Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ታላቁ ህዳሴ ግድብ በመገባደጃ ምዕራፍ ላይ

    April 1, 2023

    የአሊባባ ግሩፕ በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ገበያ ለመጀመር የሚያስችል ስራ መጀመሩን ይፋ አደረገ

    August 22, 2024

    ዶናልድ ትራምፕ በቁጥጥር ሥር ውለው በቀረበባቸው ሰላሳ አራት ክሶች ጥፋተኛ አይደለሁም አሉ

    April 6, 2023

    የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰነድ የሌላቸው የኤርትራዊ ስደተኞች መታሰራቸውን ኮነን፤ “ያለ ህጋዊ ማስረጃ የትኛው አገር መኖር ይቻላል?”

    June 4, 2023

    ቻይናዊው የፀሃይ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ከ9 ግብረ አበሮቻቸው ጋር የውጭ አገር ብሮች በማተምና በጥቁር ገበያ ወንጀል ታስረው ፍ/ቤት ቀረቡ

    September 5, 2023
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  OPINION  ሞኝን እባብ ሁለቴ  ነደፈው – አንዴ ሳያይ፣ ሁለተኛ ደግሞ ሲያሳይ
(ክቡር ገና)
OPINION

ሞኝን እባብ ሁለቴ  ነደፈው – አንዴ ሳያይ፣ ሁለተኛ ደግሞ ሲያሳይ
(ክቡር ገና)

Ethioreview newsEthioreview news—May 19, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በሀገራችን “ሞኝን እባብ ሁለቴ  ነደፈው – አንዴ ሳያይ፣ ሁለተኛ ደግሞ ሲያሳይ” የሚባል ምሳሊያዊ አነጋገር አለ፡፡ እንግዲህ ሞኙ መጀመሪያ እባቡን ሳያየው ነደፈው ለሁለተኛ ጊዜ የነደፈው ግን እንዲህ አድርጎ ነደፈኝ ብሎ ለሌላ ሰው ለማሳየት በሚሞክርበት ጊዜ መነደፉን ልብ ይሏል፡፡

ይህ አባበል ከሰሞኑ የኢትዮ ቴሌኮም ሁኔታ ጋር ይመሳሰላል፡፡ መጀመሪያ ላይ ተቋሙ ህዝቡ የኢትዮ ቴሌኮም ባለድርሻ ይሆናል ሲል አበሰረን፡፡ በመቀጠልም የአክሲዮን ድረሻው ለህዘብ ሽያጭ ቀርቦ እቅዱ በጣም ሲያንስ ትረካው ተቀየረ፡፡

አሁን ደግሞ የድርጅቱን ትልቅ ድርሻ የውጭ ባለሀብቶች ይገዙታል የሚል ሽኩሹክታ እየተሰማ ነው፡፡ እናም ለውጭ ባለሀብት ተሸጦ ከታክስ ጠቀም ያለ ገንዘብ ይገኛል፤ ከዚህም ተጠቃሚ እንሆናለን የሚል አይነት ከንቱ አስተሳሰብ እየመጣ ይመስላል፡፡

የወርቅ እንቁላል እምትጥልን ዶሮ በመሸጥ በታክስ መልክ ጥቂት እንቁላሎችን አገኛለሁ ብሎ ማሰብ ስትራቴጂያዊ አመለካከት ሳይሆን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ እጅ መስጠት ነው፡፡ የወተት ላምን ሽጦ ወተት ከገበያ እገዛለሁ ብሎ እንደመጃጃልም ይቆጠራል፡፡

ባለቤትነት ወሳኝ ነው

በኢትዮ ቴሌኮም ባለቤትነት ከዘለቅን ትርፉን ለራሳችን ጥቅም እናውላለን፣ የወደፊት አድገትና ልማታችን ላይ እንወስናለን እንዲሁም የሚያዋጣንን ስትራቴጂ ነድፈን እንጓዛለን፡፡ ይህ ሳሆን ቀርቶ ተቋሙን ለውጭ ባለሀብት ሽጠን ታክስ እንሰበሰባለን ካልን ግን ከባዶ ተስፋ በስተቀር ምንም ጠብ አይልልንም፡፡ ከታክስ ገቢ እንሰበስባለን ብለን ስናስብ ደግሞ የታክስ ስወራ፣ ገቢን አሳንሶ ማቅረብና ወደ ውጭ ሀገር ማሸሽ እነዳለም አንዘንጋ፡፡ ታላላቅ ድንበር ዘለል ካምፓኒዎች ደግሞ ታክስ በመሰወር፣ በመቀነስና በማሸሽ ረገድ የተካኑ ናቸው፡፡ በዚህ በኩል በሌሎች ታዳጊ ሀገሮች የደረሰው መታለል በኢትጵያም ላይ እንደሚደርስ እሙን ነው፡፡

ነገርን ከሥሩ ውሀን ከጥሩ!

ኢትዮ ቴሌኮም በቅርቡ የ10 በመቶ ድርሻን በአክሲዮን ለህዝብ ሽያጭ ማቅረቡና በእቅዱ መሰረት ያሰበውን ያህል ሽያጭ ያለማከናወኑ ድርሻውን ለውጭ ባለሀብት ለመሸጥ ምክንያት መሆን የለበትም፡፡ እንዲያውም አሁን ድርሻውን ለውጭ ባለሀብት መሸጥ የሚለውን የማያዋጣ ሀሰብ እርግፍ አድርጎ በመተው ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ጉዳዩን የሚያሰላስልበት፣ የሚተነትንበትና መስተካከል ያለበትን የሚያስተካክልበት ወቅት ነው፡፡

ነገርን ከሥሩ ውሀን ከጥሩ እንደሚባለው ቴሌ ለህዝብ ያቀረበው የአክሲዮን ሽያጭ ለምን አልተሳካም ብሎ መጠየቅ ብልህነት ነው፡፡ ህዝቡ በአሁኑ ወቅት በብዙ ጉዳይ ላይ ጥርጣሬ አለው፡፡ በአክሲዮን ሽያጭ ሂደቱም ላይ ሙሉ መተማማን የለውም፡፡ በዚያ ላይ የካፒታል ገበያው ገና በሁለት እግሩ አልቆመም፣ እንዲሁም ይህ ወቅት ከፍተኛ የጥሬ ገንዘብ እጥረት የተከሰተበት ጊዜ ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ግን ህዝቡ በወደፊት እጣ ፈንታው ላይ ጥርጣሬ አለው፡፡ እናም ህዝቡ ተሳስቷል ማለት እንችላለን?

በዚህ ተጨባጭ ሁኔታ ውስጥ ሆነን ያለንን ብሄራዊ አንጡራ ሀብት ለውጭ ባለሀብት አሳልፈን መስጠት ዘመናዊ መሆን ወይም ከጊዜው ጋር መራመድ ሊሆን አይችልም፡፡ እንዲያውም ይህን ካደረግን ከላይ የተቀስነውን ምሳሊያዊ አነጋገር ከመድገምም በላይ ለትውልድ የሚተርፍ ኪሳራ ነው፡፡ እዳውም ይህን ድርጊት ያስፈጸሙ የሀገሪቱ አመራሮች ካለፉ በኋል ኢትዮጵያ በቀጣይነት ስትከፍለው የመትኖረው ነው የሚሆነው፡፡

ለህዝብ የቀረበው የመጀመሪያው የአክሲዮን ሽያጭ ለምን አልተሳካም? አለመሳካቱስ ለምን አያስደንቅም? አትራፊው፣ እየተስፋፋ ያለው፣ 300 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ ሀብት ያለው ኢትዮ ቴሌኮም 30 ቢሊዮን ብር በአክሲዮን ሽያጭ ለማሰባሰብ አቅዶ ያገኘው 3.2 ቢሊዮን ብር ብቻ ነው፡፡ ለምን?

ለምን ማለት ጥሩ፡፡ ምክንያቱም አንድ ግለሰብ አንድን ትልቅ ቤት ወይም ህንጻ ገዢዎች በከሰሩበት፣ እርግጠኛ ባልሆኑበትና ሂደቱ ህጋዊነቱን ባለጠበቀበት ሁኔታ መሸጥ ስለማይችል ነዋ!

በዚያ ላይ
የካፒታል ገበያ ስር ባልሰደደበት
የጥሬ ገንዘብ እትረት ባለበት
የአክሲዮን ድርሻን በተመለከተ አስተማማኝ ህጋዊ መዋቅር በሌለበት
አክሲዮን የገዙ ሰዎች አክሲናቸውን ሽጠው ገንዘባቸውን ለማግኘት ግልጽ አሰራር በሌለበት
ክልከላና እገዳ ብቻ በሰፈነበት
የጥርጣሬ ጥቁር ደመና ባጠላበት ሁኔታ ህዝቡ እንዴት አክሲዮን ይገዛል?

በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሚባለው ህዝቡ በዋጋ ንረት፣ በግጭት፣ በውጭ ምንዛሪ ተመን ቅነሳ እንዲሁም ባልተረጋጋ የኢኮኖሚ ሁኔታ አሳሩን እየበላ ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ዜጎች መቆጠብ አይችሉም፡፡ የሚችሉትም እምት የላቸውም፡፡

የኢትዮ ቴሌኮም  የአክሲዮን ሽያጭ በተመለከተ አንድ ግልጽ መሆን ያለበት ነገር አለ፡፡ የአክሲዮን ሽያጩ ከዕቅዱ በጣም ዝቅ ማለቱ ኢትጵያውያን በኢትዮ ቴሌኮም ላይ እምነት የላቸውም ማለት አይደለም፡፡ ይልቁንም የአክሲዮን ድርሻ ባለቤት መሆን ድርጅቱን መቆጣጠር ማለት አይደለም፣ ተገቢ የትርፍ ክፍፍል አናገኝም፣ አክሲዮናችንን ሸጠን ለመውጣት ብንፈልግ ግልጽ ስትራቴጂ የለም ብለው  ስሚያምኑ ነው፡፡

እና አሁንስ ምን እያደረግን ነው? ተቋሙም ሆነ የበላይ አመራሮች እነዚህን መሰረታዊ ችግሮች ግልጸኝነት በማጎልብት፣ ሊያሰራ የሚችል ደንብና መመሪያ ባማስፍንና የጥሬ ገንዘብ ፍሰቱን ቀልጣፋ በማድረግ ከመፍታት ይልቅ የውጭ ባለሀበቶች ድርጅቱን እነዲታደጉት ባሻገር እየቃኙ እንደሆነ እየነገሩን ነው፡፡ ይህ ተቃርኖ የአንድን ቤተሰብ የከበረ ቅርስ በርካሽ ከመሸጥ ጋር ይመሳሰላል፡፡

አለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም የመንግስት የልማት ድርጅቶች ወደ ግል እንዲዛወሩ ጽኑ ፍላጎት አለው፡፡ የመንግስት ድርጅቶች ውጤታማ እነዲሆኑና እንዲስፋፉ ለግል ባለሀብት መሸጣቸው አስፈላጊ ነው ሲል ተቋሙ ይሰብካል፡፡ እዚህ ላይ የሚሸጡት ለማን ጥቅም ሲባል ነው ብልን መጠየቅ አለብን፡፡

የኢትዮ ቴሌኮምን ወደ ግል ንብረትነት ማዘዋወር የኢትዮጵያን ዜጎች አቅም እንዲኖራቸው ማስቻል ሳይሆን ህዝቡንና መንግስትን አቅም ማሳጣት ነው፡፡ እንደዚህ አይነት የሀገር ሀብት አንዴ በውጭ ባለሀብቶች እጅ ከገባ መንግስት በተቋሙ ላይ ያለውን ቁጥጥር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ያሳጣዋል፡፡ በዚህም ምክንት መንግስት ዋጋን የመወሰን፣ የቴሌ መሰረተ ልማቶችን ላልደረሳቸው ዜጎች የማዳረስ፣ ቴክኖሎጂን የማስፋፋት፣ አልፎ ተርፎም ብሄራዊ ደህንነትን የመከላከል አቅሙን ያጣል፡፡

ይህ ሁሉ ዘርፈ ብዙ ኪሳራ የሚመጣው ድርጅቱ ተሸጦ የታክስ ገቢ ይገኛል ተብሎና የተሸለ ውጤት ይመዘገባል በሚል አጉል ተስፋ ነው፡፡ ይህ ሁኔታ አንድ ሰው የመኪናውን ሞተር ከሸጠ በኋላ ከነዳጅ ወጪ ድኛለሁ ብሎ እራሱን እነደማሞኘት የሚቆጠር ነው፡፡

ጥገኝነትና ተጋላጭነት – ከፊታችን የተደቀነ አደጋ

ኢትዮ ቴሌኮም ከእጃችን ከወጣ ለፋይናስ፣ ለሀገር ደህንንትና ለኮሙኒኬሽን ወሳኝ የሆነው የኢትዮጵያ የዲጂታል መሰረተ ልማት በውጭ ባለሀብቶች እጅ ይወድቃል፡፡ የውጭ ባሀብቶች ትርፋቸውን ለማጋበስ ይተጋሉ፡፡ ለኛ ብሄራዊ ጥቅም ደንታ የላቸውም፡፡ ይህ ሁኔታ እንደ አርጀንቲናና  ዛምቢያ በመሳሰሉ ሀገሮች ታይቷል፡፡ በገዛ ሀገር የውጭ ባለሀብቶች ገባርና ሎሌ መሆን ማለት ይህ ነው፡፡

ዛሬ የኢትዮ ቴሌኮም ገቢ የመንግስትን በጀት ይደግፋል፡፡ ነገ በውጭ ባለሀብቶች እጅ ሲገባ ግን ኒዮርክ፣ ለንደንና ዱባይ በሚገኙ የአክሲዮን ባለድረሻ ቱጃሮች ኪስ ነው የሚገባው፡፡

በእርግጥ ጥቂት ታክስ ይከፍላሉ
ምናልባት!
አልፎ አልፎ!
ለዛውም ደስ ካላቸው!

በዚህ መሀል አይበለውን ኢትጵያ ውስጥ የሆነ ቀውስ ቢፈጠር እነዚህ የውጭ ባለሀብቶች ነቅለው ይወጡና ኢትዮጵያ ዋንኛ የመገኛኛ ድም ስሯን ታጣለች ማለት ነው፡፡ ወይም ደግሞ የቴሌ ኮም አገልግሎት ለማግኘት ክራይ ለመክፈል ትገደዳለች፡፡

የሚያዋጣው መንገድ – ሽያጭ ሳይሆን ማሻሻያ

ኢትዮ ቴሌኮምን በሽያጭ ለውጭ ባለሀብቶች ከማስረከብ ይልቅ ኢትዮጵያ የሚከተሉትን ብትፈጽም አዋጭ ዘዴ ይሆናል ስንል የዜግነት ምክራችንን እንለግሳለን፡-
• በኢትዮ ቴሌኮም ውስጥ መልካም አስተዳደርና ግለጸኝነትን ማጎልበት
• ከበቂ የጥሬ ገንዘብ ፍሰትና የግብይት ድጋፍ ጋር በኢትዮጵያ የመዋለ ነዋይ ሰነድ ገበያ በአግባቡ የአክሲዮን ድሻዎችን ይፋ ማድረግ
• ለአነስተኛ የአክሲዮን ባለድረሻዎች የዋስትና ከለላ በመስጠት መጠነ ሰፊ የዜጎችን ተሳትፎ መፍቀድ
• አክሲዎኖች በግልጽ የሚገዙበትና የሚሸጡበት ሀቀኛ የካፒታል ገበያ ማጎልበት
• በቴሌ ኮም ዘርፍ ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች በኢትዮጵያን ጥብቅ ቁጠጥር ስር እንዲዘልቁ ማድረግ

እምነትን፣ ገበያንና ተቋማትን መገንባት ወሳኝ ነው፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ለህዝብ የቀረበው የቴሌ የአክሲዮን ድረሻ ሽያጭ በሚገባ ባለመታቀዱና በይድረስ ይድረስ በመከናወኑ የተጠበቀውን ያህል ውጤት አላስገኝም፡፡ ይህ ሁኔታ እንደ ኢትዮ ቴሌኮም ያለን የወርቅ እንቁላል የምትጥልን ዶሮን ለውጭ ባሀብት ለመሸጥ የሚያንደረድር አይደለም፡፡ ኢትዮጵያ የሌሎች ሀገሮችን ስህተት መድገም የለባትም፡፡

እጅግ የከበረ ብሄራዊ ሀብቷን በአንድ ጊዜ ብቻ በሚገኝ ሽያጭ ለባእዳን ማስተላለፍን አሻፈረኝ በማለት የወደፊት መፃይ እድሏን የመወሰን እጣ ፈንታዋን የመወሰን ምርጫ አላት፡፡ እንደ ሞኙ ሁለት ጊዜ በእባብ ከመነደፍ እንጠንቀቅ!

OPINION
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
አሌክሳንደር ኢሳክ ከኒውካስል ሊለቅ ይችላል ተባለ
የውጭ ዜጎችን የመሬት ባለይዞታ የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ ነገ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይቀርባል
Related posts
  • Related posts
  • More from author
OPINION

እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ…

April 8, 2026
OPINION

ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት!

April 8, 2026
OPINION

ሙስጠፌ ተረኛው ባለስልጣን – የሃሰት ትርክ ዘመቻ በደቦ

March 28, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2