Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የጦር ሜዳ የጉዞ ማስታወሻ ከበር ተክላይ – አዲጉዶም
News

የጦር ሜዳ የጉዞ ማስታወሻ ከበር ተክላይ – አዲጉዶም

Ethioreview newsEthioreview news—February 1, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የጀነራሎቹ ጀግንነትና ጓዳዊነት-ከበር ተክላይ – አዲጉዶም !ጁንታው በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቅምት 24 ምሽት 2013 ዓ.ም የፈፀመውን ጥቃት ተከትሎ ፣ በራያ ግንባር ፣ የጋዜጠኞችን ቡድን ለማስተባበርና ለመከላከያ ሚዲያ ለመዘገብ ከስራ ባልደረቦቼ ጋር በከፍተኛ ወኔና ቁርጠኝነት ተሰልፈናል።ኢትዮዽያን የማፍረስ እና የማዳን ትንቅንቁ ቀናት አስቆጥሯል ። በግንባሩ የደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ በቢሶበርና ጨርጨር በተባሉ ቦታዎች ላይ አፍራሹ ሀይል መሽጏል ።

የሞት ሽረት ትግል ከምስራቅ ዕዝ ጋር እያደረገ ስለነበር ፣ በአላማጣ አቅጣጫ ሳይጀመር ለተወሰኑ ቀናት እንድንቆይ አድርጎናል።ይሁን እንጅ በነዚህ ቦታዎች ላይ ሲከላከል የነበረው የጁንታው ኃይል በጀግኖች የምስራቅ ዕዝ አባላት እና በአየር ኃይላችን ከፊሉ ሲደመሰስ ከፊሉ ደግሞ እግሬ አውጭኝ በማለት ፈረጠጠ።ከዚህ በኋላም የደቡብ ዕዝ እና የምስራቅ እዝ በጋራ በአንድ አቅጣጫ መፋለም ቀጠሉ ።እኔም በዚህ ወቅት ነበር የሁለቱን ጀነራሎች ጓዳዊነት፣ጀግንነት፣ቁርጠኝነት፣የውጊያ ጥበብና በሳል የአመራር ሰጭነት ጥበብን በቅርብ ለማየት እድሉን ያገኘሁት ።ጀነራሎቹ የምስራቅ እዝ ዋና አዛዥ ( አይበገሬው ) ሜ/ጀነራል ዘውዱ በላይ እና የደቡብ ዕዝ ዋና አዛዥ ( ነጎድጓዱ ) ሜ/ጄነራል ሰለሞን ኢተፋ ናቸው።

ከሜ/ጀነራል ሰለሞን ኢተፋ ጋር ከቆቦ እስከ በር ተክላይ ድረስ በነበረው የግዳጅ አፈፃፀም ሂደት በተደጋጋሚ የማገኛቸው የነበረ ሲሆን ፤ ከሜ/ጄ ዘውዱ በላይ ጋር ግን የተገናኘነው በርተክላይ የተባለው ቦታ ላይ የጁንታው ምሽግ ከ3ቀናት በኋላ ሲሰበር ነው።በተለይም ሁለቱም ጀነራሎች በርተክላይን አለፍ ብሎ ካለው ተራራ ላይ በማጥቃት ዕቅዶቻቸው ላይ በጋራ ከመከሩ በኋላ ፣ ፊት ለፊት መሆኒን አልፎ ፀሀፍት በተባለ ቦታ ላይ የሚገኘው 3ኛው የጠላት ምሽግ በፍጥነት እንዲሰበር ትዕዛዝ ሰጡ ።ውጊያውን በቀጥታ በቅርብ ርቀት በመሆን በሚመሩበት ወቅት የነበራቸው መተሳሰብ ፣ መከባርና መደማጥ በቃላት ሊገልፁት የሚከብድ ከአንድ ማህፀን የወጡ ወንድማማቾች እስኪመስሉ የሚደንቅ ነበር።አብረው የነበሩ ከፍተኛ አመራሮችም ትዕዛዞችን በመቀበልና በማስፈፀም የነበራቸው ቅንነትና ቁርጠኝነት እጅጉን ይገርማል።በነጋታው ፀሀፍት ላይ የነበረው የጁንታው ምሽግ በተያዘው ዕቅድ መሠረት በ21ኛ ክ/ጦር በሚገርም ጀግንነትና ብቃት ተሰበረ።

May be an image of 2 people, military uniform and outdoors

ከዚህ በኋላ ሁለቱም ጀነራሎች የግንባሩ አስቸጋሪ በሆነው ገርበገው የተባለው ቦታ ላይ የመሸገውን ሀገር አፍራሽ ለመደምሰስ በሚያስችሏቸው የውጊያ ዕቅዶች ላይ ከመከሩ በኋላ ሁለቱም ወደፊት ለመሄድ ተነሱ።ሁለቱም ጀነራሎች በጦር ሜዳ መነፅሮች አካባቢውን በደንብ ከቃኙና ካርታውን አንብበው ከጨረሱ በኋላ የግድ አንዳቸው መቅደም ነበረባቸው። በዚህን ጊዜ ሜ/ጀ ዘውዱ ቆፍጠን ባለ አነጋገር ” ሰለሞን በቃ እኔ ፊት እሄዳለሁ አንተ እዚህ ቆይ ” ብለው ከተራራው ጫፍ ላይ መውረድ ጀመሩ።ነገር ግን ሜ/ጀ ሰለሞን እሺ ብለው አልተቀበሉም ። ”አይደለም ዘውዱ ፣ እኔ ነኝ የምሄድ አንተ እዚህ ቆይ ” አሉና እሳቸውም መንገድ ጀመሩ ። በዚህ ጉዳይ ላይ ‘ እኔነኝ የምቀድም ‘ ፣ ‘ እኔነኝ’ እያሉ ጓዳዊነትና ፍቅር በተሞላበትና ‘ ከአንተ በፊት እኔ ነኝ ቀድሜ መሞት ያለብኝ ‘ በሚል ስሜት ጭቅጭቅ አዘል ንግግር አደረጉና ተግባቡ ። ሁለቱም ከተራራው በፍጥነት መውረድ ጀመሩ። እኛም በቻልነው አቅም ሂደቱን በፎቶና በምስል ለማስቀረት አብረን ቀጠልን።

More stories

«የቁንጥጫ ዲፕሎማሲ» የዲፕሎማሲው መንገድ መቀየር !

August 5, 2021

መልስ የሚሻ ዜግነታዊ ጥያቄ – ሻለቃ ፈይሳ ናኔቻ

May 9, 2021

… ሶርያ ከ 10 ሚሊዮን በላይ የመን 20 ሚሊዮን ህዝብ እንደተራበና እንደተፈናቀለ …

January 29, 2021

የደብረፅዮን የጦርነት ታክቲክ 22

September 12, 2022

በዚህ ወቅት የታዘብኩት ፣ ሁለቱም ጀነራሎች ውጊያው ከተጀመረ ጀምሮ እንደማንኛውም ተዋጊ ኃይል ብርዱና ፀሀዩ እንደተፈራረቀባቸው ከጠቆረ ፊታቸውና ከደረቁ ከንፈሮቻቸው በአይኔ በብረቱ በማየት ተገንዝቤአለሁ።ነገር ግን ምንም አይነት ፈተና ቢገጥማቸውም ያላቸው ጀግንነት ፣እልህ፣የአሸናፊነት መንፈስና ወኔ ከፊታቸው ላይ ይነበባል። ሀሳባቸው ኢትዮዽያ ናት ። እሷ ህልውናዋ ከተረጋገጠ ፣ በቃ እፎይ ይላሉ ። እስከዛው ግን ስለራሳቸው የሚጨነቁበት ደቂቃ የላቸውም ።ሰአታት እየተቆጠሩ ነው ።

ጁንታው ከማይጨው እና ከመቀሌ አቅጣጫ የከባድ መሳሪያ ድብደባ መሆኔና አካባቢው ላይ በማድረግ ወደፊት የገሰገሰው የወገን ሀይል የሎጀስቲክስና የሰው ኃይል ድጋፍ እንዳያገኝ ለማድረግ ያለ የሌለ ኃይሉን መጠቀም ጀመረ ።ይሁን እንጂ በየ10 ደቂቃው ከመሆኒ መግቢያ እስከ ፀሀፍት ባለው አስፓልት ላይ የሚወረወሩት የመድፍ ቁምቡላዎች ፣ ሰራዊታችንንም ሆነ ጀነራሎቻችንን የማስቆም አቅም አልነበራቸውም ።

ስለሆነም ከጥቂት ደቂቃዎች በሗላ ሁለቱም ጀነራለች በፍጥነት ከተራራው ላይ በመውረድ እንደ በረዶ የሚዘንበውን የጥፋት እሳት ከምንም ሳይቆጥሩ መኪኖቻቸውን በማስነሳት ወደፊት ሸመጠጡ – ምሱን ሊሰጡት ።እኛም ጀግንነትንና ቆራጥነት ተጋባብን መሰለኝ ከኋላቸው በመከተል ወደፊት በፍጥነት ተጓዝን።ለተከታታይ 4 ቀናት ሜ/ጀነራል ዘውዱ እና ሜ/ጄ ሰሎሞን ፊት ለፊት በመሆን ውጊያውን እየመሩ እንዳሉ ብናውቅም ፣ ሞርተርና ከዚያ በታች ያሉ የቡድን መሳሪያዎች የሚደርሱበት ቦታ ተጠግተው ስለነበርና እኛም ከዚህ በላይ እንድንጠጋ ስላልተፈቀደልን ሳንገናኝ ቀረን ።

ከ4ቀናት በኋላም የግንባሩ መሪ ሌ/ጀ ባጫ ደበሌ እና የግንባሩ የካባድ መሳሪያዎች አስተባባሪ ሜ/ጄ ዓለምሸት ደግፌ ገርበገው ከሚባለው የፅንፈኛው ወሳኝ ምሽግ ፊት ለፊት በጋራ በተመራው ውጊያ ሞሽጉ ሲሰበር ከነበሩት አመራሮች መካከል አሁንም ሁለቱ ጀነራሎች ሬዲዮዎቻቸውን በመያዝ ያለ እረፍት ሲያስተባብሩ አገኘናቸው። እልህ ፣ ቁጭትና የአትንኩኝ ባይነት ስሜት በፊታቸው ላይ ይንቦገቦጋል ። ያስፈራሉ ።ሁለቱም በቦታው ብዙ አልቆዩም አሁንም መኪኖቻቸውን በማስነሳት እንደ ልማዳቸው ወደፊት ሸመጠጡ – ለቀጣይ የድል ተልዕኮ !እኛም ዕለቱ አስቸጋሪው ምሽግ የተሰበረበት ቀን ስለነበር በኮ/ል ደጀኔ ፀጋዬ የድል መግለጫ ካገኘን በኋላ በፍጥነት ወደ ቆቦ በመመለስ ዜናው ለኢትዮጵያ ህዝብ እንዲደርስ አደረግን።

በማግስቱ እንደተለመደው የውጊያ ቀጣናዎችን በማቆራረጥ ሰራዊታችንና አመራሮቻችን ወደ ሚገኙበት ቦታ ተጉዘን አዲቀይህ የሚባለውን ቦታ እንዳለፍን አዲመስኖ ከሚባለው አካባቢ ደረስን።ይህ ቦታ ጁንታው ከመሸገባቸው ቤተ እምነቶች መካከል የመካነሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሚገኝበት በመሆኑ የጋዜጠኞች ቡድን በአካል እየጎበኘን ሳለ ፣ ሜ/ጄ ዘውዱ እና ሜ/ጄ ሰሎሞን በቅርብ መኖራቸውን ስለሰማሁ ለጋዜጠኞች ቡድን መግለጫ እንዲሰጡ ለማቻቸት ወዳረፋበት ተጓዝኩ ።ሀለቱንም ጀነራሎች ከሌሎች አመራሮች ጋር ለአዲጉደም ትይዩ በሆነ አንድ ጉብታ ላይ አገኘኋቸው።

ቦታው ታላልቅና ሰፋፊ ድንጋዮች የሞላበት ነው።ሜ/ጄ ዘውዱ በላይ ያለምንም ፍራሽ ወይም ምንጣፍ በድንጋዩ ላይ ገደም ብለዋል። ሜ/ጄ ሶሎሞን ኢተፋ ደግሞ አንዱን ድንጋይ ደገፍ ብለው ተቀምጠዋል።ሰላምታ ከሰጠሁ በኋላ ከአጠገባቸው አረፍ ብዬ ስመለከት የሁለቱም ጀነራል መኮንኖች ፊቶች እጅግ ጠቁሯል። ነገር ግን ፈገግታ አይለያቸውም። አይኖቻቸው እጅግ ቀልተዋል ግን አያንቀላፋም – እንደ ንስር በጥልቀት ወደፊት ይመለከታሉ እንጂ።እኔም ይህን ሳይ እንዴት ቃለ ምልልስ እንደማደርግ እያሰላሰልሁ ሳለ ሜ/ጄ ዘውዱ ” ” ሶሎሞን ” ብለው ተጣሩና ” ሂድ ትንሽ እረፍ ” አሉ። ሜ/ጄነራል ሰሎሞን ግን ፍርጥም ብለው በመነሳት ወደታች ከሄዱ በኋላ ካርታቸውን አውጥተው ማንበብና መለካት ጀመሩ ።

ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላም ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ እና ሜ/ጄ አለምሸት ደግፌ አዲመስኖ በተባለው ቦታ ላይ መጡና መግለጫ ሰጡን።ከመግለጫው በኋላም ሁለቱም የእዝ አዛዦች ከግንባሩ መሪ አጭር መመሪያ ተቀብለው ወደፊት ሄዋኔን አልፈው ወደ አዲጉዶም አቅጣጫ እንደ ልማዳቸው መጡ።በነጋታው አዲጉዶም አካባቢ ሌ/ጄ ይመር መኮንንና ሜ/ጄነራል ዘውዱ በላይን እንዲሁም ሌሎች አመራሮችን ሳገኝ ሜ/ጄ ሰለሞንን ግን አላገኘኋቸውም። ምክንያቱም በሄዋኔ አድርገው ወደ ማይጨው በመመለስ ተቆርጦ የቀረውን ኃይል ለመደምሰስ ተመልሰው ነበርና።በዚህ ሁሉ ሁኔታ ፣ የጁንታው የከባድ መሳሪያ ድብደባ ያላንዳች እረፍት እንደ ቀጠለ ነበር ። በዛው መጠን የጀነራሎቹም የውጊያ ስልት ያደገ ስለነበር ላንቃቸውን ለመድፈን ጊዜ አልወሰደባቸውም ።

ም/መ/አ ንጉሴ ውብሊቀርፎቶግራፍ ም/መ/አ ንጉሴ ውብ

መከላከያ ፌስ ቡክ የተወሰደ

  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
OPINION
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
“የእሳት ፖለቲካ” – አዲስ አበባን እየበላ ነው
ሮይተርስ ወደ አዲስ አበባ፤ ጃዋር ማናገር ቅድሚያ ነው፤50 ሰዎችን መርጠዋል፤ መንግስት ቅድሚያ ወደ ማይካድራ ይላል፤
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2