በአድልዎ ኢትዮጵያን በመደብደብና በማውገዝ የሚታወቁ የዓለም ዓቀፍ ታዋቂ ሚዲያዎች የታላቁን የህዳሴ ግድብ አስመልክተው አድናቆታቸውን ችረዋል። የመረቃውንና የግንባታውን መጠናቀቅ አስመልክቶ ሲዘግቡ የአንድነትና የሉዓላዊነት ተምሳሌት፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ቦንድ በመግዛትና በልዩ ልዩ መዋጮ የበኩሉን አስተዋጽኦ ያበረከተበትና የኢኮኖሚ እድገትና የብልጽግና መሰረት እንደሆነ አመላክተዋል።
ዶቼ ቬለ ግድቡ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ገንዘብ እና ጉልበት ያለ የውጭ እርዳታ መገንባቱን በማስታወስ ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ልብ ያስተሳሰረ ታላቅ ፕሮጀክት ሲል ምስክርነቱን ሲሰጥ፣ ቢቢሲ “የኢትዮጵያውያን ኩራት” ሲል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በይፋ መመረቁን የኢትዮጵያ ሕዝብ ካለው ትክክለኛ ስሜት ጋር አያይዞ ዘግቧል።
በግድቡ ግንባታ ወቅት የታየው ህዝባዊ ተሳትፎ በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይወሰን በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ያካተተ መሆኑን የአሜሪካው ሲቢኤስ ኒውስ አስነብቧል። ይህን ተሳትፎ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጭምር እንደ አርአያ የሚወሰድ እንደሆነም ጠቁሟል። ኢትዮጵያ በራሷ አቅም የገነባችው ግዙፍ ግድብ ከተዕፅኖ በፀዳ መልኩ የመልማት መብቷን ያረጋገጠ መሆኑንም አመልክቷል።
አሶሺየትድ ፕሬስ በበኩሉ “ኢትዮጵያውያን ተስፋን የሰነቁበት በአፍሪካ ግዙፍ ግድብ ተገንብቶ ተጠናቀቀ” ሲል፣ ዴይሊ ኔሽን በበኩሉ “የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የአዲስ ዓመት ስጦታ” ብሎታል።
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ እድገትና ብልጽግና መሰረት የጣለ መሆኑን ደጋግመው ያመለከቱት ዓለም ዓቀፍ ሚዲያዊች መካከል ሮይተርስ በአፍሪካ ትልቁ ኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ግድብ መሆኑን ጠቅሶ የኢትዮጵያን የኤሌክትሪክ አቅርቦት በእጥፍ እንደሚያሳድግ ዳታ ጠቅሶ ዘግቧል። ሮይተርስ አያይዞ “ኢትዮጵያ ለሚሊዮኖች የኤሌክትሪክ ኃይል ማዳረስ የሚያስችላትን በአፍሪካ ግዙፍ የሆነ የኃይል ማመንጫ ግድብ መረቀች” ሲል ዜናውን አልቆታል።
ፍራንስ-24 በበኩሉ “ኢትዮጵያ ሚሊዮኖችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ የሚያደርገውን ግዙፍ ግድብ ገንብታ አጠናቀቀች” ሲል፣ ኤቢሲ ኒዉስ በኢትዮጵያ ውስጥ የኤሌክትሪክ ሀይል ተጠቃሚው ህዝብ 54% ብቻ መሆኑን ጠቅሶ ከ5ሺህ 150 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል የሚያመነጨው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኤሌክትሪክ ሀይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ያለውን ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን አስታውቋል። የታዳሽ ኃይል አቅርቦት ለኢንዱስትሪ መስፋፋት፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለህዝቡ የኑሮ ደረጃ መሻሻል ወሳኝ መሆኑም አስታውሷል።
አሶሺየትድ ፕሬስ በበኩሉ “ኢትዮጵያውያን ተስፋን የሰነቁበት በአፍሪካ ግዙፍ ግድብ ተገንብቶ ተጠናቀቀ” ሲል የኢትዮጵያውያንን ተስፋ አንጸባርቋል።
ዘገባዎቹ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድቡ ጠቀሜታ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን ለአካባቢው ሀገራት ያለውን ፋይዳ ሲያስታውቁ በቀጠናው መተሳሰርን ለመፍጠር ቁልፍ ነው ብለዋል።
በመርቃቱ ላይ የተጋበዙት የምስራቅ አፍሪቃ መሪዎች እያንዳንዳቸው ገድቡ የሁሉም መሆኑን ሲያስታውቁ ፋይዳውን በማጉላትና ኃይል ለመጠቀም ያላቸውን ፍላጎት በማሳየት ነው። ኢትዮጵታ በ2030 በግምት 300 ሚሊኦን ለሚሆነው የሰብ ሰሃራ ሕዝብ ኃይል ለማቅረብ አቅዳ ለምጸራው ስራ መስፈንጠሪያ እንደሆነ ቀደም ሲል መገለጹ አይዘነጋም።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ግድቡ ለጎረቤት ሀገራት ስጋት ሳይሆን የጋራ እድል መሆኑን መናገራቸውን በማሳያነት በመጥቀስ ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ኃይል በመሸጥ ቀጣናውን በኃይል ማስተሳሰር እንደሚያስችላት ሮይተርስ እሳቸውን ጠቅሶ አመልክቷል።
የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች ግድቡን ከግዙፍነቱና ከሚያመነጨው ኃይል ባለፈ የኢትዮጵያውያንን አንድነት፣ አቅም እና ሉዓላዊነት ማሳያ አድርገው አቅርበውታል።
ቢቢሲ “የኢትዮጵያውያን ኩራት” በማለት ሲገልጸው፣ ዴይሊ ኔሽን በበኩሉ “የኢትዮጵያውያን የአዲስ ዓመት ስጦታ” በማለት ከመጭው አዲስ አመት ጋር አያይዞ ዘግቦታል፡፡

