“እስራኤል ኢትዮጵያ የቀይ ባህር ተዋሳኝ ለመሆን ለያዘችው ሁለንተናዊ ጥረት ያልተገደበ ድጋፍ ታደርጋለች!” ቤንጃሚን ኔታንያሁ፣ የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር
ዛሬ ጠዋት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ከእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋር በስልክ ተነጋግረዋል።
ሁለቱ መሪዎች በአፍሪካ ቀንድ በተለይም በቀይ ባህር ቀጠና እያደገ የመጣውን ሽብርተኝነት በጋራ ለመፋለም በሚችሉበት ዙሪያ ሰፊ ምክክር ያደረጉ ሲሆን ኢትዮጵያ የቀይ ባህር ተዋሳኝ ሀገር ለመሆን በምታደርገው ሁለንተናዊ ትግል እስራኤል ከኢትዮጵያ ጎን እንደምትቆም ለጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ አረጋግጠውላቸዋል።
በስልክ ልውውጣቸው መጨረሻ የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ለኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የጉብኝት ግብዣ ያቀረቡላቸው ሲሆን ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ በተመሳሳይ ቤንጃሚን ኔታንያሁ ኢትዮጵያን እንዲጎበኙ ጥሪ አቅርበውላቸዋል።
ሁለቱ ሃገራት በኢነርጂ፣ በመሰረተ-ልማት ግንባታ፣ በግብርና፣ በማዕድን፣ በቱሪዝምና ንግድ ዘርፎች በጋራ ለመስራት ውል ማሰራቸው ይታወቃል።
ምስል፦ From Archive

