Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የኢትዮ – አሜሪካ ስትራቴጂካዊ ትብብር እና የቀጠናው አዲስ አሰላለፍ፤ “አሰላለፉ የኢትዮጵያ የጂኦስትራቴጂ ኩስምና ማሳያ ነው”
News

የኢትዮ – አሜሪካ ስትራቴጂካዊ ትብብር እና የቀጠናው አዲስ አሰላለፍ፤ “አሰላለፉ የኢትዮጵያ የጂኦስትራቴጂ ኩስምና ማሳያ ነው”

Ethioreview newsEthioreview news—January 27, 2026
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

አዲስ ሪፖርተር – ይፋ በተደረገው አዲስ ሹመት መሰረት፣ የአርሚ 50 አዛዥ ወዲ ኤምባቲ የትግራይ ኃይሎች ዋና አዛዥ በመሆን ሌተናል ታደሰ ወረደን ተክተዋል። ታደሰ ወረደ ከትግራይ ርዕሰ መስተዳድርነታቸው በተጨማሪ ይዘውት የነበረውን የጸጥታ ጉዳይ ኃላፊነት የተነጠቁት አዲስ ለሚጀመረው ኦፕሬሽን ሊታመኑ ባለመቻላቸው እንደሆነ ተመልክቷል። የደቡብ ግንባር አዛዥ ዮሐንስ መዲድ የትግራይ ሰራዊት ዘመቻ ኃላፊ፣ ማሾ በየነ የመረጃ እንዲሁም፣ ምግበይ የስልጠና ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።

አራቱንም ቁልፍ ወታደራዊ ሹመት ለአደዋ ተወላጆች መሰጠቱን የተሿሚዎቹን የትውልድ ሃረግ የሚያውቁ አስታውቀዋል። ሹም ሽሩን ተከትሎ በጠለምት በኩል ጦርነት ተጀምሯል ። ከሱዳን፣ ከኤርትራ፣ ከፋኖ ጋር ጥምረት በመፈጠር ትህነግ የውጊያ አቅሙን ማሳደጉን ደጋፊ የሆኑ የመገናኛ ዘዴዎች አስቀድመው ሲያስታውቁ እንደነበር ይታወሳል።

ፋኖ፣ ሱዳን፣ ሻዕቢያና ትህነግ በጋራ ኢትዮጵያን ለመውጋት የደረሱበትን ስምምነት “ትግሉ ተጠልፏል” በማለት ወደ ሰላማዊ መንገድ የተመለሱ የፋኖ አመራሮች መናገራቸው ይታወሳል።

በሪፖርተር ጋዜጣ የወልቃይት አስተዳደር እንዲፈርስ መንግስት አቋም መያዙን እንዲናገር ከተደረገ በሁዋላ ዜናው በከፍተኛ ደረጃ ለቅስቀሳ እንዲውል ተደረገ። በአካባቢው ያለውን ነዋሪ ተስፋ ለማስቆረጥ ሰፊ የቅሰቀሳና የፕሮፓጋንዳ ስራ ከተሰራ በሁዋላ በሽሬ ያሉ እናቶች “እናመሰግናለን ሽሬ፣ በቀጣይ ሳምንት ምዕራብ እንገናኝ” በሚል ሲያዜሙ፣ ሲጨፍሩና ታጣቂዎችን ሲያበረታቱ የሚያሳይ ቪዲዮ ይፋ ሆነ።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ጄኔራል ምግበይ “በሚቀጥለው ሳምንት ወልቃይትን እንይዛለን” ባሉ በሳምንት ልዩነት እንደተባለው ጦርነት ተቀሰቀሰ። አርሚ 11 በትናንትናው ዕለት በማይ ዳጉሽ አቅጣጫ ወደ ምስራቅ ጠለምት ዲማ ከተማ ለመግባት 30 ኪሎሜትር ርቀት ድረስ ተጠጋ። ይህ ኃይሉን አጠናክሮ የተከዜ በረሃን አቋርጦ የተጠጋው ኃይል ከመከላከያ ሰራዊት የመከላከል እርምጃ እንደተወሰደበት የወርዳው አስተዳደር ለአዲስ ሪፖርተር አስታውቋል።

በትናትናው የዜና ዕወጃችን እንደተገለጸው ሁለት አዛዦችና የጦር መሳሪያዎች የተያዙ ሲሆን፣ የተገደሉና የቆሰሉ በርካታ መሆናቸው ታውቋል። ከመከላከያ የመከላከል እርምጃ በሁዋላ የአርሚ 11 ኃይል ወደ መጣበት መመለሱ ታውቋል። የምስራቅ ጠለምት ወረዳ አመራር እንዳሉት፣ አሁን ላይ 30 ጉዊላ፣ በሚባልና ደገብራይ በሚባሉ ቦታዎች ቅርብ ርቀት ላይ ያለው የትህነግ ኃይል ለጊዜው ውጊያ ቢያቆምም ኃይሉን አሰብስቦ ዳግም በሌሎች አቅጣጫዎችም ጭምር ጦርነቱን በማስፋት የመቀጠል ዕቅድ እንዳለ መረጃ እንዳላቸው አመልክተዋል።

የተከዜን በረሃ አቋርጠው የማዕከል ከተሞችን ለመያዝ አቅደው በሁለት አቅጣጫ ውጊያ የከፈቱት የትህነግ ኃይሎች፣ የማይጠብሪን መንገድ መቁረጣቸው ተሰምቷል። ጦርነቱን የሚመራው የአገር መከላከያ በመሆኑ ብዙ መረጃዎች መስጠት ባይቻልም፣ የማይጠብሪ መንገድ የተቆረጠው ጠለምትን በመገደብ ስትራቴጂካል ጥቅም እናገኛለን ብለው በማሰባቸው እንደሆነ ተመልክቷል።

በትናትናው ዕለት በአገር መከላከያ የመከላከል እርምጃ ወደ መጣበት ከተመለሰው ኃይል ውስጥ አብዛኞቹ የማይጠብሪ ተወላጆች በመሆናቸው እየከዱ ወደ መኖሪያ ቤታቸው እያመሩ መሆኑ ተሰምቷል። በዚሁ ሳቢያ ከሽሬ ወደ ማይጠብሪ የሚሄደውን መንገድ ትህነግ እንደዘጋው የአካባቢው የአዲስ ሪፖርተር ተባባሪ አስታውቋል።

አርሚዎች የተደራጁት በአካባቢ ተወላጆች በመሆኑ፣ ካለፈው ጦርነት ጠባሳ የተነሳ መዋጋት የማይፈልጉ እየሸሹ ወደቤታቸው መግባት አሁን አሁን የተለመደ እንደሆነ እነዚሁ ወገኖች ይናገራሉ። ወደ ቤታቸው የማይገቡት ደግሞ የትግራይ ሰላም ኃይሎችን ይቀላቀላሉ። ጦርነቱ ትናንት ተጀምሮ እንደቆመ ቢገልጽም የትህነግና የፋኖ ደጋፊዎች የአርሚ 11 ኃይሎች ወደ ምስራቅና ምዕራብ ጠለምት እየተጠጉ መሆናቸውን እያስታወቁ ነው።

ሰፊ መሬት በመቆጣጠር ከፋኖና መለያ ልብሳቸውን ከቀየሩ የሻዕቢያ ኃይሎች ጋር በመሆኑ ጥቃታቸውን ማጠናከራቸውን እነዚሁ ወገኖች እየገለጹ ነው። ከሁሉም ወገን የሚወጡ መረጃዎች በሚታወቁ በገለልተኛ ወገኖች ማረጋገጫ አልተሰጠጠባቸውም። ትህነግም በሚታወቁ የማህበራዊ ገጾቹ የገለጸው ነገር የለም።

በሌላ ተመሳሳይ የጦርነት ዜና ሱዳን የነበረውና ከሻዕቢያ ጋር በይፋ ወታደራዊ ጥምረት መፈጸሙ በመረጃ ይፋ የሆነበት አርሚ 70 ሺረረና መሰፈራቸው ታውቋል።

ይህ በሱዳን በኩል ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ ሺረርና የሰፈረው ኃይል ከፋኖ የአካባቢው ኃይል ጋር ግንባር ገጥሟል። የአካባቢው የመረጃ ሰዎች እንዳሉት የካቲት 11 ቀንን በወልቃይት ለማክበር ከፋኖ ጋር የጥምር ጥቃት ለመሰንዘርና፣ እነሱን ተከትሎ የሻዕቢያ ኃይል ሙሉ ደጋፍ ለመስጠት ቦታ ይዘዋል።

የወልቃይት ዞን ስለጉዳዩ የሚያውቀው እንዳለ ከአዲስ ሪፖርተር ለቀረበለት ጥያቄ “እኛ ጋር ምንም የለም። ሁሌም ዝግጁ ነን” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። የአገር መከላከያ ድንበር አካባቢ በመሆኑ ሰፊ ዝግጅት እንዳለ ያመለከቱት እንደሚሉት የትህነግ፣ ፋኖና ሻዕቢያ ኃይሎች በወልቃይት አቅጣጫ ከመጡ ሙሉ የተከዜ ኃይል፣ መከላከያና ራሱን ያደራጀው ሕዝብ ይሆናል ያሉትን ርምጃ ይጀመራሉ።

ይህ በንዲህ እንዳለ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ መሪ ዘመነ ካሴ በኤርትራ ከፍስሃ ማንጁስ ጋር ከተገናኑ በሁዋላ የደረሱበት ስምምነት ታውቋል። በኦምሃጀር በተደረገ የጋራ ውይይት ትህነግ ለፋኖ ሎጂስቲክ፣ በጦርነት ለሚጎዱ የሕክምና፣ የጦር ሜዳ የወጊያ ታክቲክ ንድፍ ድጋፍ፣ በሚደረገበት አግባብ ዝርዝር ስምምነት አድርገዋል።

ቀደም ሲል ትህነግ ሕዝብ ከጎኑ እንዲሰለፍ ሲያደርግ እንደነበረው ፋኖም በመከላከያ ሰራዊት መለያ ዩኒፎርም ከባድ ወንጀሎችን እየፈጸመ ህዝብ በመንግስት ላይ እንዲነሳ የሚያስችል ፕሮፓጋንዳ እንዲሰራ ስትራቴጂ ተነድፎለታል። ፋኖ በዚሁ ዕቅድ መሰረት የተሰጠውን ሲተገብር የትህነግና የሻዕቢያ ተባባሪ ሚዲያዎች ይህንኑ በማስተጋባት ሕዝብ እንዲነሳና እንዲማረር ቅሰቀሳ እንድሚያደርጉ ቃል ተገብቷል።

በቅርቡ እነ አቶ ነዓምን የመሰረቱት ኢትዮጵያን በህዝባዊ እምቢተኛነት የማነሳሳትና የማተራመስ ዕቅድ ለፋኖ በተቀረጸው ስትራቴጂ መሰረት የሚፈጸሙ ከባድ ወንጀሎችን በማሰራጨት፣ በማራባትና፣ በማግን የፕሮፓጋንዳ ስራ እንዲሰራ ከስምምነት መደረሱን በዙም የተደረገውን ስብሰባ ዋቢ አድርገን ማቅረባችን አይዘነጋም። አድማጮቻችን የጦርነት ውሎ ዘገባዎችን በአዲስ ሪፖርተር የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገጾቻቸን የከተሉ። የዩቲዩብ ገጻችንን ላይክና ሼር ታድርጉ።

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
“ኢትዮጵያ ወደ ባህር የመውጣት ፍላጎቷን እውቅና እንሰጣለን” ሶማሊላንድ
“ራሳቸው የለኮሱትን እሳት ራሳቸው ይሙቁት” አቶ ጌታቸው ረዳ – ትህነግ ወጣቶችን እንደ ልማዱ ለመማገድ የሚደረገው ሩጫ ይቁም!
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2