው የወርቅ ዘረፋ እንዳይጋለጥበት በማሠብ ነው።

በሌላ በኩል ምግበ ሀይለ የፕሪቶሪያን ስምምነት እንዲፈርስ እንዳይሳካ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ያለ ከመሆኑም በላይ የጊዜያዊ መሥተዳድሩን ማህተም ለመንጠቅ እና በሀይል አፍርሶ ሥልጣን ለመያዝ የሞከረ የፀረ ሠላምና ፀረ ልማት አራማጅ ነው።

የሠላም ጠንቅ የሆነው ምግበ ሃይሌ ለዚህ መሰሪ ተግባሩ ጅላጅሉን ፋኖ እንደ ተባባሪነት በመጠቀም ፅንፈኛው ፋኖ በራሱ ክልል ላይ ያልተገባ ውድመት እንዲፈፅም አዞታል። ነገር ግን ዘመቻ አንድነት በሚል ስያሜ ፅንፈኛውን አሥተባብሮ በጀመረው ትንኮሳ ከፍተኛ የሆነ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሷበታል።

በደቡብ ጎንደር፣ በምዕራብ ጎንደር፣ በሰሜን ጎጃም፣ በምስራቅ ጎጃም፣ በምዕራብ ጎጃም እንዲሁም በሰሜን ወሎ የምግበ ሀይለ ተላላኪ ፅንፈኞች በለኮሱት እሳት ተለብልበዋል።

በዚህ ሁለት ቀናት ብቻ 317 የተገደ’ለ፣ 41 የተማረከ፣ 125 የቆሰለ፣ 27 እጅ የሠጠ፣ 51 በምህረት የገባ፣ 15 መረጃ አቀባይ የተያዘ፣ በድምሩ 576 የሠው ኪሳራ ሲደርስበት 01 መትረየስ፣ 119 ክላሽ፣ 46 ኋላቀር መሣሪያ፣ 08 ሽጉጥ፣ 22 ቦምብ፣ 2,290 የተለያዩ ዓይነት ተተኳሾች፣ 28 ትጥቅ፣ የመገናኛ ራዲዮ፣ ተሽከርካሪ፣ ባጃጅ፣ ሞተር ሳይክልና ሌሎች ልዩ ልዩ ቁሶችም በሠራዊታችን ቁጥጥር ስር ውለዋል።

ይህ በምግበ ሃይለና በግብረ አበሮቹ አይዞህ ባይነት ተነሳስቶ በህዝብ ላይ ጉዳት ለማድረስ የተነሳው ፅንፈኛ ቡድን በዚህ ልክ ኪሳራ የደረሰበት ሲሆን በህይወት የተረፈው እግሬ አውጭኝ የተበታተነ መሆኑ ተረጋግጧል።

በቴሌግራም ያግኙን https://t.me/+f_kxmaPjD-9jYTdk

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ሻዕቢያ ለአውሮፓ ሕብረት ያቀረበው ጥያቄ የ”ዝምታ” መልስ ተሰጠው
Gov’t Striving for Sustainable Peace & Open for Peace Talks: PM Abiy
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2