“በቅርቡ ለመከላከያ ሠራዊት አባላት ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች የተሰጠው የማዕረግ ዕድገት ተጨማሪ ግዳጅ እና ተልዕኮንም ታሳቢ ያደረገ” መሆኑ የአገር መከላከያ የሰው ኃብት አመራር ዋና መመሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄነራል አጫሉ ሸለመ አስታወቁ። የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አገራቸው በቀይ ባህር ጉዳይ ለመደራደር ዝግጁ መሆኗን ለአሜሪካ አስታወቁ።
ይህ የተገከጸው ሌተናል ጄነራል አጫሉ ሸለመና መዘጋጀት ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄነራል ጌትነት አዳነ በጋራ በቅርቡ የተሰጠውን የጦር መኮንኖች የማዕረግ ዕድገት አስመልክቶ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ. ም. በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በተላለፈ ቃለ ምልልስ ወቅት ነው።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፤ ማናቸውንም የአገሪቱን ብሔራዊ ጥቅሞች ለማስከበርና ለመጠበቅ፣ ይህንንም በማከናወን ረገድ ሊፈጠር የሚችል የደኅንነት አጣብቂኝ በብቃት ለመወጣት በቂ ዝግጅት እንዳለውም በምልልሱ ተመልክቷል።
ኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካ፣ የኒኩሌር ሃይል ግንባታ የመሳሰሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች እንዳላት በማስታወሰ፣ በውሃ የመጠቀም መብትና የወደብ ጥያቄን የመሳሰሉ ከፍተኛ ብሔራዊ ጉዳዮች እንዳላት በማስታወስ ስለ አገር መከላከያ ዝግጅት አስፈላጊነት ያወሱት መዘጋጀት ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄነራል ጌትነት አዳነ ተናገሩ።
መንግስት ስልሳ ስድስት ለሚሆኑ ከፈተኛ መኮንኖች የማዕረግ ዕድገት መስጠቱን ተከትሎ በሻዕቢያ በሚደገፉና በግልጽ በሚታወቁ ግለሰቦች፣ ሚዲያዎች፣ በውጭ አገር ባሉ ተቀናቃኝ ፖለቲከኞች፣ በአክቲቪዝም ስም በሚቀሳቀሱና በግልጽ ሻዕቢያ የሆኑ የማህበራዊ ሚዲያ ተሰላፊዎች ዘንዳ ከፍተኛ ተቃውሞ መሰማቱ አይዘነጋም። ሹመቱ ኤርትራን ለመውጋት እንደሆነ አድርገው የቅሰቀሳ መረጃ ሲያሰራጩ፣ ሹመቱም የአንድ ብሄር አባላት የበዙበት እንደሆነ በማመልከት ከኢህአዴ ጊዜ ጀምሮ በተዋረድ የመጡ ሲኒየር መኮንኖች እንደሆኑ ማስተባበያ ሲሰሰጥም ሰንብቷል።
መከላከያ ሠራዊት ብሔራዊ ጥቅሞችን በማስከበር ሂደት ለሚመጣ የደኅንነት አጣብቂኝ እንደሚዘጋጅ ቃል አቀባዩ ሲያስታውቁ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሃብቷን ስታለማና በራሷ ብሄራዊ ትቅም ዙሪያ ስትንቀሳቀስ ለሚገጥማት ተግዳሮት መዘጋጀት እንዳለባት መገለጹ፣ ልክ ” የጦርነት ማስጠንቀቂያ” እንደሆነ አድርገው እነዚሁ ክፍሎች ተደጋጋሚ ፕሮግራም ሰርተዋል። “ኢትዮጵያዊ ነን” የሚሉት እነዚሁ ክፍሎች በአደባባይ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ መዘጋጀት እንደማያስፈልጋት ሰብከዋል።
የማዕረግ ዕድገት የተሰጠው የመከላከያ ሠራዊት ሕጎች እና አሠራሮች ተጠብቀው እንደሆነ የሠራዊቱ የሰው ኃብት አመራር ዋና መመሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄነራል አጫሉ ዝርዝር መረጃ በመስጠት አስታውቀዋል። የማዕረግ ዕድገቱ ሲሰጥ ታሳቢ ከሚደረጉ መስፈርቶች ውስጥ ወታደራዊ ግዳጅ አፈጻጸም፣ የአመራር ችሎታ፣ ብቃትና ሥነ ሥርዓት አክባሪነት በዋነኛነት የሚጠቀሱ ጉዳዮች እንደሆኑም አመልክተዋል።
ሹመቱን የሚያገኙ መኮንኖች ስብጥር “ኢትዮጵያን እንዲመስል” ማድረግ እና ክፍት የሹመት ቦታ መኖርም ከግምት ውስጥ እንዲገቡ ጄነራሉ አምልክተዋል። አክለውም “ሹመት ቀጣይ ሊኖር የሚችለውን ግዳጅ መሸከም እንዲችል ኃላፊነትን ተቀብሎ የመሥራት ጉዳይ” መሆኑን ግልጽ አድርገዋል።
የጦር መኮንኖች ወታደራዊ ሹመት የሚያገኙት “ተጨማሪ ግዳጅ እና ተልዕኮ መሸከም እንደሚገባ ታሳቢ ተደርጎ” እንደሆነም ገልጸዋል።
የመከላከያ ሠራዊት የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር የብርጋዴር ጄነራል ጌትነት አዳነ በበኩላቸው፤ የተሰጠው ሹመት የሠራዊቱን ዝግጁነት እንደሚያጠነክር እና ለወደፊት ተልዕኮ በጎ ተጽእኖ እንደሚፈጥር አንስተዋል። በሌላ ቋንቋ የተሰጠው ከፍተኛ ሹመት ስነልቦና የሚገነባ፣ ለበለጠ ኃላፊነት የሚያነሳሳ መሆኑን ገልጸዋል።
የማዕረግ ዕድገቱ “ከብሔራዊ ጥቅም” እና “ሉዐላዊነትን ከማጽናት” አንጻርም መታየት እንዳለበት አስገንዝበዋል።
በአሁኑ ወቅት መንግሥት “ብሔራዊ ጥቅም” በሚል በአጀንዳነት ያቀረባቸው ጉዳዮች መኖራቸውን የጠቀሱት ቃል አቀባዩ፤ ከእነዚህም መካከል በውሃ የመጠቀም መብት እና የወደብ ጥያቄ እንደሚገኙበት አመክተዋል።
“ጋዝ፣ የኒውክሌር ማብላያ ፕላንት፣ የማዳበሪያ ኢንዱስትሪዎች መመሥረት” ጉዳዮችም ከአጀንዳዎቹ መካከል እንደሆኑ አንስተዋል። ብርጋዴር ጄነራል ጌትነት፤ “በሕዝብ የተመረጠ መንግሥት እነዚህን ብሔራዊ ጥቅሞችን ‘እነዚህ ናቸው ላሳካቸው የምፈልገው’ እስካለ ድረስ ሠራዊት ደግሞ መዘጋጀት አለበት” ብለዋል።
ሠራዊቱ የሚያደርገው የመጀመሪያ ዝግጅት አንጀንዳዎቹን በማስፈጸም ሂደት ውስጥ በሌላ አካል ሊፈጠር ከሚችል ወደ ኃይል አማራጭ የመምጣት አዝማሚያ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ተናግረዋል።
“የኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕዝብ ይህንን ጥያቄ ሲያነሳ ‘በሰላማላዊ መልኩ እፈታዋለሁ’ ብሎ ነው የሚያነሳው። ግን ደግሞ በዚህ ውስጥ የሚገባ security dilemma የሚባል ነገር አለ” ሲሉ በሂደቱ የደኅንነት አጣብቂኝ ሊፈጠር እንደሚችል ጠቁመዋል።
” ‘ኢትዮጵያ ይህንን ካነሳችማ እንዲህ ሊሆን ነው’ ብሎ ወደ ኃይል አማራጭ የሚመጣ ነገር ከሆነ ሠራዊት መዘጋጀት አለበት ማለት ነው” ሲሉም ሐሳባቸውን አብራርተዋል።
በሠራዊቱ በኩል የሚደረገው ዝግጅትም “የመንግሥትን ተልዕኮ እና ትዕዛዝ ያከበረ” እንደሚሆንም አያይዘው ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ባለፈው ሳምንት መስከረም 6/2018 ዓ.ም. ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ “የጂኦግራፊ እስረኛ ሆና ለዘላለም” እንደማትኖር መናገራቸው ይታወሳል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ “አይቀሬ” መሆኑን በአጽንኦት የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ጉዳዩ የሚመለክታቸው አገራት “በፈጠነ ጊዜ ራሳቸውን ለድርድር ዝግጁ እንዲያደርጉ አሳስባለሁ” ማለታቸው አይዘነጋም።
ከለወጡ በሁዋላ በብዛት፣ በጥራት፣ በትጥቅ፣ በዓይነት ራሱን በአየር፣ በመድርና በባህር ኃይል ያበቃው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አቅም በቀጣናው አስፈሪ መሆኑን ተከትሎ በቀጣናው ሰፊ ኃላፊነት በመቀበል ላይ እንደሆነ እየተሰማ ነው።
በተለይም በቀይ ባህር ላይ ስጋት ያላቸው ኃያላን አገራት፣ ኢትዮጵያ ወደ ቀይ ባህር እንድትገባ ድጋፍ በሚሰጡበት ወቅት ኤርትራ ለድርድር ዝግጁ መሆኗን ማስታወቋ ተሰምቷል።
“በአፍሪካ ቀንድ ፣ በቀይ ባህር ፣ በናይል ተፋሰስ ዙሪያ ትርጉም ያለው ውይይት ለማድረግ ዝግጁ ነኝ ” መሆኗን የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኦስማን ሳሌህ ናቸው የተናገሩት። ኦስማን ሳሌህ ይህን ማለታቸው በተደጋጋሚ ለመነጋገር ጥያቄ ለመታቀርበው ኢትዮጵያ ማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ የማነ በቲውተር ገጻቸው “የምን ድርድር” በሚል ሲረጩት ከነበረርው ምላሽ ጋር የተቃረነ ሆኗል።
በአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት መሥሪያ ቤት የፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ማሳድ ቡሎስ አሜሪካ ኒውዮርክ በተባበሩት መንግሥታት (UN) ጉባኤ ላይ ሆነው በጎንዮሽ ከኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳሌህ ጋር ባደረጉት ውይይት ነው ይህ የተባለው።
በውይይት ኢትዮጵያ ግልጽ ያደረገችው የቀይ ባህር ጉዳይ የተነሳ ሲሆን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ ሀገራቸው ብሔራዊ ሉዓላዊነቷን በጠበቀ ሁኔታ በጋራ ጉዳዮች ላይ በተለም በአፍሪካ ቀንድ ፣ በናይል ተፋሰስ፣ በቀይ ባህር ዙሪያ ትርጉም ያለው ውይይት ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የአሜሪካው ከፍተኛ ባለስልጣን ማሳድ ቦሎስ ሀገራቸው አሜሪካ ለዓለም አቀፍ ንግድ፣ ደህንነት እና ፀረ-ሽብርተኝነት ጥረቶች ወሳኝ በሆነ ቀጠና ውስጥ ውይይት እና መግባባትን ለመፍጠር ፅኑ ፍላጎት እንዳላት አስምረውበታል።
ኤርትራ አጋጣሚውን ከአሜሪካ ጋር ግንኙነት ለማደስ እንደምትጠቀምበት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አመልክተዋል። አሜሪካም በተመሳሳይ ከኤርትራ ጋር ለመስራት ፍላጎት እንዳላት አስታውቃለች ተብሏል።
ኤርትራ ለዝግጅት ክፍት መሆኗን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ በኩል የተባለ ነገር የለም። ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ በታሪክ፣ በህግ፣ በዓለም ዓቀፍ አጋብቦችና የባህር በሯን ስትነጠቅ በነበሩ አስቻይ ያልሆኑ ህገ ወጥ አካሄዶችን ሳቢያ መብቷን ማታቷን በማንሳት የተፈጠረው የታሪክ ስብራት የሁለቱንም ሕዝብና አገራት በማይጎዳ መልኩ ለማስፈጸም እንደምትሰራ ደጋግማ ማስታወቋ አይዘነጋም።
በ80ኛው የተባበሩት መንግስታት ስብሰባ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ስላሴ የኢትዮጵያን ፍላጎት ከዓለም ዓቀፍ ህግ አንጻር ቀይ ባህር ብቻ ሳይሆን እስከ ህንድ ውቅያኖስ መጠቀም ሊከለከል እንደማይገባ ጠቅሰው ተናግረዋል።
“ኢትዮጵያ የባህር በር አያስፈልጋትም፣ ተዘገታ መኖር አለባት” የሚሉት በስም “ኢትዮጵያዊ” የሚባሉ ቡድኖችና ግለሰቦች የኤርትራን አዲስ አቋም አስመልክቶ ይህ እስከተጻፈ ድረስ ያሉት ነገር የለም።
የኤርትራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያነጋገሩት የአሜሪካው ከፍተኛ ባለስልጣን ማሳድ ቦሎስ አዲስ አበባ በመምጣት ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር መምክራቸው አይዘነጋም። በምክክራቸውን በተመሳሳይ ጉዳይና በቀተናው እንዲሁም በቀይ ባህር ጸጥታ ዙሪያ ገንቢ ውይይት ማደራግቸውን ማስታወቃቸው ይታወሳል። ይህ ውይይት የዚያ ቀታይ እንደሆነም ይታመናል።

