“መጀመሪያ ትህነግን” በሚል ቅድመ ዝግጅት የህልውና ዘመቻው ላይ ከተሳተፉ በሁዋላ ፋኖን በማደራጀት የተከሰሱትና ከአገር ውጭ ያሉ በአብዛኛው የጎጃም ባለሃብቶች ክስ እንዲቋረጥ መወሰኑ ተሰማ። ሽምግልና ተልኮ በጥብቅ ውይይት እየተደረገበት እንደሆነ በቅርቡ መዘገባችን ይታወሳል።
የህዳሴው ግድብ በሚመረቅበት ወቅት ዋዜማና፣ ኢትዮጵያን በመስከረም በአመጽ ለማነቃነቅ ቀጠሮ ይዘው ቅስቀሳ የሚያሰራጩ፣ በተለይም የስደት መንግስት ማቋቋማቸውን ይፋ ያደረጉ ኃይሎች ሰፊ ቅስቀሳ ላይ ባሉበት በዚህ ወቅት ይህ ዜና አስደንጋጭ እንደሚሆን ዜናውን ያጋሩን አስታውቀዋል።
የኢትዮሪቪው ታማኝ የመረጃ ምንጮች እንዳሉት የተጠቀሱት “እውቅ” ባለሃብቶች ወደ አገራቸው ለመመለስ እንቅስቃሴ መጀመራቸውን። ጅማሮው ተስፋ የሚሰጥ እንደሆነ በዘገብንበት ዜና ላይ ዜናው የክልሉንና የአገሪቱን ብጥብጥ ለሚፈልጉና ከጀርባ ሆነው ለሚያቀጣጥሉ አስደንጋጭ እንደሚሆን ምንጮቹን ጠቅሰን አስታውቀን ነበር።
በስም ከሚታወቁ የጎጃም ባለሃብቶች መካከል ከፋኖ እንቅስቃሴ ጀርባ መሆናቸውን አደባባይ ወጥተው የመሰከሩ መኖራቸው አይዘነጋም። ከፋኖ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ የሚሰሩ ሚዲያዎችንና በሚዲያው ላይ የሚሰሩትን ወርሃዊ ደሞዝ ከመስጠት ጀምሮ መቋቋሚያ የለገሱና በቋምኒነት ድጋፍ እያደረጉ ያሉ መኖራቸውንም በተደጋጋሚ የሚገለጽ ጊዳይ ነው።
በዚህን መሰሉና ቀደም ሲል በህልውናው ትግል ወቅት ጀምሮ ዝግጅት የነበራቸው አካላትን ሲደግፉ የነበሩት የጎጃም ባለሃብቶች ከአገር የወጡት በህቡዕ ሲያከናውኑት የነበረው ድጋፍ ይፋ በመታወቁ ሳቢያ እንደሆነ በወቅቱ መዘገቡ አይዘነጋም።
እነዚህ ከፍተኛ ሃብት ያላቸውና በአገሪቱ ባንኮችም ሰፊ እዳ እንደተሸከሙ የሚነገርላቸው ባለሃብቶች ወደ አገር ቤት ለመግባት በከፍተኛ ሚስጢር ሽምግልና ሲካሄድ ቆይቷል። የመረጃው ባለቤቶች እንደሚሉት፣ አሁን ላይ በሌሉበት የተመሰረተባቸው ክስ እንዲቋረጥ ተወስኗል። ይሁን እንጂ እሳኔው ፖለቲካዊ በመሆኑ ወደ አፈጻጸም መላኩን የዜናው ሰዎች ይህ እስከተጻፈ አላረጋገጡም።
አሁን ላይ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የአገሪቱን ፖለቲካ በመገምገም ባለሃብቶቹ በምህረት ወደ አገራቸው ገብተው በሰላማዊ መንገድ ለመስራት ከውሳኔ መድረሳቸው ተሰምቷል። ሁሉም ይሁኑ የተወሰኑት ባይገለጽም በዚሁ ውሳኔያቸው መሰረት ጉዳይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር እንዲደርስ ዕቅድ መያዙን የዜናው ባለቤቶች በነገሩን መሰረት ዘግባን እንደነበር ይታወሳል።
ካለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ በሰላም ከሚኖርበት መንደሩ ሳይቀር ሁከት፣ ዝርፊያ፣ ግድያ፣ እገታ፣ የማዳበሪያ አቅርቦት፣ ሕክምና፣ ትምህርት ቤት፣ ማህበራዊ አገልግሎት፣ የትራንስፖርት አቅርቦት፣ የሸቀጦች ፍሰት ወዘተ ለተናጋበት የአማራ ሕዝብ ዜናው በአስዲስ ዓስመት በጎ ዜና እንደሚሆን ይጠበቃል። የዜናው ምንጮች እንዳሉት የፋኖ እንቅስቃሴ በተለይም የጎጃሙ አካባቢ ወደ መገባደዱ ተቃርቧል ብለዋል። ምን አልባትም ታጣቂዎቹን የሚመሩት “የጥሞና ጊዜ” የሚወስዱበት ቀን ሩቅ እንደማይሆን አመለክተዋል።
በሽምግልናው ውስጥ እነማን እንዳሉበት የዜናው ሰዎች ለጊዜው አልተናገሩም።

