ስለ ኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ መናገርና መተንተንን የፖለቲካ ስትራቴጂ ያደረጉት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፉወርቂ ፕሮፌሰር አስመሮም ኢትዮጵያን በወራሪነት ከፈረጁበት ቃለ ምልልስ ጋር የተዘመደ መግለጫ ሰጡ፡፡ ኢትዮጵያን የማተራመስ አጀንዳ በመያዝ እየፈጸሙ ስላለው ተግባር ሳይተነፍሱ ራሳቸውን መላዕክ አድረገው ማቅረባቸው የሚነሳባቸውን የጤና ችግር ጉዳይ አጉልቶባቸዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፖለቲካ ጉዳዮች ምክትል ዋና ፀሐፊ አምባሳደር ኃይሌ መንቆሪዎስ ጦርነት ከተነሳ ጉዳቱ ከፍተኛ እንደሚሆን ለቢቢሲ ትግርኛ ክፍል ሲያስታውቁ ” ኤርትራ ተወረርኩኝ፤ እርዳታ እሻለሁ ካለች፣ ወረራውን ለመቀልበስ ከየትኛውም አገር ድጋፍ የመጠየቅ መብት አላት” ሲሉ ኢትዮጵያን ወራሪ አድርገው መሳላቸው ይታወሳል።
ይህን ተከትለው በብቸኛው የአገራቸው ብሄራዊ ቴሌቪዥን ሑለት ሰዓት በፈጀ መግለጫቸው በተመሳሳይ ኢትዮጵያን በወራሪነት ፈርጀዋል። በጅምላ ሲያስጨፈጭፉት ለነበረው የትግራይ ሕዝብና ፋኖ ጥብቅና ቆመዋል።
የእነ ደብረጽዮን ቡድን ከሻዕቢያ ጋር በይፋ ግንኙነት መፍጠሩን፣ ይህም አደባባይ የሚታወቅና እየተሰራበት ያለ ጉዳይ ሆኖ ሳለ ኢሳያስ ለአፍታም አላነሱትም።። አምባሳደር ኃይሌ መንቆሪዎስ ግን ኤርትራ ከፋኖና ከከፊል የትግራይ ኃይሎች ጋር ግንኙነት መፍጠሯን እንደሚያውቁ መስክረዋል።
የኤርትራ ሕዝብ ነፃ አውጪ ግንባር (ሻዕቢያ) ከፍተኛ አመራር የነበሩት አምባሳደር ኃይሌ፣ ኢትዮጵያ የባህር በር መጠየቋን ተከትሎ ሳዑዲ አረቢያና ግብጽ ጣልቃ እንደሚገቡ ተናግረው፣ “…..ኤርትራ እጇን አጣጥፋ አልተቀመጠችም። ከተለያዩ ቡድኖች ጋር ግንኙነት እየፈጠሩ እንደሆነ መረጃ አለኝ። በከፊል በትግራይ ግንኙነት እየፈጠሩ ነው፤. . . በአማራም ከፋኖዎች ጋር እንዲሁ ግንኙነት አላቸው” ሲሉ የሚያውቁትን የአደባባይ ሃቅ ይፋ አድርገዋል።
ይህ እየታወቀ ፕሬዚዳንቱ ራሳቸውን ከደሙ ንጹህ አድርገው ኢትዮጵያን ወራሪና በኤርትራ ጥቅም ላይ ያነጣጠረች አገር አድርገው ሲወነጅሉ ተደምጠዋል።
የሙግት ጥያቄም ሆነ ማብራሪያ እንዲያቀርቡ ጥያቄ የማይቀርብላቸው ኢሳያስ አፉወርቂ፣ ዘወትር ምክንያት ፈልገው ንግግር ካደረጉ ከሀገራቸው ጉዳይ ይልቅ ስለ ሰው ሀገር ጉዳዮች ሰፊ ጊዜ ወስደው በመናገርና በመተንተን የሚታወቁት የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ፣ ትላንት ምሽት ኢትዮጵያን ወራሪ አድርገው ሲስሉ ለመከላከል መዘጋጀታቸውንም በማስታወስ ነው።
አገራቸውንና ብሔራዊ ጥቅሟን አሳልፈው በመስጠት በኢትዮጵያ ባንዲራ ታጅለው ኢትዮጵያን የሚደበድቡና እንድትፈርስ ሌት ተቀን የሚሰሩ ሚዲያዎችም የሚያውቁትን ሃቅ ትተው “ኢሳያስ እንዲህ አሉ” በሚል መግለጫቸውን እያራገቡላቸው ነው።
በቅርቡ “ነጻነት” በሚል በሚከበረው የኤርትራ በዓል ላይ ፕሬዝዳንቱ ለገራቸው ሕዝብ ስለራሳቸው ጉዳይ ምንም ሳይሉ፣ ስለ ኢትዮጵያ እና ቀጠናው ጉዳይ ትንታኔ ሲሰጡ እንደነበር አይዘነጋም። አብዛኞችን የሚያስገርመው ግን ከመንግስት ወገን ለሳቸውም ሆነ በእሳቸው ዙሪያ ያሉ ለሚሰነዝሩት ክስ “የዝምታ ፖለቲካ” መምረጡ ነው፤
ትላንት በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ደግሞ ንዴትን በቀላቀለ ሁኔታ በማይመጥኑ ቃላት የኢትዮጵያን ስም ሲያነሱና ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የባህር በር ጥያቄ ማንሳታቸውን “የልጅ ጨዋታ” በሚል ሲያቃልሉ ተሰምተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የወደ ጉዳይ ሲያነሱላቸው በጅቡቲ እንጀራ ጣልቃ መግባት እንደማይፈልጉ መናገራቸውን አብይ አHመድን ” ልጅ” ባሉበት አንድበታቸው ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ያነሳችውን የባህር በር ጥያቄ ሲያጣጥሉት ነው ያመሹት ኢሳያስ ፣ጥያቄውን ” የህጻን ጨዋታ ነው፣ ማሳሳቻ ነው፣ የረከሰ ውሸት ነው ፣ የውስጥ ጉዳይ ማዳፈኛ ነው ፣ ጀርባው የተባበሩት አረብ ኤሜራት የወደብ ማስፋፋት አጀንዳ ነው ” በሚል ሲቀባቡ ተደምጠዋል።
ይህንኑ ዲስኩር “ኢትዮጵያ የባህር በር አያስፈልጋትም የሚሉ ኢትዮጵያዊያን የተባሉ ‘ኢሳያስ ሃቁን አፈረጡ’ ” በሚል ሲያራግቡት ” አንዳንድ የትግራይ አክቲቪስቶች ደግሞ ከበሮ ጭምር እየመቱ አዳንቀዋል። እነዚህ ክፍሎች ኢሳያስን “ጄኖሳይደር” በማለት ሲከሱና በትግራይ ላላቁት አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ተጠያቂ ሲያደርጉ የነበሩ መሆናቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የባህር በርን ጉዳይ አለም አቀፍ አጀንዳ ማድረጓን ተከትሎ በርካታ ሀገራት ለጥያቄዋ ድጋፍ ማድረጋቸው በተለያዩ ታዋቂ ሚዲያዎች መዘገቡ ይታወሳል። ይህ የዲፕሎማሲ አካሄድ ውጤታማ እንደሆነ የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዘወትር መግለጫው ላይ እግረ መነገዱን ጠቆም የሚያደርገው ጉዳይ ፕሬዝዳንት ኢሳያስን እንዳላስደሰተም። በርካቶች እንደሚሉት ስጋት ላይ ጥሏቸዋል።
በዚሁ መነሻ ” ፈረንሳይ ከኛ ጋር ናት፣ አሜሪካ ፣ ኤሚሬት፣ አውሮፓ ህብረት ከኛ ጎን ናቸው ማለት ጭንቅ እንጂ የድል መንገድ አይደለም ” በማለት ለማጣጣል የሞከሩት ኢሳያስ፣ ነገሩን አዙረው ” ኢትዮጵያውያን የውስጥ ችግራችሁን ፍቱ ” ሲሉ ተደምጠዋል። እሳቸው በትግራይ፣ በኦጋዴን አማራና ኦሮሞ ታጣቂዎችን በማስለጠን፣ በውክልና በሚያገኙት እርዳታ እየስታጠቁ ኢትዮጵያን የማተራመስ የማይቆም አጀንዳቸውን ለምን እነደማያቆሙ የሚጠይቃቸው የለም።
በማተራመስ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሰነሰለታቸውንና ኤምባሲያቸውን ተጠቅመው በዶላር አጠባ፣ በኮንትሮባንድና ዝርፊያ የተሰማራው መንግስታቸው ከማጅራት መቺነት ወጥቶ መቼ እንደመንግስት እንደሚያስብ ፍንጭ ሰጥተው አያውቁም።
በኢትዮጵያ በኩል ሀገራቸው ላይ የጦርነት ስጋትና ዛቻ እንዳለ በማመላከትም ” እራሳችንን እንጠብቃለን ” ሲሉ ከአምባሳደርሩ ጋር የተመሳሳለ የፍረጃ ክስ ለሕዝባቸው የገለጹት ኢሳያስ፣ ኢትዮጵያ ለባሕር ስትል ኤርትራንም ሆነ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር የመውጋት አንዳችም ፍላጎት እንደሌላት በተደጋጋሚ ማሳወቋን ጆሮ ዳባ ብለዋል።
ኢትዮጵያ አንድም ጊዜ የአሰብን ስም አንስታ እንደማታውቅ፣ የባህር በር ጉዳይ የህልውናዋ ጉዳይ መሆኑን በመግለጽ በዓለም የንግድ ህጎች ሁሉ በሰላማዊ መንገድ ይህንኑ ፋልጎቷን ለማሳካት እንደምጸራ ይፋ ከማድረጓ አንጻር በመንግስት ደረጃ የተመዘገበ የጦርነት አዋጅ ይህ እስከታተመ ድረስ አልተደመጠም። ይልቁኑም ኤርትራ ተቃዋሚዎችን በማደራጀት፣ የኢትዮጵያን ክልል ዘለቃ በመግባት ሰብአዊ መብት እየጣሰች በመሆኑ ዓለም “አንድ ይበል” የሚል ደብዳቤ ለተባበሩት መንግስታት መላኳ ነው በይፋ የሚታወቀው።
አምብሳደር ኃይሌም ይህ ደብዳቤ እሳቸው ለሚሰሩበት ድርጅት መላኩን እያወቁ በዝምታ አልፈውታል። ይልቁኑም “ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ሊተማመነባቸው የሚችሉ የአገር ውስጥ ኃይሎች ተከፋፍለዋል” በሚል ሻዕቢያ በጣልቃ ገብነት እየሰራ ያለውን ሴራ አኘው አሳይተዋል። አክለውም “ኢሳይያስ በህወሓት እና በአማራ አማካኝነት በሁሉም በኩል ዐቢይን ለመክበብ እየሞከረ አይደለም ማለት አይቻልም” ሲል ራሳቸውን ዳር የቆሙ በማስመሰል በትክክል መሬት ላይ የሚሞከረውን መስክረዋል።
ይህን ሁሉ እያደረጉና በራሳቸው ሰዎች ሳይቀር እየተመሰከረባቸው ያሉት ፕሬዜዳንት ኢሳያስ “ኢትዮጵያ ተመድ ሄዳ ከሳናለች ክሱ አስነዋሪና አሳፋሪ ነው ” ሲሉ ተደምጠዋል። ኢሳያስ ጦራቸው የኢትዮጵያን አስር ኪሎ ሜትር ርቆ መግባቱን ሴንቸሪ ያወጣው ሪፖርት ሰሞኑን ማጋለጡ አይዘነጋም።
ስለ ፕሪቶሪያ ስምምነትም ሲናገሩ የትግራይን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሲፈረም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት እንዳሻከረች በይፋ የሚታወቅ መሆኑበመሸምጠጥ ነው።
” ኤርትራን ከመክሰሳችሁ በፊት የፕሪቶሪያን ውል ተግብሩ ፤ የውስጥ ችግራችሁን መፍታት አስቀድሙ ፤ ለምን ስምምነቱ በቅን ልቦና አልተተገበርም ለምን ፋኖ ላይ ጦርነት ከፈታችሁ ” የሚል መጨበጫ የሌለው የወቀሳ አስተያየት ሰንዝረዋል።
ፕሬዚዳንቱ የፕሪቶሪያው ስምምነት ሲፈረም ” ተኮላሊፍና” ወይም “ከሸፈብን” ሲሉ ትህነግን ከምድር ላይ የማጥፋት ዕቅዳቸው በመሰናከሉ በይፋ ከመንግስት ጋር ያላቸውን ትብብር ማቆማቸውን ይፋ ማስታወቃቸው የቅርብ ጊዜ ጉዳይ እንደሆነ ዘንግተዋል።
ሌላው ኢሳያስ ለኤርትራ ሕዝብ በይፋ የተናገሩትና ሰሚዎችን ያሳቀው ጉዳይ ቢኖር የዴሞክራሲ ፍሬዎችን አንስተው ምክር መለገሳቸው ነው። ምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሚዲያ፣ የዕምነት ነጻነት ፣ የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት፣ በጀት፣ ህግ አውጪና ተርጓሚ፣ ኢንተርኔት፣ የመናገርና የመሰብሰብ ነጻነት ወዘተ የማይታወቅባትን ኤርትራ የሚመሩት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ” በኢትዮጵያ መታየት ጀምሮ የነበረው የለውጥ ተስፋ ጨልሟል ፤ የፖለቲካ ፓርቲ ብሎ የለም ” የሚል ንግግር አሰምተዋል። ይህን ሲናገሩ ጠያቂዎች ሆነው የተመደቡት ሁለት አጃቢዎቻቸው የሰውነት እንቅስቃሴ እንኳን አይታይባቸውም።
ያለአንዳች ተቀናቃኝ ከ30 ዓመት በላይ ኤርትራን እየገዙ ያሉት ኢሳያስ አፈወርቂ እንደ ሁል ጊዜው የትላንት ምሽቱ ቃለ ምልልሳቸው ስለ ሀገራቸው ጉዳይ ሳይሆን ስለ ኢትዮጵያ እንዲሁም ስለ ሌሎች ሀገራት ጉዳይ በመተንተን አሳልፈዋል።
ከዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ተነሳሽነት በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ሰላም እንዲወርድ ከተደረገ በኃላ የትግራይን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እስኪፈረም ድረስ ኢትዮጵያን እና አስተዳደሯን ሲያሞካሹ እንደቆዩ በአደባባይ የሚታወቅ ሀቅ ነው። ዕርቅ በተፈጸመ ማግስት ከአራት መቶ ሺህ በላይ ኤርትራን ለቀው በድንበር ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውም አይዘነጋም።
በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ አገሩን ጥሎ የሚፈልሰው የኤርትራን ሕዝብ እድሜ ጾታ ሳይለዩ በየአገሩ በስደት የሚኖሩት፣ አብዛኞች በባህር ላይ የሚያልቁትና በበረሃ የሚሞቱት የኢሳያስን አስተዳደር በመጥላት መሆኑ እየታወቀ ስለ ኢትዮጵያ ለውጥ ማንሳታቸው ጤናቸውን ለሚጠራጠሩ ማረጋገጫ ሆኗል።
“በኤርትራ ሰዓት ቆሟል” በሚል የወጡ ዶክመንታሪ ፊልሞች እንደሚያሳዩት በአስመራ የኤቲኤም የመክፈያ ስርዓት በቅ ነው። ኢንተርኔት በስለፍና በቀጠሮ ነው። ቲክቶክና የማህበራዊ ሚዲያ ምስሎች ማውረድና መጫን አይታሰብም። ሰዎች የሚኖሩት በገደብ ነው። እንደፈለጉ መውጣትና መግባት አይቻልም። ከተማዋ ቀለም እንኳን በአግባቡ አልተቀባችም። የመንገድ እድሳትና አዳዲስ ነገሮች የሉባትም። በተለይም ወታቶች ብዙም አይታዩባትም። እንዲህ ያለውን አገር ከጎረቤቶቻቸው ጋር በመሆን ከማሳደግ ይልቅ በውክልና ከጎረቤቶቻቸው ጋር ሁሉ የተዋጉት ኢሳያስ፣ ፕሮፌሰርሩ እንዳሉት ኢትዮጵያን ከውስጥ ባንዶች ጋር ሆነው ለማፍረስ እየሰሩ ነው። ይህንን የተረዱ ” ኢሳያስ እያሉ ኢትዮጵያ ሰላም አታገኝም” በሚል ደምድመዋል።



