Skip to content
VOE
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ሔማን በቀለ – ታይም መፅሄት የዓመቱ ምርጥ ያለው ህልመኛ ታዳጊ ሳይንቲስት

    September 4, 2024

    በዩክሬን በኩል ወደ አውሮፓ የሚደርሰው የሩሲያ የተፈጥሮ ጋዝ  ስራው እንዲቆም ተደረገ

    January 1, 2025

    በኦሮሚያ ክልል ማን፣ ምን ፈጸመ? የኢሰመኮ ሪፖርት

    August 5, 2025

    በኦሮሚያ በሌብነት ጉዳይ አናቱ ተፈርቷል፤ በ289 ሺህ ካሬ.ሜ.መሬት ላይ ማጣራት ተጀምሯል

    December 3, 2022

    የአፋር ክልል ከ፴ ዓመታት በሁዋላ በትግራይ ክልል የተወሰደበትን ኣንድ ቀበሌ “ነጻ አ ወጣሁ” አለ

    June 7, 2021
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ከፊል የፋኖ አደረጃጀት የሰላም ድርድር እየተሳካ ነው፤ ለክረምት ዝግጅት ወደ ሱዳን ያመሩ አሉ
News

ከፊል የፋኖ አደረጃጀት የሰላም ድርድር እየተሳካ ነው፤ ለክረምት ዝግጅት ወደ ሱዳን ያመሩ አሉ

Ethioreview newsEthioreview news—June 17, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በተለያዩ አደረጃጀቶች ከሚታውቁት የፋኖ አካላት መካከል በደቡብ ወሎና ሰሜን ሸዋ የሚገኘው ኃይል በሰላም አማራጭ ድርድር ወደ መግባባቱ መድረሳቸው ተሰማ። በክረምት ጦርነትን ለመክፈት ዝግጅት እያደረጉ ካሉት ጋር ለመገናኘት ሱዳን ያመሩ መኖራቸው ታውቋል።

የኢትዮሪቪው የዜና አቀባዮች እንዳሉት ከሆነ በደቡብ ወሎ የሚንቀሳቀሰው የአማራ ፋኖ በወሎ ዕዝ ዋና አዛዥ ኮሎኔል ፋንታሁን ሙሃባ ጋር እየተደረገ ያለው ንግግር መግባባት ላይ የተደረሰበት ነው። ይህ ኃይል አሁን ላይ ደላንታ አካባቢ የተቀመጠ ሲሆን ውጊያም ሆነ ተኩስ እንደሌለ፣ ሕዝቡም ስጋቱ የቀነሰለትና ስምምነት እንዲደረግ የሚሻ ነው።

የዝግጅት ክፍላችን ተባባሪ ከአዲስ አበባ ለኮሎኔል ፋንታሁን ደውሎ ” አይመቸኝም” የሚል ምላሽ እንደሰጡት አመልክቷል። ደግሞ ሲደውል ጥሪውን አስቁመዋል። ጉዳዩን የሚከታተሉት ወገኖች ዝርዝር ጉዳይ ውስጥ መግባት ባይፈልጉም በቅርቡ ይፋ የሚሆን ጉዳይ ስለመኖሩ አስታውቀዋል።

በሰሜን ወሎ አካባቢ የሚንቀሳቀሰው የምሬ ወዳጆን ኃይል አስመልክቶ እነዚሁ ወገኖች እንዳሉት ከሆነ በቅርቡ ከእገት ጥቆማ ጋር ተያይዞ የአገር መከላከያ በወሰደው እርምጃ ላስታ የነበረውን መሰረታቸውን ማስጠበቅ አቅቷቸው የተረፈውን ኃይል በመያዝ ትግራይ ድንበር ኮረም አካባቢ ለጊዜው ማረፋቸውን ጠቅሰዋል።

More stories

ከትግራይ ከሻዕቢያ ጋር የሚዶልቱ ፣ መከላከያን የሚጋብዙ ድምጾች ይሰማሉ፤ መንግስት ዝም ብሏል

January 5, 2025

ትህነግ “የብልጽግና መንገድ እንጀምር” አለ፤ ለትግራይ ህጻናት ዕልቂት ተጠያቂው ማን ነው?

September 11, 2022

ደራርቱ የፖለቲካ መሪዎችን በእንባ ተማጸነች

March 23, 2022

6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ነጻና ፍትሃዊ ለማድረግ ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ ሁኔታ እየተሰራ ነው፡-ምርጫ ቦርድ

May 10, 2021

ምሬ ከሚመራው ኃይል ውስጥ በብዛት እጃቸውን መስጠትና መግባት የሚፈልጉ እንዳሉ የሚጠቅሱት ወገኖች ችግር እንደገጠማቸው ገልጸዋል። የአገር መከላከያ እጃቸውን የሚሰጡ የፋኖም ሆነ የሸኔ ኃይሎች መሳሪያ ይዘው ካልመጡ አይቀበላቸውም። አሰራሩን የሚያውቁት ኧዚሁ ክፍሎች እጃቸውን ከሰጡ መስማታቸውን በማለከት እንዳሉት የምሬ ፋኖ ኃይላት መሳሪያ ፈትተዋል።

ሲያብራሩም ሲያስፈልግ ካልሆነ በቀር ታጣቂዎች መሳሪያ አይይዙም። በአካባቢው ቋንቋ ” መሳሪያ ይከዘናል” በዚህም የተነሳ እጃቸውን መስጠት የሚፈልጉ የምሬ ኃይሎች ችግር ገጥሟቸዋል። ያም ሆኖ ባገኙት አጋጣሚ ሲታጠቁ ሸሽተው የሚመጡ አሉ።

ሰሜን ሸዋ የመሸገው እስክንድር ነጋን አስመልክቶ “እሱም በንግግር ላይ ነው፤ ከኮሎኔል ፋንታሁን የተለየ ነገር የለውም” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። እስክንድር ባለበት አካባቢ አሁን ላይ ምንም ጦርነት እንደሌለ የአካባቢው ነዋሪዎች ምስክር ናቸው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የጎጃም ፋኖ አመራሮች ወደ ሱዳን ማቅናታቸው ታውቋል። ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ በዱባይ የሚኖሩና ለድርጅቱ ቅርብ እንደሆኑ የሚናገሩ እንዳሉት የጉዞው ዓላማ በክረምት ለታቀደው ውጊያ ለመነጋገርና ነው።

ሱዳን ላይ የትህነግ፣ የሻዕቢያና የአማራ ፋኖ በጎጃም ወኪሎች እየመከሩ እንደሆነ በተላያዩ አካላት ሰሞኑን ሱገለጽ መሰንበቱ ይታወቃል። በትግራይ ሕዝብ ጦርነት መቃወሙና ጭራሽ የጦርነት ወሬ መስማት እንደማይፈልግ ማስታወቁ፣ በጎንደር አካባቢ ያለው የፋኖ አደረጃጀት በብዛት ወደ ሰላማዊ መንገድ መመለሱና በወልቃይት ሰፊ ህዝባዊ አደረጃጀት መፈጠሩ፣ መከላከያ ሰፊ ኃይልና ትጥቅ ማደራጀቱ አንድ ላይ ተዳምሮ የክረምት የውጊያ ዕቅዱ ላይ ስጋት ማስነሳቱን አንዳንድ ወገኖች ይናገራሉ።

በቀርቡ ልደቱ አያሌው፣ ቴድሮስ ጸጋዬና ጃዋር መሐመድ ያዘጋጁት የሰማይ ላይ ትዕይነት ላይ የተሳተፉት አካላት ” መንግስት ቢለመን፣ ለውይይትና ለድርድር ቢጋበዝ፣ ሁሉንም ያካተተ የሽግግር መንግስት እንዲያቋቁም ቢጠየቅ እምቢ ስላለ ግንባር ለመፍጠር ተዘጋጅተናል” ለማለት ዝግጅት ላይ መሆናቸውን ያስታወቁት የዜናው ሰዎች የሱዳኑ ምክክር የዚሁ ጅማሬ እንደሆነ አመልክተዋል።

በዚሁ የኢንተርኔት ሰልፍ ላይ ከተሳተፉት መካከል አንዱ የሆኑትና የሶማሌ ህዝብን ኮንግረንስን ወክለው የተሳተፉት ዶከተር ኢስማኤል ጎርሴ “ተሸውደን ነው። የሸወደን ልደቱ ነው። ከስብሰባው በሁዋላ በስልክ አነጋግሬው ሁሉንም ጉዳይ እናጋልጣለን። የሰራችሁት ሁሉ ስህተት ነው። ማጭበርበር ነው” በማለት ቅሬታቸውን ሲገልጹ አቶ ልደቱ ” ኮሚቴው አስገድዶኝ ነው ጠብ መንጃ ያነሱ ኃይሎችንና እነ ስብሃትን የጋበዝኩት” የሚል መልስ እንዳገኙ በስልክ ለኢትዮሪቪው ገልጸዋል። እሳቸው እንዳሉት የብሄር ብሄረሰቦች ክምችት እንዳለው ለማስመሰለ ታስቦ የተሰራው ስብሰብ ቀጣይ ዕቅዱ ግ ንባር መመስረት ነው። ከዶከተር ኢስማኤል ጎርሴ ጋር ያደውረገነውን ቃለ ምልልስ ሙሉውን እናቀርባለን።

በዚሁ መነሻ በሱዳን የተሰባሰቡት አካላት ግንባር ሊፈጥሩ የሚችሉበትን አግባብም ያመቻቻሉ ተብሎ የጠበቃል፤ ጥምረቱ አሁን ያፋ ባይሆንም አካሄዱ ግን ወድዚያው እንደሆነ እንቅስቃሴውን የሚከታተሉ ገልጸዋል።

በሌላ ዜና ሻዕቢያ በበላይነት እየሰራው ያለውን ይህን ጥምረት በፕሮፓጋንዳ ለማገዝ 460 ሺህ ዶላር መመደቡን የስብሰባው ተሳታፊዎች አጋልጠዋል። ካጃዋር ጋር ተጣልተው የነበሩ የኦሮሞ ልሂቃንና አብረውት ሲሰሩ የነበሩ አክቲቪስቶችን በማስማማት ፕሮፓጋንዳው ኦሮሚያ ላይ ስንጥቅ እንዲፈጥር እንዲጠናከር ዕቅድ ተያዟል።

የአቶ ታዬ ደንደአ ቃለ ምልልስ የዚሁ ኦሮሚያን የመከፋፈልና ትህነግ ያጣውን ስም ለመመለስ የሚደረግ ዘመቻ አንዱና የመጀመሪያው ምዕራፍ እንደሆነ ተመልክቷል። አቶ ታዬ ብቻ ሳይሆኑ ሌሎችም ከመሃል በማውጣት ” ይህን ሰምቻለሁ፣ ይህን በሚስጢር አድርገናል ወዘት …” በሚል መንግስትን በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ያነጣጠረ፣ መከላከያን የሚከፋፍል ዘመቻ አከታትሎ ለማቅረብ ሰፊ ዕቅድ መያዙን የዲሲው ተባባሪያችን አስታውቋል።

በግብጽ የበላይነት ሻዕቢያ የሚመራው ይህ ኃይል መዳረሻ ዕቅዱ የኢትዮጵያን መከላከያ ማፍረስ እንደሆነ፣ ይህንንም ለማሳካት ልክ በደርግ ጊዜ ” የመንግስቱ ጦር፣ የፋሽስት ጦር” ወዘተ በማለት የአገር መከላከያን ለማፍረስ የዳቦ ስም እንዳወጡት ሁሉ አሁንም በዘመናዊ አደረጃጀት የተሰራውን የኢትዮጵያ አገር መከላከያ ለመበተን ” የአብይ ጦር፣ የብልጽግና ጦር…” ወዘተ በማለት የሚሰራው ማጠልሸት እንደሆነ ፕሮፓጋንዳውን እንዲሰሩ ከተመደቡት ጋር ቅርበት ያላቸው ለዲሲው ተባባሪያችን ነግረውታል። የአገር መከላከይ ሰራዊት አባላት ሜዳ ላይ ተጥለው ለማኝ እንደተደረጉ የሚታወስ ነው።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ጎርጎራ ሄሊኮፕተር ተከስክሶ “አለቁ” የተባሉት ከፍተኛ ባለስልጣናት በምስልና ቪዲዮ ባህር ዳር ታዩ
በወንጀል የተገኘን ሃብትና ሽብርተኝነትን መርዳትን ለሚመረመሩ መርማሪዎች የተሰጠው ስልጣን እያነጋገረ ነው
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2