Skip to content
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
  • News
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የፕሮፓጋንዳ ምችና የጦርነት አሻራ በትግራይ

    March 11, 20230

    ሥርዐት አልባው ንግድ እና ስጋት የፈጠረው የኑሮ ውድነት!

    April 4, 20220

    በጥቃት ሳቢያ ተመድ በአማራ ክልል የረድዔት ሥራዎቹን ሊያቆም ነው – የኤርትራና ኢትዮጲያ የስልክ ግንኙነት ተቋረጠ

    October 9, 20240

    የህወሓት ‘ቀጣይ ዕቅድ’ አፈትልኮ ወጣ

    July 1, 20210
    Prev Next Showing 1 Of 1866
  • Design
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ብልጽግና ከሸነፈ – ቀጣይዋ የአዲስ አበባ ከንቲባ ሌሊሴ ነሜ

    June 19, 20210

    “በግብፅ እና በእስራኤል መካከል ትልቅ ጦርነት በማንኛውም ሰአት ሊፈነዳ ይችላል”

    February 18, 20250

    የቆዳ ዋጋ መውደቅና አገራዊ ኪሳራው

    May 9, 20210

    “ኡሁሩ ኬንያታ የትግራይ አማጺ ቡድን ደጋፊ መሆናቸውን ይፋ አደረጉ”

    October 7, 20220

    Uhuru Pulls Out of First African Union Peace Talks

    October 7, 20220
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • Video
    video

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለፓርላማ የሰጡት ማብራሪያ

    July 4, 2024
    video

    የህብታቸውን ምንጭ የሚያውቁ አይሰጉም! ማብራሪያ

    June 22, 2024
    video

    የሀገር አቀፍ የምክክር ሂደት ይፋዊ የማስጀመሪያ ሥነ ስርዓት

    June 4, 2024
    video

    የምክክር ሂደት ይፋዊ ማስጀመሪያ ላይ ያደረጉት ሙሉ ንግግር

    June 4, 2024
    Prev Next Showing 1 Of 5
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • News
  • Design
  • Video
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  News  የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በምንም መልኩ እንደማይታጠፍ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ በድጋሚ አረጋገጡ፤ አሜሪካ ደገፈች
News

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በምንም መልኩ እንደማይታጠፍ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ በድጋሚ አረጋገጡ፤ አሜሪካ ደገፈች

Ethioreview newsEthioreview news—June 5, 20250
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በቅርቡ የኢትዮጵያ የጸጥታ ምክር ቤት አጠቃላይ የአገሪቱን ጸጥታ ሲገመግም የባህር በር ጉዳይ ግለቱን ጠብቆ እንደሚቀጥል ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ይህንኑ በመድገም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ “ብሔራዊ ጥቅማችን፣ ሀገራዊ ጥቅማችንን አስመልክቶ ያለን አቋም አይዛነፍም” ሲል በድጋሚ ለተወካዮች ምክር ቤት አረጋገጡ። ከኤርትራም ጋር መንግስት የቃላት ጦርነት ውስጥ እንዳልገባ አመልከቱ። አሜሪካ ኢትዮጵያ በሰላማዊና ህጋዊ መነገድ የባህር በር ለማግነት የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አሜሪካ አስታውቃለች።

በኤርትራ በኩል “ትንኮሳ ቢኖርም፤ አንዳንዴ በሆደሰፊነት፣ አንዳንዴ ሰምቶ አንዳልሰማ፣ አንዳንዱን ደግሞ በራሱ በዲፕሎማቲክ ቻናል የሚመለሰውን ለመመለስ ጥረት እናደርጋለን” ሲሉ የተደመጡት ዶ/ር ጌዲዮን ይህን ያሉት ዛሬ ሐሙስ ግንቦት 28 ቀን 2017 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት ነው። ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው በኢትዮጵያ በኩል”ወደፊትም የቃላት ጦርነትውስጥ የምንገባ አይመስለኝም” ብለዋል።

ኢትዮጵያ ኃላፊነት በተሞላው መንገድ የምትራመድ አገር መሆኗን አበክረው የተናገሩት ሚኒስትሩ፣ “ነገር ግን” አሉ “ነገር ግን ብሔራዊና አገራዊ ጥቅማችንን አስመልክቶ ያለን አቋም አይዛነፍም” በማለት መንግስታቸው አስቀድሞ ከያዘው አቋም ፈቀቅ እንደማይል አጉልተው አሳይተዋል። የኢትዮጵያን የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ ዓለም አቀፍ አጀንዳ ማድረግ ያስቻለ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ስራ መሰረቱንም አመልክተዋል። ይህ ንግግራቸው እስራኤል፣ አሜሪካ፣ ፈረንሳይና ሌሎች ተጽዕኖ ፈጣሪ አገራት በይፋ ከሰጡት ድጋፍ ጋር የገጠመ ሆኗል።

ከተሰነጠቀው ትህነግ ተለይተው አዲስ ፓርቲ ያቋቋሙት ወገኖች ሻዕቢያ ኢትዮጵያ የባህር በር አጀንዳዋን እንድትቀይር ጫና ለማድረግ፣ ትህነግም በትግራይ ውስጥ ያሻውን እንዲያደርግና በፌደራል መንግስት ውስጥ የሚፈልገውን ቦታ ለማግኘት ስልት ነድፈው ጫና ለመፍጠር እየሰሩ መሆናቸውን ማመልከታቸው አይዘነጋም። እነዚሁ ክፍሎች ከውስጥ ያገኙትን መረጃ ጠቅሰው እንዳሉት ሁለቱም የመዋጋት አቅም የላቸውም። ሻዕቢያ በተለይ የተዋጊ ቁጥሩ የተመናመነና ተተኪ አልባ መሆኑን ትህነግ መገምገሙን መናገራቸው ይታወሳል። የጌዲዮን መግለጫም ይህንኑ እውነታ ያገናዘበ እንደሚመስል ተመልክቷል። መንግስት በቂ መረጃ ስላለው የጦርነት ስጋት እንደሌለበትም አመላካች እንደሆነ ተመልክቷል።

More stories

“ABO Shanee waliin mariin Nageenyaa iftaan Taanzaaniyaatti gaggeeffama”

April 23, 2023

የኢትዮጵያ ነርሶች ማህበር ታካሚዎች ለሞትና እንግልት እንዳይዳረጉ አስጠነቀቀ

May 19, 2025

ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል

March 28, 2026

“የሰው ልጅ የመብት ተከራካሪ ነን” የሚሉት የእነ ሂውማን ራይትስ ዎች የሐሰት ሪፖርት ገበና ሲጋለጥ

December 19, 2021

የኢትዮጵያን የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ ዓለም አቀፍ አጀንዳ ማድረግ ያስቻለ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ስራ መሰራቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) ገለጹ ሲል ኢትዮኢንሳይደር የሚከተለውን ዘግቧል።

ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሚኒስትሩ ከፓርላማ አባላት በቃል ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ ተወካይ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ፤ የኢትዮጵያ እና ኤርትራን ወቅታዊ ሁኔታ አንስተዋል።

ኤርትራ እና ኢትዮጵያን “ወደ ጦርነት ጅማሮ” እየወሰዳቸው ያለ “የቃል ጦርነቱ የተጀመረ ይመስለኛል” ያሉት የፓርላማ አባሉ፤ ሁለቱ ሀገራት በአሁኑ ወቅት ያላቸው “ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት” በምን መልኩ እንደሚገልጽ ጠይቀዋል። ዶ/ር ደሳለኝ ከኤርትራ ጋር “ወደ ጦርነት መግባት እድል አለ ወይ?” ሲሉም ተጨማሪ ጥያቄ አክለዋል።   

ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ለዚህ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፤ “ ከኤርትራ መንግስት ጋር የኢትዮጵያ መንግስት የቃላት ጦርነት ውስጥ አልገባም” ሲሉ አስተባብለዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን በመወከል “ንግግር” የሚያድርጉ ተቋማት እንዳሉ ያመለከቱት ዶ/ር ጌዲዮን፤ “እስከማውቀው ድረስ የቃላት ጦርነት ውስጥ፤ እንዲህ እና እንዲያ ወደማለት አልገባንም” ሲሉ ለጥያቄው ምላሽ ሰጥተዋል።

ጉዳዩ የሚያሳስባቸው፣ የሚመለከታቸው ዜጎች፣ የህዝብ ተወካዮች እና የቀድሞ የመንግስት ኃላፊዎች “የራሳቸውን ምልከታ” እንደሚያጋሩ ግን ሚኒስትሩ አልሸሸጉም። እነዚህ አካላት “ጆሮ ሊሰጣቸው ይገባል” ሲሉም አሳስበዋል። “በቅርቡ የእነርሱ ንግግሮችን በተመለከተ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአሁኑ ቃል አቀባይ በተቋሙ መድረክ ላይ የተናገሩት ንግግር አለ። ያ የቃላት ጦርነት የሚባል አይደለም” ሲሉም ሚኒስትሩ ገልጸዋል። 

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቃባይ አቶ ነብያት ጌታቸው ባለፈው ሳምንት በነበራቸው ሳምንታዊ መግለጫ ላይ፤ የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በቅርቡ ኢትዮጵያ በተመለከተ ስላቀረቧቸው ውንጀላዎች ተጠይቀው ነበር። “ከዚህ ቀደምም ከተወሰኑ ጎረቤት ሀገራት፣ በመሪዎች ደረጃ የተለያዩ inflammatory የሆኑ ንግግሮች፣ ውንጀላዎች፣ ክሶች፣ ዘለፋዎች የመጡበት አጋጣሚዎች ነበሩ” ሲሉ ቃል አቃባዩ በዚሁ መግለጫዎች ላይ አስታውሰዋል። 

ሆኖም ኢትዮጵያ እነዚህ በመሰሉ “እንካ ሰላንታ ሳትጠመድ”፤ “የሰከነ ዲፕሎማሲ” አካሄድን ስትከተል መቆየቷን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ “ረጅሙን ርቀት የሚያስኬደውን አማራጭ በማየት፤ አሁንም ቢሆንም ከጎረቤቶቿ ጋር ተባብሮ መስራት ላይ ያተኮረ የውጭ ግንኙነት መርህ ነው የምትከተለው። ስለዚህ በየጊዜው የሚነሱ ጉዳዮች በዚያ አግባብ ነው የሚስተናገዱት” ሲሉ አቶ ነብያት በባለፈው ሳምንት መግለጫቸው አብራርተው ነበር። 

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በዛሬው የፓርላማ ጥያቄ እና መልስ ቆይታቸው የቃል አቃባዩን ምላሽ አስተጋብተዋል። “መንግስት ፎርማሊ የሚላቸውን ነገሮች ብሏል። በፍጹም የቃላት ጦርነት የሚባል ነገር ውስጥ አልገባንም። እዚያ ውስጥ የማንገባው፤ እኛ ቀጠናዊ መረጋጋት እና ቀጠናዊ ሰላም እንዲኖር በኃላፊነት ስሜት የምንቀሳቀስ ሀገር ስለሆንን ነው። ዓለም አቀፍ መርሆዎችን፣ ህጎችን እና አሰራሮችን አክብረን የምንቀሳቀስ ሀገር ስለሆንን ነው” ብለዋል ሚኒስትሩ። 

ከኢትዮጵያ አመራሮች የሚወጣ ቃል “ትልቅ ትርጉም” እና “ክብደት” እንዳለው የጠቆሙት ዶ/ር ጌዲዮን፤ በእንደዚህ አይነት ጉዳዮች ላይ በመንግስት በኩል “በዘፈቀደ” እና “በመሰለኝ” ንግግሮች እንደማይደረጉ አመልክተዋል። “እንነጋገር ብንል ብዙ የሚያነጋግር ነገር አለ” ሲሉ የተደመጡት ሚኒስትሩ፤ ጉዳዩ መመራት ያለበት “በሚዛኑ”፣ “በጊዜው” እና “በጥንቃቄ” እንደሆነም አስረድተዋል። 

በኤርትራ በኩል “ትንኮሳ ቢኖርም፤ አንዳንዴ በሆደሰፊነት፣ አንዳንዴ ሰምቶ አንዳልሰማ፣ አንዳንዱን ደግሞ በራሱ በዲፕሎማቲክ ቻናል የሚመለሰውን ለመመለስ ጥረት እናደርጋለን” ሲሉ ዶ/ር ጌዲዮን ጉዳዩ አጽንኦት ሰጥተዋል። በኢትዮጵያ በኩል ወደፊትም ወደ ቃላት ጦርነት “የምንገባ አይመስለኝም” ሲሉ በድጋሚ ማረጋገጫ የሰጡት ሚኒስትሩ፤ “ነገር ግን ብሔራዊ ጥቅማችን፣ ሀገራዊ ጥቅማችንን አስመልክቶ ያለን አቋም አይዛነፍም” ሲሉ የኢትዮጵያ መንግስት በዚህ ረገድ ያለው አመለካከት ያልተለወጠ መሆኑን አስረድተዋል።  

“የጋራ ተጠቃሚነት እንዳለው ባለመረዳት ወይ በተለያየ ምክንያት፤ ኢትዮጵያ ስትራቴጂክ የሆኑ ሀገራዊ ጥቅም ጉዳዮች [ስታነሳ] ትኩሳታቸው የሚጨምሩ ሀገራት አሉ” ሲሉ የተደመጡት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ ሆኖም ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞቿን በተመለከተ ያላትን አቋም “አጠናክራ” እንደምትቀጥል ገልጸዋል። 

“ግድብ ስንገነባ ‘እንዴት ይገነባል’ ብለው፤ ‘እንዴት ሲደረግ፣ እኛ ሳንፈቅድ፣ እኛ እሺ ሳንል ወይም ያለ እኛ ቡራኬ’ የሚሉ ነበሩ። ያ ሳያስቆመን ግድቡን እንዳጠናቀቅነው ሁሉ፤ ሌሎች መሰል ስትራቴጂ ፋይዳ ያላቸው የሀገራዊ ጥቅም ፕሮጀክቶቻችንም፤ ቅር ቢላቸውም፣ ደስ ባይላቸውም እውን ማድረጋችን አይቀርም” ሲሉ ዶ/ር ጌዲዮን ለፓርላማ አባላቱ ተናግረዋል። 

“የጋራ ተጠቃሚነት እንዳለው ባለመረዳት ወይ በተለያየ ምክንያት፤ ኢትዮጵያ ስትራቴጂክ የሆኑ ሀገራዊ ጥቅም ጉዳዮች [ስታነሳ] ትኩሳታቸው የሚጨምሩ ሀገራት አሉ”– ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

ኢትዮጵያ ጥቅሟን የምታስከብረው “የጋራ ተጠቃሚነት መርህን ታሳቢ ባደረገ መልኩ” እና “የዓለም አቀፍ ህግ አሰራር መርሆዎችን ከግንዛቤ ባስገባ መንገድ” እንደሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ መንግስት “ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት መሆን አለባት” የሚል አቋም በጽኑ እያራመደ ይገኛል። 

በሌላ የባህር በር ዜና አሜሪካ የኢትዮጵያን የባህር በር የማግኘት ጥረት እደግፋለሁ ብላለች። ኢትዮ ኤፍ ኤም 98 ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት የአሜሪካ መንግስት ይደግፋል መባሉን የገለጸው በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋን ጠቅሶ ነው።

ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ሰላማዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ጥረት የአሜሪካ መንግስት እንደሚደግፍ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ አስታወቁ፡ ኢትዮጵያ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገት እያስመዘገበች መሆኗንም አምባሳደሩ አረጋግጠዋል።

በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ሰላም እና ፀጥታ ለማረጋገጥ አሜሪካ ከወሳኝ አጋሯ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ እንደምትሰራም ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት እንደምትሰራ በአጽንኦት መግለጻቸው ይታወሳል።

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በፈጣን ኢኮኖሚ እድገት ውስጥ ትገኛለች። ሀገሪቱ ሰፊ የህዝብ ቁጥር ያላት እና ፈጣን ኢኮኖሚ እያስመዘገበች እንደምትገኝ ያወሱት አምባሳደር ማሲንጋ፤ ይህ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገት እንደሚቀጥልም ትንበያ መኖሩን አመልክተዋል።

በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በዓለም ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ ለመገንባት ያላትን ህልም ለማሳካት የባህር በር አማራጯን ማስፋት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ በሰላማዊ እና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት የአሜሪካ መንግስት የሚደግፈው መሆኑንም አረጋግጠዋል።

አምባሳደር ማሲንጋ እንዳብራሩት፤ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ሰላም እና ፀጥታ ለማረጋገጥ አሜሪካ ከወሳኝ አጋሯ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ ትሰራለች።

ኢትዮጵያ ቀጣናው ወደ መረጋጋትና ሰላም እንዲመለስ አስተዋጽኦ እያደረገች መሆኑን አመልክተው፤ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ መስራት አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ ያላት ጠንካራ አቋም መሆኑን አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ በቀጣናው ግዙፍ ብቻ ሳትሆን አቅም እና ተጽዕኖ ያላት ሀገር ነች ያሉት አምባሳደር ማሲንጋ፤ በቀጣናው መረጋጋትና ሰላም ለማስፈን ሀገራቱ በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

Ethioreview news

A journalist

አሜሪካ ኤርትራን ”አሸባሪነትን መከላከል” በሚል የቪዛ እገዳ ጣለችባት፤ “ኢትዮጵያ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባታል” 
ሻዕቢያ ኢትዮጵያ ላይ የአየር ክልል መቆለፉ ይፋ ሆነ፤ ተግባሩ የህልውና ቀይ መስመር መሆኑ ቁጣ አስነስቷል፤ ሻዕቢያን እስከመቼ?
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 20260
Load more
Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 20260
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 20260
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 20260
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedbusinesshotarchivetips
    © Copyright 2026, All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2
    • Home Demo news