Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  SOCIETY  በመስከር በሚፈጸም ወንጀል ስለሚኖር የወንጀል ሀላፊነትና የህጉ አንድምታ
SOCIETY

በመስከር በሚፈጸም ወንጀል ስለሚኖር የወንጀል ሀላፊነትና የህጉ አንድምታ

Ethioreview newsEthioreview news—February 3, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

አንድ ሰው ወንጀል ፈጽሟል ተብሎ ክስ ሊቀርብበት እና ሊቀጣ የሚችለው የተላለፈውን የወንጀል ድርጊት ሊያቋቁሙ የሚችሉት ህጋዊ፤ ግዙፋዊ እና ሞራላዊ ፍሬ ነገሮች ባንድ ላይ ተሟልተው ሲገኙ ብቻ እንደሆነ የኢፌድሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 23/2/ ይደነግጋል፡፡ በዚህ መሰረት የወንጀል ፈጻሚው የሀሳብ ክፍል (moral element) መረጋገጥ ያለበት አንዱ ዋናው የወንጀል ማቋቋሚያ መስፈርት መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡ በሌላ በኩል አንድ ሰው በወንጀል ህግ መደበኛ ድንጋጌዎች መሰረት የሚቀጣው ላደረገው ድርጊት ሃላፊ የሆነው ወንጀል አድራጊ ብቻ ነው፡፡ በእድሜ፣ በህመም፣ ባልተለመደ የእድገት መዘግየት፤ ጥልቅ በሆነ የአእምሮ የመገንዘብ ወይም የማመዛዘን ችሎታ መቃወስ ወይም በማናቸውም ስነ ህይዎታዊ ዘዴ ድርጊቱ ሊያስከትል የሚችለውን ውጤት ለመገንዘብ የማይችል እንደሆነ ፍርድ ቤት ቀርቦ ችግሩ ስለመኖሩ በበቂ ማስረጃ ሲረጋገጥ በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ከወንጀል ተጠያቂነት ሊድን እንደሚችል የወንጀል ህጋችን አንቀጽ 48 እና 49 ድንጋጌዎች ያመለክታሉ፡፡

በተመሳሳይ መልኩ በአልኮል ወይም በሌላ አዕምሮን በሚያደነዝዝ ነገር መስከር የአእምሮ የመገንዘብ ወይም የማመዛዘን ችሎታ መቃወስ ሊያስከትል ቢችልም ከጉዳዩ ልዩ ባህሪ አንጻርም በመስከር በሚፈጸም ወንጀል ስለሚኖር የወንጀል ሃላፊነት፤ ፍፁም ወይም ከፊል ኢ-ሃላፊነት ሊያስይቅ እንደሚችል ተደንግጓል፡፡ በእነዚህ ድንጋጌዎችም መሰረት በስካር ውስጥ ሆነው የወንጀል ድርጊት የፈጸሙ ሰዎች እንደየሁኔታው ከሙሉ ሃላፊነት እሰከ ከፊል ሃላፊነት ወይም ሙሉ በሙሉ ኢ-ሃላፊ ናቸው በሚል በፍርድ ቤቶች ውሳኔ ይሰጣል፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ብዙ ተከሳሾች ወንጀሉን የፈጸምሁት ሰክሬ ነው፤ ሃላፊነት የለብኝም በሚል የሚከራከሩ እና በዚሁ መሰረት ውሳኔ ሲሰጥ ይሰተዋላል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ መከራከሪያ ከመቅረቡ በፊትም ሆነ በዚህ መከራከሪያ መሰረት ውሳኔ ለመስጠት የሚከተሉት ነጥቦች በሚገባ መታየት አለባቸው፡፡ ይኸውም ግለሰቡ የሰከረው እና ድርጊቱን የፈጸመው፡-

• ወንጀሉን ለመፈፀም በራሱ ፍላጐት ወንጀሉን ለመፈፀም በማቀድ ወይም ሊፈፅም እንደሚችል እያወቀ (50/1/) መሆኑ፣ ወይም
• ድርጊቱ ወንጀሉን ለመፈፀም እራሱን እንደሚያጋልጥ እያወቀ፣ ማወቅ እየቻለ ወይም ማወቅ እያለበት በራሱ ጥፋት ስለመሆኑ(50/2/ሀ/) ፣
• በቸልተኝነት ራሱን ወደ ከፊል ወይም ፍፁም ኢ-ሃላፊነት ራሱን ካስገባ በኋላ ሊያደርግ ያልፈቀደውን ወይም ያላሠበውን ወንጀል ስለማድረግ አለማድረጉ 50/3/፤59 እና 491፣ ወይም
• ምንም ጥፋት ሣይኖረው (ተገዶ) በፍፁም ኢ-ሃላፊነት ውስጥ ባለበት ጊዜ የፈፀመው ድርጊት (50/4/) ስለመሆን አለመሆኑ፣
• ከሁሉም በላይ ግን የተከሣሽን ፍፁም ወይም ከፊል ኢ-ሃላፊነት ማስረዳት ያለበት ማን እና በምን ሁኔታ ነው የሚሉትን ነጥቦች ከወንጀል ህጉ አንቀጽ 51 መሠረታዊ ሃሳቦች ማየት ተገቢ ይሆናል፡፡

እነዚህ ነጥቦች ባብዛኛው የሰውን ልጅ ውስጣዊ የእምሮ ማገናዘብ እና የማመዛዝን ደረጃን እና ሁኔታን የሚመዝኑ በመሆኑ የሚረጋገጡትም ጠንከር ባለ እና በበቂ ማሰረጃ አንዳንዴም በሞያ ማስረጃ (expertise witness) ሊሆን ይችላል፡፡ በመሠረቱ የወንጀል ህጉ አንቀጽ 51/1/ ድንጋጌ በግልፅ እንደሚያመለክተው አንድ ሠው በስካርም ይሁን በሌላ ምክንያት አንድን ድርጊት ሲፈፅም በከፊል ወይም በፍፁም ሀላፊ ስለመሆኑ አጠራጣሪ ነገር ሲኖር ልዩ የአዋቂ ምርመራ በፍ/ቤት ትዕዛዝ መሠረት ሊጣራ የሚገባው ስለመሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ስለሆነም አንድ ሰው አልኮል አልኮል በመሽተቱ፣ በመኮላተፉ እና በመንገዳገዱ ምክንያት በፍፁም ሃላፊነት ውስጥ እራሱን አስገብቶ ነበር ብሎ መደምደም ተገቢነት ያለው አይደለም፡፡ ይህም ተከሳሽ በመስከሩ እና ማገናዘብ ባለመቻሉ ምክንያት ድርጊቱን ስለመፈጸሙ ፍ/ቤት አዝዞ በልዩ የአዋቂ ምርመራ ባልተረጋገጠበት ሁኔታ በግምት ተከሣሽ ፍፁም ኢ-ሃላፊነት ነበረው ወደሚለው መደምደሚያ ይወስደናል፡፡ በሌላ በኩል የተከሣሽን መስከር በምስክሮች ቃል አረጋግጫለሁ ቢባል እንኳን (ምስክሮች በጉዳዩ ላይ ልዩ አዋቂ አለመሆናቸው እንደተጠበቀ ሆኖ) ተከሣሽ ወደ ፍፁም ኢ-ሃላፊነት የገባው ከላይ በተገለፀው አግባብ ድርጊቱን ለመፈፀም በማቀድ፣ ወይም ሊፈፀም እንደሚችል እያወቀ አስቦ እራሱን ወደ ፍፁም ኢ-ሃላፊነት አስገብቶ ከሆነ እነዚህ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ የማይሆኑለት እና በመደበኛ ድንጋጌዎች መሠረት ሊከሰስ እና ሊቀጣ የሚገባው ስለመሆኑ የወንጀል ህጉ አንቀጽ 50/1/ ድንጋጌ ያስረዳል፡፡ በአንፃሩ ተከሣሽ የወንጀል ድርጊቱን ለመፈፀም ራሱን እንደሚያጋልጥ እያወቀ ወይም ለማወቅ እየቻለ ወይም ማወቅ እያለበት በራሱ ጥፋት ወደ ፍፁም ኢ-ሃላፊነት ወይም ከፊል-ሀላፊነት ራሱን ካስገባ በኋላ ድርጊቱን የፈፀመ እንደሆነ በወንጀል ህጉ አንቀጽ 50/2/ እና 59 መሠረት በቸልተኝነት በፈፀመው ድርጊት ተጠያቂ እንደሚሆን ይደነግጋል፡፡

More stories

ወገኛ ምርኮዎች !!

August 27, 2021

በዓለም ባንክና በኢትዮጵያ መንግሥት የሚተገበር የ550 ሚሊዮን ዶላር ፕሮጀክት ዛሬ በይፋ ይጀመራል

January 29, 2022

በድንገተኛ የሞተር ብልሽት የፖላንድ አውሮፕላን አዲስ አበባ አረፈ

September 18, 2021

ኤርትራዊያን ስደተኞች “አሸባሪው ወራሪሃይል ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ፈጽሞብናል” ሲሉ የዓለም ሕብረተሰብ ተማጸኑ

February 23, 2022

በሌላ በኩል አድራጊው በገዛ ጥፋቱ ወደ ፍፁም ኢ-ሃላፊነት ራሱን ካስገባ በኋላ ያልፈቀደውን ወይም ያላሰበውን የወንጀል ድርጊት ከፈፀመም በወንጀል ህጉ አንቀጽ 491 መሠረት ተጠያቂ እንደሚሆን የወንጀል ህጉ አንቀጽ 50/3/ ድንጋጌ ያዝዛል፣ በተጨማሪም ተከሣሹ ምንም ጥፋት ሳይኖረው ወይም በሌላ ሰው ተገዶ በፍፁም ኢ-ሃላፊነት ውስጥ የነበረ ከሆነም የወንጀል ተጠያቂነት የሌለው ስለመሆኑ የወንጀል ህጉ አንቀጽ 50/4/ ድንጋጌ ያስቀምጣል፡፡

ስለሆነም አንድ ሰው በወንጀል ተከሶ ድርጊቱን የፈጸመው በስካር ውስጥ መሆኑ ቢረጋግጥ እንኳን ወደ ስካር የገባው ወንጀሉን ለመፈጸም አቅዶ ስለመሆኑ ወይም በሶስተኛ ወገን ተገፋፍቶ ስለመሆኑና አለመሆኑ ወይም ስለሀላፊነት መጠኑ በአግባቡ በማስረጃ መረጋገጥ ያለበት ጉዳይ ነው፡፡
በአጠቃላይ በስካር የሚፈጸሙ የወንጀል ድረጊቶች በአብዛኛው ከወንጀል ተጠያቂነት የማያድኑ በመሆኑ ዜጎች ይህንን ተገንዝበው ተገቢውን የጥንቃቄ እርምጃ መውሰድ ይጠበቅባቸዋል፡፡ በተጨማሪም ስካር እና የወንጀል ሃላፊነት በጥንቃቄ ሊታይ የሚገባው እና የማስረጃ ደረጃዉም ከተለመደው የማስረጃ አቀራረብ ላቅ ያለ የአዋቂ ማስረጃን የሚጠይቅ በመሆኑ ተከሳሾች፣ ዐቃቢያነ ህጎችም ሆነ ዳኞች በሚሰጧቸው ውሳኔዎች ላይ ትኩረት ሰጥተው ማየት ተገቢ ነው እንላለን፡፡

Attorney general

SOCIETY
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ማይካድራ ላይ የተፈፀመው የጅምላ ጭፍጨፋ በመላው ዓለም ከተፈፀሙ 10 አስከፊ የሽብር ጥቃቶች በርካታ ንፁሃን ዜጎች የተገደሉበት ወንጀል ሆኖ መመዝገቡን ኢንተርፖል አስታወቀ
Ethiopia: Central Bank Blacklists Individuals for Alleged Forex Fraud
Related posts
  • Related posts
  • More from author
SOCIETY

አስጨናቂዋን ሰዓት ወደ ደስታ የቀየረው የኢትዮጵያዊያን የሕክምና ባለሙያዎች ስኬት

August 23, 2025
News

በ2018 ጓደኞቼ ዩኒቨርስቲ ይገባሉ፤ በድህነት ከተማ ሄዶ መማር ይልቻለው ታዳጊ ለቅሶ!

August 22, 2025
SOCIETY

“በጠለምት ወረዳ በዝናብ እጥረት ሳቢያ እንስሳት እየሞቱ ነው፤ ሕዝብ እየተሰደደ ነው”

August 18, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2