Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  “ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ
News

“ ንስሃ ገብቻለሁ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል ፤ ሲያፈገፍጉ የተረሸኑ ታጋዮች አሉ ” አቶ ጌታቸው ረዳ

Ethioreview newsEthioreview news—May 13, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የትህነግ ቃል አቀባይ በመሆን ጦርነቱን በፕሮፓጋንዳ ሲያቀጣጥሉት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ አሁን ላይ የሆነው ሁሉ እረፍት እየነሳቸው ያሉ ይመስላል፡፡ በጦርነቱ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ ቁልፍ ሚስጢሮችን ሲከላከሉና ሲያመክኑ ቆይተው አሁን ላይ ራሳቸው ይፋ እያደረጉ ነው።
ከትግራይ ጊዜያዊ መንበራቸው በአመጽና በጠመንጃ ኃይል እንዲወገዱ የተደረጉት አቶ ጌታቸው ውስን ያሉዋቸውን ጄነራሎች ስም እየጠቀሱና በጥቅሉ ተጋባራቸው “የብረሃን ስራ በብርሃን ነው” እንደተባሉ ጠሰው ይፋ አድርገዋል፡፡

 አቶ ጌታቸው ረዳ ከፋና ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ በውጊያ ወቅት ያፈገፈጉ የትግራይ ታጣቂ ኃይሎች ዘጠና ሜትር ረቀት ላይ ሆነው በሚያዋጉ ጄነራሎች መረሸናቸውን መስክረዋል፡፡ “ውሸት በቃኝ” በማለት የሚያውቁትን እየዘረገፉ ያሉት አቶ ጌታቸው፣ ይህን የሚያደርጉ ውስን የጦር መኮንኖችና የፖለቲካ አመራሮች ተቧድነው በወርቅ ዝርፊያ ላይ መሰማራታቸውን አመልክተዋል፡፡ በዚህም ሳቢያ ትህነኝ ወንጀለኛ ድርጅት እንደሆነ አመልክተዋል።

በትግራይ ያለው ህገወጥ የወርቅ ንግድ ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኃላ የጀመረ ሳይሆን በጦርነቱ ጊዜም ሳይቀር ሲሰራ የነበረ ወንጀል እንደሆነ አመልክተዋል፡፡ ዛሬ ድረስ ይኸው ዘረፋ አሁንም በቡድን መቀጠሉን አስታወቀዋል።

አቶ ጌታቸው፤ ብዙ ሰው የወርቅ ንግድ የፕሪቶሪያ ስምምነት ከተፈራረምን በኃላ የጀመረ እንደሚመስለው አመልክተው ሃቁን ገልጠዋል። ጦርነቱም እየተካሄደ፣ የትግራይ ልጆች እየተማገዱ የወርቅ ዝርፊያውና ንግዱ ይካሄድ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ በዚህና በበርካታ ምክንያቶች “እኔ የማምንበትን ትግል ነው ያካሄድኩት ብዬ አምናለሁ” ያሉት አቶ ጌታቸው ይህን ሲሉ ዛሬ ድረስ አማራና አፋር ክልልን ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የወረረው ፓሪታቸው የፈጸመውን ግፍ ይሁን ሌላ ጠያቂው አልጠየቃቸውም።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

“… በማምንበት ትግል ውስጥ የትግራይን ህዝብ አጀንዳ ይዘው የታገሉ ብዙ የጦር መኮንኖች አሉ፡፡ ለሰሩት ስራ ያለኝ ክብር በፍጹም አይቀንስም፡፡ ግን ደግሞ ገና ገና ጦርነቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶችን ይበላ በነበረበት ወቅት ሳይቀር ምሽግ ለመቆፈር ብለን የወሰድነው ኤክስካቫተር ወርቅ ለመልቀም ይጠቀሙበት የነበሩ አዛዦችም ነበሩ” ሲሉ ሁለት መልክ ያለውን አመራር ተግባር ለይተው አሳይተዋል።

“ሲዋሹ በጣም ነው የሚገርመኝ” ያሉት አቶ ጌታቸው “እኔ እስካሁን የዋሸሁት ይበቃኛል እስካሁን የታገስኩትም ይበቃኛል” ከሚል እሳቤና እምነት የሚያውቁትንና የደበቁትን ሚስጢር ለሕዝብ መግለጻቸውን አስታውቀዋል።

አቶ ጌታቸው “የኤርትራን ሰራዊት እናፍርሰው” በሚል ዓላማ ዘመቻ የጀመረና ዘመቻውን የሚመራው አመራር ሰዎችን እያፈነ ገንዘብ ሲሰበስብ እንደነበር ተናግረዋል። የሰው ልጅ ይሸጡ እንደነበር አመልክተዋል፡፡ ይህን ሲሉ የትህነኝ ቁንጮዎች ወነጀለኛነት ደጋግመው በመግለጽ ነው።
የሰው ልጅ ሽያጭን ሲያስረዱ “ሰው ሲሸጡ የሚኖሩ ሰዎች አሉ” ቀጥለው የሽያጩን ምደባ ሲገልጹ የሚሸጠው ሰው ኤርትራዊ ከሆነ ወይም ኤርትራዊ የሚሸጥ ከሆነ “ንብረት ” በሚል ስያሜ ይጠራል። እናም ሽያጩ መከናወኑን ለመለየት “ንብረቱ ወርዷል ወይ ? ይባላል።

አቶ ጌታቸው የድርጅታቸውን ውንብድና ሲገልጹ ምስኪኖች ይታፈኑና ቤርተሰቦቻቸው ውጭ ሀገር ያሉት ክፍያ በውጭ አገር አገር ባሉዋቸው ሰዎች አማካይነት ገቢ እንዲደረግላቸው ይደረጋል፡፡ ይህ አገር ሲመራ የነበረ የማፍያ ቡድን በእያንዳንዱ ሰው በትንሹ አራት ሺህ ዶላር ነው የሚጠይቀው።
ለምሳሌ ሲያስረዱ ሃያ ሰው ካፈኑ ሰማኒያ ሺህ ዶላር ያገኛሉ፤ በዚህ የውጭ አካውንት ከፍተው በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን እየሸጡ፣ እያገቱ ገንዘብ ከሚሰበስቡት መካከል ከፍተኛ አመራሮች እንደሚገኙበት ገልጸዋል። ይህ ተግባር መጀመሪያ በኤርትራውያን መጀመሩን ከዛም ወደ ትግራይ ተወላጆች መዞሩን አስታውቀዋል። የትህነግና ሻዕቢያ ፕሮፓጋንዲስቶች ይህን ጉድ ተኝተውበት መኖራቸው መነጋገሪያ ሆኗል።

እዚህ ጉዳይ ላይ ጥናት ተደርጎ አመራሮቹ ለህግ እንዲቀርቡ ሙከራ ቢደረግም ማቅረብ እንዳልተቻለና ጥናቱም ከተሰራ ሁለት ዓመት እንደሆነው ጠቁመዋል። አቶ ጌታቸው “ይሄን የሚመራ የመረጃ መምሪያ ኃላፊ እርምጃ እንዲወሰድበት ወይ ከስራ እንዲነሳ ብለን ወስነን ስናበቃ ለማስፈጸም ኃላፊነት የሚሰጣቸው የፀጥታ አመራሮች አላስፈጸሙም” ማለታቸውን ይፋ አድርገዋል።

የፀጥታ አመራሮች በባህሪያቸው ጥፋት ያጠፋውም ያላጠፋውም የመተጋገዝ ባህሪ እንዳላቸው አቶ ጌታቸው በንግግራቸው አስታውቀዋል፡፡ አክለውም ከዚህ በተጨማሪ አቶ ጌታቸው ረዳ በወርቅ ንግድ ውስጥ ስለተነከሩ አመራሮች ዝርዝር አብራርተዋል።

“ወርቅ ንግድ ውስጥ የገባ ለትግራይ ነጻነት እስከመጨረሻው እሰዋለው እያለ የሚፎክር ጀነራል አለ አሁንም፤ እንዲህ አይነቱን የወርቅ ንግድ ቀጥሏል” ብለዋል። ስም ጠቅሰውም ማስረጃቸውን ዘርዝረዋል።

እነ ጀነራል ምግበ በወርቅ ንግድ ውስጥ ተሰማርተው እንደሚገኙ በስም ጠቅሰው ይፋ ያደረጉት አቶ ጌታቸው ይህ በውል የሚታወቅ፣ በቡድን የሚሰራ እንደሆን ጠቅሰው እርምጃ ለመውሰድ አጋጋች ያደረገውም ይኸው ቁርኝት መሆኑን አመልክተዋል።

አቶ ጌታቸው ” … ወጣቶች ለስደት በሚዳርግ ደረጃ ወደ ተራ የወርቅ ንግድ ገብተው ሲያበቁ የስርቆት ተግባራቸውን የትግራይ ግዛት አንድነት የማረጋገጥ አርገው እየገለጹ እንደገና ይሄን ወጣት ለሌላ መስዕዋትነት ሊዳርጉ እየተንቀሳቀሱ ነው” ሲሉ በስም የጠቀሷቸውን ጨምሮ ቡድናቸው ለዝርፊያው የሚሰጠውን ምክንያት ጠቁመዋል።

“እነ ኃይለስላሰም አሁን በትግራይ ህዝብ አንድነት ስም የትግራይን ወጣት ከኤርትራም ጋር ቢሆን አብሬ ለማገዶነት እንዳርገዋለው በሚል በጀግንነት ስም እየፎከረ ነው” ሲሉ ገልጸዋል። አክለውም እነ ምግበ ፣ እነ ኃይለስለሰን “በወንጀል የተነከሩ ሰዎች ናቸው” ብለዋል።

ድንገት ሰላም ቢፈጠር “ተጠያቂ እሆናለሁ፤ አደጋ ውስጥ እገባለሁ” ብለው ስለሚያስቡም ግርግር እንዲያልቅ አይፈልጉም” ሲሉ ተናግረዋል።
የትግራይን ህዝብ ለሌላ ጦርነት ለማስገባት እያሰቡ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ ጌታቸው ” የፌዴራል መንግሥት ድንገት ውጊያ ይገጥመናል በሚል ስጋት ሻዕቢያ ውጊያውን ትግራይ ውስጥ እንዲያካሄድ የሚያስችል ስትራቴጂ ተቀይሶ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ገልጸዋል።

” ሰላም መስፈን አለበት፤ በኢትዮጵያም በኤርትራም መካከል ጦርነት መፈጠር የለበትም፣ የኤርትራ ህዝብ ለአደጋ መዳረግ የለበትም” የሚል ዕምነት እንዳላቸው የገለጹት አቶ ጌታቸው “መምረጥ ካለብኝ የትግራይ ህዝብ ድጋሚ የጦር አውድማ የሚሆንበት ሁኔታ እስከመጨረሻው ድረስ እንዳይሆን እታገላለሁ ” ሲሉ ለአገራቸው እንደሚያደሉ አስታወቀዋል።

በዚህ አግባብ እንቅፋት የሆኑት የወርቅ ንግድ ላይ የተሰማሩት ዘራፊዎች ናቸው ሲሉ ደጋግመው አመልክተዋል። ” የግንባር አዛዥ ነኝ ይላል ኝ ወርቅ ሲዘርፍ ነው የሚውለው ” ሲሉ የስብዕናቸውን መቆሸሽ አሳይተዋል።

“በ2014 ወጣቶች በየግንባሩ ሲተናነቁ በርቀት ዳባት፣ደባርቅ ፣ሊማሊሞ ሆኖ ውጊያ ይመራ የነበረ ሰው በተመሳሳይ ሰዓት በኤክስካቫተር ወርቅ እየቆፈረ ይሸጥ ነበር” ሲሉ የነበረውን የሃፍረት ደረጃ አሳይተዋል። አዋጊዎቹ ብቻ ሳይሆኑ በዚህ የዝርፊያ ኔትዎርክ ፖለቲከኞችም እንዳሉበት አመልክተዋል። አክለውም በመቶ ሚሊዮን ዘርፏል ስላሉት ኃይለስላሰም ተናግረዋል።

” ኮምቦልቻ issue account ነበር፤ በዛ ሰዓት ጦርነት ላይ ገንዘብ ስለሚያስፈልገን ትክክለኛ ውሳኔ ነው” በማለት በወቅቱ የተፈጸመውን ወረራ ያሞካሹት አቶ ጌታቸው፣ ገንዘብ እንዴት ከባንኮች እንደሚዘረፈ የተነደፈውን እቅድ አስታውሰዋል።

በዕቅዱ መሰረት “የወሰነው የግል ባንኮች ሳንነካ የመንግሥት ባንክን ብቻ እንውሰድ ብለን ፓለቲካሊ ወሰንን” ሲሉ ዛሬ የሚያበሻቅጡትን ደርጅታቸውን ገበና የሚገልጹት አቶ ጌታቸው፣ ከዘርፋው ውሳኔ በሁዋላ እሳቸው እስከሚያውቁ ትድረስ አራት ቢሊዮን ብር መወሰዱን አመልክተዋል።

መጠኑ issue account ላይ የተቀመጠ በመሆኑ ይሄን ከብሔራዊ ባንክ ማረጋገጥ እንደሚቻል አመልክተዋል። ” ጊዜያዊ አስተዳደር ከሆንኩም በኃላ ወረቀት መጥቶልኛል ምን እንደተፈጠረ ባንኮች ውስጥ ግለጹልን የሚል እና issue account ውስጥ ያለውን ገንዘብ እንዲሰበስቡ ከተመደቡት ሰዎች መሃል አንዱ የግምባር አዛዥ የሚባለው ኃይለስላሰ በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ነው የወሰደው ወደ አንድ ቢሊዮን አካባቢ ገንዘብ ነው የወሰደው እሱ ስር ተፍ ተፍ የሚሉ የሱ አገልጋዮች የተወሰነ ድርሻቸው የወሰዱ አሉ ” ብለዋል። ሲል ዝርፊያው አግባብ መሆኑን ጠቁመው፣ የተዘርፈውን ሃብት ዳግም የዘረፉትን ኮንነዋል።

አብዛኛው ሰው ትግሉን ለትግራይ ህዝብ ካለው የህልውና ጥቅም አንጻር እንጂ “ገንዘብ አገኝበታለሁ” ብሎ አይደለም የተሳተፈው ብለዋል። “እኔ በማውቀው ባረጋገጥኩት በሰነድ ጭምር እነ ኃይለ የወርቅ ማሽኖችን ሲያስገቡ ነው የሚውሉት” ብለዋል። የፖለቲካ አመራሩም አብሮ የወርቅ ንግድ ውስጥ መሰማራቱን ጠቁመዋል።

ሰዎቹ ማሽን ሲያዝባቸው የፌዴራል ሰዎች ጋር እየተደዋወሉ በመሞጋገስ እንዲለቀቅላቸው ሲማጸኑ እንደሚውሉ አቶ ጌታቸው በቃለ ምልልሳቸው አረጋግጠዋል።

ቀደም ሲል በጠቆሙት በጥናት እያንዳንዱ የዘረፈው ሃብት ተዘርዝሮ እርምጃ እንዲወሰድ ቢጠየቅም እንዳልተቻለ አመልክተዋል። የቀረበውን የጥናት ሰነድ እነ ደብረጽዮን (ዶ/ር) እንደሚያውቁት፤ በሳቸው ሰብሳቢነት ይፋ የሆነና አሁን ድረስ እጃቸው ላይ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

“ትግሉ ውስጥ ትልልቅ አስተዋጽኦ ያላቸው ሰዎች ስም ሌሎችን ይዞ እንዳይጠፋና የውሸት አንድነት ለማስቀጠል ሲባል እምርጃ መውሰድ አልተቻለም” ሲሉ የሚቀርብላቸውን ሰበብ ተናግረዋል። አክለውም “የመረረኝ ሰዓት እርምጃ እንዲወሰድ ዶክመንት አቅርቤም ተግባራዊ አልተደረግም” ሲሉ ጉዳይ ከአቅማቸው በላይ እንደነበር ጠቁመዋል።

እነ ምግበን፣ እነ ኃይለስላሰን በስም ጠቅሰን መጠየቅ ስላልቻልን “ሁሉም የሰራዊት አመራሮች ዘርፈዋል” የሚል የጅምላ መልዕክት እያስተላለፍን ነው የመጣነው ይህ ትክክል አይደለም ብለዋል።

ተጠያቂነት እንዳይሰፍን የፖለቲካ መሪዎቹ እንቅፋት እንደሆኑ ይህን የሚያደርጉትም እነሱም ተጠያቂ ስለሆኑ እንደሆነ አቶ ጌታቸው ረዳ ይፋ አድርገዋል። አብዛኛው የሰራዊት አመራር ግን ሰላም ፈላጊ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡

ጌታቸው ረዳ ጸረ ድሮን እንገዛለን በሚል 1.4 ሚሊዮን መዘረፉን ሲናገሩ በግርምት ነው። ሰዎቹ ይመጣሉ የተባሉ ከእስራኤል ሲሆን በአፋር በኩል ገብተው ላብቶፓቸውን በመዘርጋት ድሮን ሲመጣ ምልክት የሚሰጡ እንደሆነ ለዶር ደብረጽዮን ተነግሯቸው መዘረፋቸውን አመልክተዋል፤ ዝርፊያው በቅንጅት የሚሰራ ሲሆን ዲያስፖራው ያዋጣው ሃብት እንዴት እንደተበላ ለማሳየት ያነሱት ምሳሌ ነው።

በትግራይ ከተደፈሩ ሴቶች 76 በመቶ የሚሆኑትን የሻዕቢያ ሰራዊት እንደፈጸመው ጥናት አጣቅሰው ካስረዱ በሁዋላ፣ በአንድ ትምህርት ቤት በተሰባበረ ሰሌዳ ላይ “ሰላሳ ዓመት ወደሁዋላ መልሳችሁናል፣ አርባ ኣመት ወደሁዋላ እንመልሳችኋለን” በሚል የሻዕቢያ ኃይሎች መጻፋቸውን ጠቅሰው ሁሉም ሲከናወን የነበረው በዕቅድና በፕላን መሆኑን አስረድተዋል። እንግዲህ የደብረጽዮን ትህነግ እያበረ ያለው ከዚህ ዓይነቱ የጥፋት ተቋም ሻዕቢያ ጋር መሆኑ ደርብ ሃዘን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

አቶ ጌታቸው እየደጋገሙ የወንጀል ኢንተርፕራዝ እያሉ የጠሩት የትህነግ ቡድን ከትግራይ ሕዝብ ጫንቃ ላይ ሊወገድ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በአሁኑ ሰኣት እሳቸው ብቻ ሳይሆኑ ከተለያዩ አቅጣጫዎችና በውጭ አገር የድርጅቱ ከጥቂቶቹ በቀር ደጋፊ የሆኑት ሁሉ ፊታቸውን ትህነግ ላይ አዙረዋል። የአማራ ፋኖ ደግሞ ትህነግ ወይም ሞት በማለት የሸዕቢያን የበላይነት ተቀብሎ ኢትዮጵያን በማፍረሱ ዕቅድ ውስጥ ተሳታፊ መሆኑን በይፋ አስታውቋል፤



NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ለምህላቸው ከሚኖሩት መካከል – ሰርጉን ጥሎ ነብስ የታደገው ሐኪም
የመጨረሻው መጀመሪያ የማሪያም መንገድ – ራስ ዱሜራ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2