Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  Events  የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም? 
EventsNews

የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም? 

Ethioreview newsEthioreview news—August 6, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የሃይማኖትና የመንግሥትን መጣመር የሚደግፉም ሆነ ጥምረታቸውን በጽኑ የሚቃወሙ ጠንካራ የመከራከሪያ ነጥቦችን ያነሳሉ። ይህ ዘመናትን ያስቆጠረ ክርክር ባለንበትም ዘመን ሠለጠነ ከሚባለው ዓለም እስከ አገራችን የመወያያና የመከራከሪያ አጀንዳ ሆኖ ቆይቷል።  

ይህ አጭር ጽሑፍ በሁለቱ ጽንፎች መካከል የሚካሄደውን ክርክር ለማቅረብ ወይም ለአንዱ ለመወገን ያሰበ ሳይሆን የሁለቱ ጥምረት ምን ውጤት አመጣ? ታሪክስ ምን ያስተምረናል? የሚለውን በጣም በጥቂቱ ለማንሳት ነው። ለማሳያነትም የክርስትና እምነትና መጽሐፍ ቅዱስ የምንጠቀም ሲሆን ይህ ማለት ግን ስለ ሌሎች ሃይማኖቶች ታሪክ ምንም አይልም በሚል እንዳይወሰድ አደራ ለማለት እንወዳለን።

የሦስቱ ታላላቅ ሃይማኖቶች አባት የሚባለው አብርሃም ይኖርበት ከነበረው ባቢሎን (የከለዳውያን ዑር) ወይም ያሁኗ ኢራቅ አካባቢ እግዚአብሔር ውጣ ብሎ ሲጠራው ታዘዘና ወጣ። ከዚያም በፊት እግዚአብሔር ዓላማና ፈቃዱ የሚያሳይበት ሰው ወይም ሕዝብ ሲፈልግ እንደነበር እናነባለን። ጣዖት አምልኮ እና ጸረ እግዚአብሔር አስተሳሰብ እየገነነ በመጣባት በዚያን ጊዜዋ ዓለም የክፋትን ሃሳብና አሠራር የሚቃወም ወይም የሚገዳደር ሕዝብ ወይም ግለሰብ አምላክ መፈለጉ እንደ ስህተት ሊታይ አይገባም።  

ለአብርሃም የተሰጠው ተስፋ ትበለጽጋለህ እና በምድር ደስ ብሎህ ትኖራለህ ሳይሆን ታላቅ ሕዝብ ትሆናለህ፣ የኔንም ስም ታስጠራለህ፣ እኔም ካንተ ጋር እሆናለሁ የሚል ነበር። የታላቅነቱ መጠንም በባሕር አሸዋ ወይም በሰማይ ከዋክብት የሚተመን እንደሆነ የተሰጠው ተስፋ ላይ ተነግሮታል። ይህ ሃይማኖትን መሠረት ያደረገ አገረ መንግሥት ምሥረታ ጥንስሱን የምናይበት ነው። 

More stories

“ጉዳዩ መሬት የመያዝ እንጅ የሀይማኖት አይመስልም” – “ታቦቱ ከቦታው አልነሳ አለን”

April 9, 2022

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ” ህዝቡ ለአማራዊ ማንቱ ዘብ ሆኖ ይቆማል” ሲል ለትህነግ ምላሽ ሰጠ

April 20, 2025

የሶማሌ ክልል – ያለፈውን ስቃይና ሰቆቃ አንረሳም፤አይረሳም

November 1, 2021

አፍሪካ ሕብረትና ኢጋድ ሸኔንና ትህነግን በይፋ በአሸባሪነት እንዲፈርጁ ዝግጅት እየተደረገ ነው

February 17, 2022

ነገሩን አፍጥነነው የአብርሃም ዘሮች በግብጽ ምድር እጅግ በሚያስመርርና ተስፋ በሚያስቆርጥ ባርነት ውስጥ እያሳለፉ መቆየታቸውን ስናይ ለአብርሃም የተገባው ቃል የት ገባ የሚያስብል ይሆናል። ሆኖም እግዚአብሔር በብርቱ ክንድ ከባርነት አውጥቶ ሕዝብ ሊያደርጋቸው፣ ሀገር መሥርቶ ሊያስተዳድራቸው ነበር ዓላማው። “የካህናት መንግሥት” ትሆኑልኛላችሁ ነበር እርሱ ያላቸው። በሌላ አነጋገር ቲዎክራሲ theocracy በምድር ላይ እየተመሠረተ ነበር (theo = god; cracy = “rule” or “government”)። 

እስራኤላውያን የባርነት ዘመናቸው አልፎ በከንዓን ምድር መኖር ሲጀምሩ የቲዎክራሲ ሃሳብ መዝለቅ አቃተው። ሕዝቡም ዓመጸኛና ጸረ እግዚአብሔር ሆነ። የእግዚአብሔርን የበላይ መሪነት እምቢ ብለው እንደ አሕዛብ ንጉሥ እንዲነግሥልን ነው የምንፈልገው አሉ። ለበርካታ ዓመታት በቲዎክራሲ ሥር ሆነው በእግዚአብሔር ሉዓላዊ መሪነትና እንደ ኢያሱ፣ ጌዲዮን፣ ሳምሶን ወዘተ ባሉ መስፍንነት ወይም ፈራጅነት ሲመሩ ቆይተው በሳሙኤል ዘመን ዘመነ-ቲዎክራሲ አበቃ። ሳዖል የመጀመሪያው ንጉሥ ሆነ፣ ዳዊት ቀጠለ፣ ሰሎሞን ሠለሰ። 

በዘመነ-ቲዎክራሲ ሃይማኖት አንድ ነው፣ ዓላማው ሌሎችን በግድ ወደ አምልኮ እግዚአብሔር ማምጣት አይደለም። ነገር ግን የብርሃን ማማ መሆን፤ በሞራል ልዕልና ደምቆና ከፍ ብሎ መታየት፤ ለሌሎች አርአያ መሆን፤ በሥነምግባር የታነጸና ለሌሎች ምሳሌ የሚሆን ሕዝብ ማሰባሰብ ነው።

ጦር መስበቅና ወታደር ማደራጀት ዋናው ዓላማው አይደለም። በርግጥ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተካሄዱ ጦርነቶች ተዘግበዋል፤ የተካሄዱበት ዓላማና በበቂ ምክንያትና አሳማኝ ማስረጃ አለ፤ የዚህን ጽሑፍ ሃሳብ በማስረዘም ወደ ሌላ አቅጣጫ ስለሚወስደው በሌላ ትንታኔ የሚታይ ይሆናል። 

የቲዎክራሲ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ሕዝብን በግብር ማስጨነቅ አይደለም። ይልቁንም ከገቢ ከአሥር አንድ ወይም ዐሥራት በመመለስ በእምነትና በሰላም መተዳደር ነው። ወታደር እና መከላከያ መሥርቶ እሱን መቀለቢያ ብር አምጣ እያሉ ሕዝብን ማስገደድ አይደለም። ጦርነት የሚመራው በካህናት ነው፤ የሚከተሏቸው ተዋጊዎችም መለከት የሚነፉ መዘምራን ናቸው። ይህ ዓይነቱ ሠራዊት እንደ ኢያሪኮ በማይበገር ቅጥር የተቀጠሩ ከተሞችን በጥሩምባ የሚያፈርስ ነው። 

እስራኤል ቲዎክራሲን አልፈልግም ብሎ በንጉሥዊ (monarchical) አገዛዝ መገዛት ከጀመረበት ከንጉሥ ሳዖል ጀምሮ በርካታ ነገሥታት የተፈራረቁ ሲሆን በመጨረሻም “ደሙ በእኛና በልጆቻችን ላይ ይሁን” ብለው ክርስቶስን ከሰቀሉ በኋላ በ70ዓም የሮም ሠራዊት በጀኔራል ታይተስ በመመራት ኢየሩሳሌምን ሲያወድማትና ቤተ መቅደሱን ሲያፈርስ ሁሉም ነገር አከተመ። ከመሳፍንት የቲዎክራሲ አስተዳደር በኋላ ለእግዚአብሔር የተለየ ሕዝብ ሆኖ የቆየው እስራኤል ያንንም አጣ። ደማዊ የአብርሃም ልጅነት አክትሞ አሕዛብ በሙሉ የእግዚአብሔር ልጅ ተባሉ።

ከዚህ በኋላ በአውሮጳ ክርስትናን መሠረት ያደረገ መንግሥታዊ ሃይማኖት በሦስተኛ ክፍለ ዘመን ላይ ማቆጥቆጥ ጀመረ። ጣዖት እምላኪ የነበረው ታላቁ ንጉሥ ቁስጥንጢኖስ በሰማይ መስቀል አይቶ ጦርነት በማሸነፉ ክርስትናን በተቀበለበት ወቅት ቤተ ክርስቲያን ቤተ መንግሥት ጉያ ሥር ገባች። በውጤቱም ምዕራብ አውሮጳን በበላይነት የሚገዛ የሮም ካቶሊክ ጳጳሳዊ አሠራር የሁሉ የበላይ ሆነ። “ካቶሊክ ማለት ዩኒቨርሳል” ነው በሚለው ትርጉም ቤተ ክርስቲያን ሉዓላዊ ሆነች፤ ንጉሥዊ አገዛዝን ተቆጣጠረች፤ ንጉሥ አንጋሽና አውራጅ ሆነች።

“የጨለማው ዘመን” ተብሎ በታሪክ በሚያወሳው ዘመን የሮም ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሳትፈቅድ ንጉሥ መሆን የማይቻልበት ደረጃ ላይ ተደረሰ። ከዚያ አልፎ የቤክርስቲያኗን አስተምህሮ የሚቃወሙ ሁሉ መናፍቅ እየተባሉ ተሰደዱ፣ ተሰቃዩ፣ ለአራዊት ተሰጡ፣ ተቃጠሉ፣ ተገደሉ። በዚያ አስከፊ ዘመን በትንሹ 50 ሚሊዮን ተጨፍጭፈዋል።  

በዘመኑ ቤተ ክርስቲያኗ የነበራትን የሥልጣን ልዕልና የሚያሳይ በርካታ የታሪክ ማስረጃ አለ። ለአብነትም ያህል በ11ኛው ክፍለዘመን በሮም ካቶሊክ ርዕሳነ ሊቀጳጳስ (ፖፕ) ግሪጎሪ 7ኛ እና በጀርመኑ አጼ ሔንሪ 4ኛ መካከል የተፈጠረውን ውዝግብ መመልከቱ በቂ ፍንጭ ይሰጣል።

በ1056 ዓ.ም. የስድስት ዓመት ልጅ እያለ የጀርመን ንጉሥ የሆነው ሔንሪ 4ኛ፣ በ1084 ዓ.ም. አጼ ሆኖ ማስተዳደር ሲጀምር፣ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጳጳሳትን የመሾምና የመሻር ሥልጣን የእርሱ እንደሆነ ገለጸ። ይህ አካሄድ በወቅቱ “የግሪጎሪ ተሃድሶ” በሚል የታወቀውንና 27 ነጥቦችን የያዘ “Dictatus papae” የተሰኘ መመሪያ አውጥተው የነበሩትን የሮሙ ሊቀጳጳስ ግሪጎሪ 7ኛን አላስደሰተም። በመመሪያው ውስጥ ጳጳሳትን የመሾምና የማውረድ፣ ነገሥታትን ከሥልጣን የማስወገድ የቤተ ክርስቲያኗ እንደሆነ በግልጽ የተቀመጠ ሲሆን፣ ከእነዚህ ሌላ በርዕሳነ ሊቀ ጳጳሱ ላይ ማንም ፍርድ ማስተላለፍ አይችልም የሚል ነጥብም ይገኝበታል።

አራተኛው ሔንሪ ግን እነዚህን መመሪያዎች በመቃወም የጳጳሱን ሥልጣን በመጋፋቱ፣ ግሪጎሪ 7ኛ ሔንሪን አወገዙት (excommunicate አደረጉት)። ከዚህም በላይ፣ በእርሱ ሥር የነበሩት ዜጎች ከሔንሪ ነጻ እንደወጡና ለእርሱ መታዘዝ ወይም ግብር መክፈል እንደሌለባቸው ግሪጎሪ 7ኛ አወጁ።

ይህ ሁኔታ ያስፈራው ሔንሪ፣ ዓመጽ ይነሳብኛል በሚል ስጋት፣ ይቅርታ ለመጠየቅ በከባድ የአውሮጳ ክረምት ለሦስት ቀናት ተጉዞ ግሪጎሪ 7ኛ ይገኙበት ወደነበረበት ካኖሳ የተባለች የሰሜን ጣሊያን ከተማ ደረሰ። ሊቀጳጳሱም ሊያዋርዱትና የበላይነታቸውን ሊያሳዩት በመፈለግ እንደደረሰ ወዲያውኑ አልተቀበሉትም። ይልቁንም ሔንሪን በባዶ እግሩ በረዶ ላይ ውጪ እንዲቆይ ካደረጉ በኋላ፣ መጨረሻ ተፈቅዶለት ሲገባ በግምባሩ ተደፍቶ እግራቸውን ስሞ ይቅርታ እንዳስጠየቁት ታሪክ ያወሳልናል።

ይህ የጳጳሳዊ ሥልጣን ለረጅም ጊዜ በልዕልና ቢቀጥልም፣ በ1798 ዓ.ም. ናፖሊዮን ቦናፓርት የሮም ሊቀጳጳስን ንጉሥ የመሾምና የመሻር ሥልጣን በመቃወም ራሱን አጼ አድርጎ ዘውድ ደፋ። ከዚህም በላይ፣ ጄኔራል በርቲየርን በመላክ በወቅቱ ሥልጣን ላይ የነበሩትን ጳጳስ ፓየስ 6ኛን ከሥልጣን በመፈንቀል ወደ ፈረንሳይ በግዞት ላካቸው፤ እርሳቸውም ከ18 ወራት በኋላ በግዞት እያሉ አረፉ። በዚህ መልኩ በአውሮጳ ላይ ለዘመናት ሰፍኖ የነበረው የቤተ ክህነትና የቤተ መንግሥት ጋብቻ ተጠናቀቀ።

ይህንን ፍቺ ተከትሎ በአውሮጳ የተከሰተው ጸረ ሃይማኖት አመለካከት እስካለንበት ዘመን የዘለቀ በርካታ አስተምህሮና ርዕዮተ ዓለም ፈጠረ። ጸረ እግዚአብሔር የሆነው ማርክሳዊ የኮሙኒስት ርዕዮት (የኮሙኒስት ማኒፌስቶ በ1840ዎቹ ነው የወጣው)፣ ሂውማኒዝም የተሰኘውና ሰውን ትናንሽ አምላክ የሚያደርገው አስተሳሰብ በ1840ዎቹ በጀመርን በልዩ ሁኔታ ሥሩን ሰደደ፤ ሌሎችም ሃይማኖትን (በተለይ ክርስትናን) ጠል የሆኑ አስተሳሰቦች የፈሉበት ዘመን ሆነ።  

ናፖሊዮን ቦናፓርት

ለእነዚህ ሁሉ መነሳት ትልቁን ሚና የተጫወተው በ1780ዎቹ መጨረሻ ላይ የተከሰተው የፈረንሳይ አቢዮት ነው። በጨለማው ዘመን ሃይማኖት በመንግሥት ላይ በነበረው ፍጹማዊ የበላይነት የተንገፈገፈው ሕዝብ፤ በዋልታ ረገጥ እሳቤ እጅግ ጸያፍ ተግባራትን ያቀነቀነውንና ሰዶማዊነትን ጨምሮ እስካሁን ድረስ ለምናየው የሞራል ልሽቀት ጥሩ በር ከፋች የሆነውን ጸረ እግዚአብሔር አቢዮት በፈረንሳይ አካሄደ። በፈረንሳይ አቢዮት ወቅት ብልግና መልካም ስነ ምግባር ሆነ፤ ርኩሰት ጽድቅ ተባለ፤ ሃይማኖት እጅግ ተጠላ፤ መንግሥት ዓለማዊ መሆን አለበት የሚለው ጽኑ እምነት ጥሩ መሠረት አገኘ።

የቤተ ክህነትና የቤተ መንግሥት ጥምረት ለሺህ ዓመታት በአውሮጳ ሲዘልቅ የሃይማኖት መሪዎች ፍጹማዊ ሥልጣን በመቆናጠጥ ብዙ ብልሽቶች አስከትለዋል። የሥልጣን ገደብ የለሽነትና በሕዝብ ላይ ያለ ውክልና የሚደርሰው ግፍ እንደ ፈረንሳይ አቢዮት ዓይነቱን ነውረኛ ክስተት አዋልዷል። የዚያኑ ያህል አገራት በቲዎክራሲ የሚመሩ ይመስል ከአንድ ሃይማኖት ሌላ ኢአማኒ ከመሆን ጀምሮ ሌሎች ሃይማኖቶችን የሚከተሉ ህዳጣኖች ተደምስሰዋል። ከገዢው ሃይማኖት ሌላ ማንም የፈለገውን እንዲያምን ወይም እንዳያምን ፈቃድ ስለማይሰጠው የሰዎች ኅሊና ተረግጧል።

ሃይማኖት በቤተመንግሥት ሲታገዝ ጨቋኝ ብቻ ሳይሆን ገዳይም ይሆናል። መጽሐፍ ቅዱስም ቢሆን ሰው ወዶና ፈቅዶ እንጂ በግድ እግዚአብሔርን ማምለክ ይገባል አይልም። አስገዳጅ ኃይል አምላካዊ ሳይሆን ሰይጣናዊ ነው። በአገራችንም ቢሆን ይህ በመጠኑ የታየ ጉዳይ ነው።

አጼ ቴዎድሮስ ትልቁ ጸባቸው ከቤተክህነት ጋር ነበር። “ማርቆስ አባቴ እስክንድርያ እናቴ” በማለት ከአንድ ሺህ ዓመታት በላይ ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላት ግብፅ ፓትሪያርክ (ሰላይ ሊባሉ ይችላሉ) ታስመጣ የነበረችው ቤተ ክርስቲያን በግብጻውያኑ ተጽዕኖ በርካታውን የሥራ ቀን በበዓላት በመመደብ ሥራ እንዳይሠራ፤ ስንፍና እንዲዳብር፤ አገር እንዳታድግ፤ የራሱን ተፅዕኖ አድርጓል። አጼ ቴዎድሮስ ይህንን መቃወማቸው ቤተ ክህነቱን አላስደሰተም፤ መጨረሻቸውንም አፈጠነው።

አጼ ዮሐንስ የቴዎድሮስ ጽዋ እንዳይደርሳቸው በማሰብ ይመስላል በሌላኛው ጽንፍ በመሄድ ሃይማኖትን በሕዝብ ላይ በአስገዳጅነት ጫኑ። ኦርቶዶክሳዊ ክርስትናን እየተቀበለ የማይጠመቅ ማንኛውም ሰው (በተለይ ሙስሊም) ለእምቢተኝነቱ የአጸፋ እርምጃ እንዲወሰድበት በንጉሣዊው መንግሥት ተደረገ። ቤተ መንግሥትና ቤተ ክህነት ሲጣመሩ የሚሆነው ይህ ነው። ብልሑ መሪ ምኒልክ ጉዳዩን በጥበብ ያዙትና ቤተ ክህነቱን በስልት በማስተናገድ ከብዙ ተቃውሞና ጫና ጋር ሥልጣኔን ለኢትዮጵያ አመጡ። አባ ጠቅልል ኃይለሥላሴም የቤተ ክህነቱን ጡንቻ ያስተዋሉ በመሆናቸው በጥበብ መርተውታል። ከሁሉ በላይ ግብፃዊ ፓትሪያርክ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይመጣ በማድረግ ለአገራቸው ትልቅ ውለታ ውለዋል።

ለዘመናት የቆየውን የክርስትናውን የበላይነት በመቃወም እንደ ግራኝ አህመድ ዓይነትም ባገራችን ተነስቷል። በርሱ የውድመት ዘመን እስልምና መር አገዛዝ ለተወሰነ ጊዜ መመሥረት ቢችልም ማስቀጠል ግን አልቻለም። ከርሱ ኪሣራ ያልተማሩ እንደ ጃዋር ያሉ “ዘመነኞች” የ21ኛው ክ.ዘ. ግራኝ አህመድ ነኝ ብለው እስላማዊ መንግሥት ለመመሥረት በሚል ስሑት አካሄድ ሌላ ውድመት አስከትለዋል።  

ከላይ እንደተወሳው ያለንበት ዘመን ቲዎክራሲን ማስተናገድ የሚችል አይደለም። ምክንያቱም በአንድ ሀገር ውስጥ ከኢአማኒ ጀምሮ የተለያየ አመለካከት ያላቸው ዜጎች አሉ። አሁናዊው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሃይማኖታዊ መልክዐ ምድርና ስብጥር ቲዎክራሲን መሸከምም ሆነ ማስተናገድ የሚችል አይደለም። የሚበጀው በአንድ ጨፍላቂ ሃይማኖት ሕዝብን ለማስተዳደር መሞከር ወይም መመኘት ሳይሆን ለሁሉም የሚሆን በሕዝብ የተወከለ መንግሥት መመሥረት ነው፤ ገዢና አዋጪውም ይኸው ነው።

መንግሥት ሃይማኖታዊ ሲሆን አግላይ፣ ጨፍላቂና ጨቋኝ እንጂ አካታችና ነጻ ሊሆን አይችልም። ሃይማኖት ተበደለ፤ ምዕመናን ተጎዱ፤ ሞራል ላሸቀ፤ ንዋየ ቅዱሳት ረከሱ፤ ወዘተ በሚል ሃይማኖትን መንግሥታዊ ለማድረግ መሞከር “ቲዎክራቲክ ሆኖ በደለኝ” ከተባለው በላይ ፍጹም አምባገነንና የለየለት ጨቋኝ ሥርዓት መመሥረት ማለት ነው። ያሁኗ ኢትዮጵያ ይህንን የሚሸከም ትከሻ የላትም።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

eventNEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ኦነግ ጃዋር በመስረተው አዲስ ህብረት ውስጥ “የለሁበትም” አለ፤ ውስኔው ከሕግ ተጠያቂነት ለማለጥ ነው ተብሏል
ብሔራዊ ባንክ በዱባይ ያሉ ድርጅቶን ተጠንቀቁ አለ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2