በአሁኑ ሰዓት ወደ ቀድሞ የማህበራዊ ሚዲያ አክቲቪዝም የተመለሰው ጃዋር መሐመድ ከኦፌኮ መሰናበቱን ፓርቲውን የለቀቁ ለዝግጅት ክፍላችን አስታወቁ። ፓርቲው ውሳኔውን በይፋ ማስታወቅ አልፈለገም ተብሏል።
ቀደም ሲል የኦሮሞ ነጻነት ግንባርን መቀል ሞክሮ ተቀባይነት ያላገኘው ጃዋር አቶበቅለ ገረባን በመያዝ ኦፌኮን መቀላቀሉ አይዘነጋም። ፓርቲውን እንድተቀላቀለ ወዲያው ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር የሆነ ጃዋር በፋይናንስ ድጋፍ ማድረጉን ዜናውን ያቀበሉን አመልክተዋል። ከኦህዴድ ሰዎች ጋር በመሆን በትግሉ ወቅት ያገኘውን ተቀባይነት ተጠቅሞ ሰፊ ተከታይ በማፍራቱ ጃዋር ኦፌኮን ሲቀላቀል በአመራሮች ዘንዳ የደስታ ስሜት ቢፈጥርም ቅር የተሰኙ ግን ነበሩ።
ከሌሎች ጋር አብሮ በመስራትና አክራሪነትን በመቃወም የሚታወቀውን ኦፌኮን፣ እንዲሁም አመራሮቹን ከሕዝብ እንደሚነጥል አስቀድመው ስጋት እንደነበራቸው የጠቆሙት እነዚሁ ወገኖች እንዳሉት ጃዋር ከፓርቲው ከተባረረ ቆይቷል። ወይም ራሱን አሰናብቷል።
ከእስር ከተፈታ ጀምሮ ፓርቲው ጽህፈት ቤት ተገኝቶ እንደማያውቅ፣ እንደማይሰበሰብና በጋር ማናቸውንም ጉዳዮች እንደማይወስን መረርጃውን ካጋሩን ክፍሎች ለመረዳት ተችሏል።
በቅርቡ ኦፌኮን በብዛት ለቀው ወደ ብልጽግና ካቀኑት ውስጥ የዞንና ከዛም በላይ አመራር የሆኑ ድርጅታቸውን ለቀው የወጡበትን ምክኛት ሲጠየቁ ” ብዙ የለፋንበትን፣ የታሰርንበትንንና ዋጋ የከፍለንበት ፓርቲ ውስጥ ትናንት መጥቶ ባይተዋር አደረገን” የሚል ምላሽ መስጠታቸውን ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል።
ድርጅቱን የለቀቁት እንዚህ ወገኖች “ጃዋር እኮ አሁን ተባሯል። ካሁን በሁዋላም ወደ አገር ቤት አይመጣም። በሚቀጥለው ምርጫ እሱና አቶ በቀለ በሌላ ይተካሉ” የሚል መልስ እንደተሳጣቸው ገልጸዋል።አቶ በቀለ ገርባ ከፓርቲው ኃላፊነታቸው በገዛ ፈቃዳቸው መልቀቃቸውን በይፋ ማስታወቃቸው አይዘነጋም። አቶ በቀለ በግላቸው ያመኑበትን አቋም ይዘው እንደሚሰሩ ጠቀሰው ነበር ፓርቲውን የተሰናበቱት። እንደ እሳቸው ገለጻና አሳባቸውን የተረዱ እንዳሉት እሳቸው ከአገር ውጭ ሆነው በሚያራምዱት ማናቸውም ጉዳይ ፓርቲያቸው እንዳይጠየቅ ነው የተከላከሉት።
በቅርቡ ጃዋር አመጽ በማደራጀትና አመጽን የሚቀሰቅሱ መረጃዎችን በማሰራጨት ስራ ላይ መጠመዱን ተከትሎ ለፕሮፌስረ መራራ ጥያቄ አቅርበን “በይፋ ምን እያደርገ እንደሆነ አላየሁም” የሚል ላሽ ሰጥተውን ነበር።
የጃዋርን ከኦፌኮ መሰናበት አስመልክቶ የጠየቅናቸው አንድ የፓርቲው አመራር “ድሮስ ከእኛ ጋር እየሰራ ነበር እንዴ” ሲሉ ጥያቄን በጥያቄ በመመለስ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል። ይሁን እንጂ መረጃውን ከሰሙ በሁዋላ ለማስተባበል አልሞከሩም።
ጃዋር አሁን ላይ ዳግም የራሱም ሚዲያዎች ለማራባት እየሰራ መሆኑ ይታወቃል፤ ከእነ አቶ ልደቱ ጋር ለመለይትም በቋፍ ላይ መሆኑ ተሰምቷል። የወለጋ ልጆች የቀደመርውን ተጽዕኖ ፈጣሪነቱን ስለነጠቁትና በሻዕቢያ በኩል እንደ ፕሮፌሰር ሕዝቅኤል የሚታመን አለመሆኑ፣ ሚዲያም እንደፈለገው የማግኘት ችግር ስላጋጠመው የባይተዋርነት ችግር ውስጥ እንዳለ እየተጠቆመ ነው። እነዚህ ወገኖች ጃዋር “አልጸጸትም” የሚለውን መጽሃፍ ሲያወጣ በርብርብ ክፉኛ ይተቹት እንደነበር አይዘነጋም። ይህም የሆነው አዲስ አበባ ሲገባ የያዘውን ሃብት በሙሉ የብቻው በማድረግ እነሱን ስላገለላቸው መሆኑ በወቅቱ መዘገቡ አይዘነጋም።

