Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News2  ኦነግ ጃዋር በመስረተው አዲስ ህብረት ውስጥ “የለሁበትም” አለ፤ ውስኔው ከሕግ ተጠያቂነት ለማለጥ ነው ተብሏል
News2POLITICS

ኦነግ ጃዋር በመስረተው አዲስ ህብረት ውስጥ “የለሁበትም” አለ፤ ውስኔው ከሕግ ተጠያቂነት ለማለጥ ነው ተብሏል

Ethioreview newsEthioreview news—August 5, 2025
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር / ኦነግ “ሲያትል ተሰባስበን ህብረት መሰረትን” ካሉት ውስጥ “የለሁበትም” ሲል መግለጫ አወጣ። ሲያትል ትመሰረተ የተባለው የኦሮሞ ልሂቃን ህብረት ጦርነት ከከፈቱ፣ ከውጭ አገራት መንግስታት ጋር ግንባር ከፈጠሩ፣ በውጭ አገራት ከሚረዱ ኃይሎች ጋር ሳይቀር አብሮ እንደሚሰራ ማስታወቁ አይዘነጋም። ፕሮፌሰር መረራ የሚመሩት ኦፌኮ በህብረቱ ውስጥ እንዳለበት ቢጠቀስም ቢያንስ እንደ ኦነግ አላስተባበለም። ኦነግ የያዘው አቋም በሕግ ላለመጠየቅ ሊሆን እንደሚችል አስተያየት የሰጡ አሉ።

የኦሮሞ ምሁራንና የፓለቲካ ፓርቲ ተወካዮች በሚል እራሱን የሰየመ የልሂቃን ቡድን ባሳለፍነው ሰሞን በዩናይትድ ስቴትስ ተሰብስቦ በኦሮሚያ ክልል፣ በኢትዮጵያና የአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ላይ መቅወያየውቱን ገልጾ የፖለቲካ ግቡን አስቀምጦአ ነበር። በሕብረቱ ውስጥ እንደተወከለ የተነገረለት ኦነግ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ በስብስቡ ውስጥ የወከለው አካል አለመኖሩንና ይፋ አድርጓል። በይፋ “የለሁበትም” ሲል በሕግ ሊነሳበት የሚችለውን ስጋት ገፏል።

የኦሮሞ ምሁራን እና የፓለቲካ ፓርቲ ተወካዮች በሚል እራሱን የሰየመ የልሂቃን ቡድን ባሳለፍነው ሰሞን በዩናይትድ ስቴትስ ተሰባስቦ ህብረት መመስረቱን ሲያስታውቅ ወዲያው የተነሳስው ጥያቄ “አገር ቤት ያሉት ኦነግና ኦፌኮ በሰላማዊ መንገድ እነታገላለን እያሉ እንዴት ከዚህ ህብረት ጋር ሊቀላልቀሉ ቻሉ” የሚለው ነበር።

በርካቶች እንደሚሉት በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ የተለመደው የፖለቲካ ጨዋታ የሰላምና የመሳሪያ ትግሉን አንድ ላይ በስልት መጫወት ነው። መሪዎቹ ከተማ ተቀምጠው ወታደውራዊ ክንፎቻቸው በጫካ የተኩስ ትግል ያደርጋሉ በሚል የሚከሰሱ የፖለቲካ ድርጅቶች ምላሻቸው ” ተለያይተናል። አብረን አንሰራም” የሚል ነው። አዲስ አበባ የተቀመጡት መሪዎቻቸው ይህን ይበሉ እንጂ አንድም ቀን በንጹሃን ላይ ለሚፈጽሙት በደል በገሃድ ሲቃወሟቸው አይሰማም።

More stories

የደቡብ ሱዳን ወደ ቀውስ ማምራትና የተመድ ማስጠንቀቂያ

August 24, 2025

የኦሮሞ ዞን ምክር ቤት ጥብቅ ገደብ ጣለ

May 17, 2022

ኢትዮጵያ ላይ በማንኛውም መልኩ የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል- ፊ.ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

June 12, 2025

ከ40 ቀናት ክትትል በሁዋላ 27.75 ኪሎ ግራም ወርቅ በቁጥጥር ስር ዋላ፤ የውጭ አገር ዜጎች አሉበት

August 2, 2025

ሲያትል ስብሰባ ተቀምጦ የነበረዉ ይኸዉ የልሂቃን ስብስብ ውስጥ በአገር ቤት በሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ውስጥ የሚገኙ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግሬስ (ኦፌኮ) እና የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ – ኦነሠ ) በማለት አንድ ድርጅት እንደሆኑ አድርጎ በመግለጽ በስብሰባው መሳተፋቸውን በአደባባይ አስታውቋል።

ይህ ከሆነ ከቀናቶች በሁዋላ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ባወጣው ይፋዊ መግለጫ በስብስቡ ውስጥ የወከለው አካል አለመኖሩንና ተሳትፎም አለማድረጉን አመልክቷል። ስለህብረቱም የሰማው በሚዲያ እንደህነ ጠቁሟል።

” …. የኦሮሞ ፖለቲካ ድርጅቶች (ኦነግ-ኦነሠ፣ ኦፌኮ እና ኦነግ) አስፈላጊውን ለውጥ ለማምጣትና መጪውን ሽግግር ስኬታማ ለማድረግ በተደራጀ መንገድ የሚደረግ ያለውን ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ለመደገፍ መስማማታቸውንም በመግለጽ፤ ለተለያዩ አካላት አብሮ የመስራት ጥሪ አሰምቷል” ሲል ያወጣውን መግለጫ ተከትሎ የጎጃም ፋኖ አድናቆቱን ጠቅሶ አብሮ ለመስራት መዘጋጀቱን ማስታወቁ አይዘነጋም።

ተፈጠረ በተባለው ህብረት ውስጥ ያለበት የኦሮሞ ነጻነት ግባር (ኦነግ) ግን በዚህ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ተደርጓል በተባለው የውይይት መድረክ ላይ ተሳትፎ አለማድረጉንና ሰውም አለመወከሉን ጠቅሶ ስሙ ያለአግባብ ባልነበረበት ስፍራ መጠቀሱን ተቃውሟል፡፡ ፓርቲው ባወጣው ይፋዊ መግለጫ፤ ኦነግ የሲያትል ውሳኔ በሚል ከተላለፈው የፖለቲካ አቅጣጫ ውስጥ ምንም አይነት ተሳትፎ እንደሌለውና ስሙም በዚያ መጠቀሱ ስህተት ነው ብሏል፡፡

የፓርቲው ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዓለማየሁ ድሮ በዚሁ ጉዳይ ዙሪያ ለዶይቼ ቬለ በሰጡት ተጨማሪ አስተያየት፤ “ኦነግ በዚህ ስብሰባ ላይ፣ አልተጋበዘም፣ አልተሳተፈም እንዲሁም የወጣው የአቋም መግለጫ እኛን የሚመለከተን አይደለም” ሲል ነው የገለጸው፡፡ ፓርቲያቸው ጉዳዩን ከማህበራዊ ሚዲያ መስማቱን የገለጸው ኦነግ አቋሙንም ለሚከተለው ህዝቡ ይፋ ማድረጉንም አቶ ዓለማየሁ አስታውቀዋል፡፡

ለኦሮሞ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የአንድነት ጥሪ ያቀረበው የአቋም መግለጫ ያወጣው የፖለቲካ ልሂቃን ስብስቡ ግን ፤ በኦሮሞ የፓለቲካ ኃይሎች መካከል የተጀመረው ውይይት እንዲቀጥልና ከሌሎች የአገሪቱ  ሕዝቦችና ዜጎች ጋር ምክክር ለማድረግ ከስምምነት እንደተደረሰበት አሳውቋል። በዚህም ላይ አስተያየታቸውን የሰጡት አቶ ዓለማየሁ ድሮ፤ “እኛ በመሪህ ደረጃ የኦሮሞ ህዝብ እና የፖለቲካ መሪዎች አንደነት የምንደግፈው ቢሆንም ይሄን መድረክ በተመለከተ ግን ምንም ተሳትፎ ያላደረገበት በመሆኑ ውሳኔውንም እንደማይቀበለው” ነው የገለጸው፡፡ 

ኦነግ “ሁለት መንገድ አጣቀስክ” በሚል ላለመጠየቅ ሲል “እኔ የለሁበትም” ማለቱን የገለጹ ኦፌኮ ዝምታን መምረጡ አስገርሟቸዋል። “ቢያንስ ለፋቸው እንኳን እንዴት ተቃውሞ አላሰሙም” የሚሉ “ነገ መንግስት መሳሪያ ካነገቡ፣ ከተርምስ ኃይሎች ጋር አብራችሁ ትሰራላችሁ ብሎ ህግ ቢጠቅስ ምን ይመልሳሉ” ሲሉ ጠይቀዋል።

የኦነኝ መግለጫ ተከትሎ ኦፌኮ ምን አቋም እንዳለው ለማወቅ ለፕሮፌሰር መረራ ጥያቄ ለማቅረብ ብንደውልም ስላካቸው አይነሳም። ኦፌኮ መስል በሚሰጥበት ወቅት ምላሹን የምናትም እንደሆነ ከወዲሁ እናስታውቃለን።

ጃዋር ህብረቱ ከተፈጠረ ቀናት በሁዋላ በቅርቡ ለውጥ እንዲሚመጣ፣ መንግስትም እንደሚወድቅ የሚያበስር መልዕክት በማህበራዊ ገጹ ማሰራጨቱ ይታወሳል። ኦነግም ይህ ከሆነ በሁዋላ ነው መግለጫ በማውጣት “የለሁበትም” ያለው።


homePOLITICS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ የተመዘገቡ 73 ሺህ በላይ ኤርትራውያን የከተማ ሰደተኞች አሉ፤ ከ7.8 ሚሊዮን በላይ አይማሩም
የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም? 
Related posts
  • Related posts
  • More from author
POLITICS

ኢራን እኛ ላይ ምን ልታደርግ ትችላለች?

March 28, 2026
News2

ብሔራዊ ጥቅምን አሳልፎ ለመስጠት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ባለድርሻ ሊሆኑ አይገባም – በለጠ ሞላ

March 8, 2026
News2

ለክቡር የኢፌዴሪ ማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኝና ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው የቀረበ ጥሪ

March 8, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2