Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የኬሪያና የጃዋር ድብቁ ግንኙነትና አዲሱ የቤት ውስጥ እስር
News

የኬሪያና የጃዋር ድብቁ ግንኙነትና አዲሱ የቤት ውስጥ እስር

Ethioreview newsEthioreview news—March 11, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የቀድሞ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የነበሩት ወ/ሮ ኬሪያ በዋስ መፈታታቸው ተሰምቷል። ፖሊስ ለችሎት እንዳስረዳው ወይዘሮዋ የተፈቱት ቀዳሚ ምርመራ እስኪሰማ ድረስ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ አንቀጽ 28 መሰረት ነው።  

ፋና ችሎቱን ጠቅሶ እንደዘገበው ወይዘሮ ኬሪያ ቀዳሚ ምርመራ እስከሚሰማ ድረስ የሚቆዩት በሰርቪስ ማረፊያ ነው። የህግ ማስከበሩ ሲጀመር ሌሎች ሲሸሹ መቀሌ ሆነው እጃቸውን የሰጡት የቀድሞ አፈ ጉባኤ፤ እጃቸውን ከሰጡ በኋላ ክስ ሳይመሰረትባቸው መቆየቱ ይታወሳል።

ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም እንዴት ወደ መቀሌ ሄዱ?

አፈጉባዔዋ ወደ መቀሌ የሄዱት ከአዲስ አበባ ተገፍተው መሆኑንን ጉዳይን በወጉ ሲከታተሉ የነበሩ ይናገራሉ። ኬሪያ ሃላፊነታቸውን በገዛ ፈቃዳቸው መልቀቃቸውን ከማስታወቃቸው በፊት ከአቶ ጃዋር ጋር ጥብቅ ግንኙነት እንዲመሠርቱ ተደርጎ ነበር።  

ለጃዋር ሳሎን ቅርብ የሆኑ ኬሪያን በተደጋጋሚ እዚሁ ሳሎን እንዳዩዋቸው ምስክርነት ይሰጣሉ። የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ መረጃ የሚቀበላቸው የኦፌኮ ሰዎች እንዳሉት አፈጉባዔዋ ወደ መቀሌ ሊሄዱ ሰሞን በጃዋር ከፍተኛ ግፊት ይደረግባቸው እንደነበር አመራሮቹ ሲናገሩ መስማታቸውን አረጋግጠዋል።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

ጃዋር መሀመድ ለምን ጫና ሊፈጥርባቸው እንደቻለ ሲያስረዱ “ወቅቱ የመንግሥት ፍጻሜ በመሆኑ ወ/ሮ ኬሪያ እጅግ ተፈላጊ ሚና መጫወት እንዳለባቸው በትህነግና በእነጃዋር ታምኖበት ነበር” ሲሉ ይጀምራሉ። አክለውም “ኬሪያ ወደ መቀሌ የመሄድ ብዙም ፍላጎት እንደሌላቸው ሲታወቅ ጃዋር መንግሥት እንደሚቀየር በማሳመን ከፓርቲያቸው መለየት እንደሌለባቸው በማስገንዘብ እንዲሄዱ ገፍቷቸዋል” ብለዋል።

“መንግሥት የመንግሥትነቱን ዕድሜ ጨርሷል” የሚለው ቅስቀሳ በትብብርና በቅንጅት ሲጀመር፣ ጎን ለጎን የትህነግ ሰዎችና አፈቀላጤዎች አጠር ባለ ጊዜ መንግሥትን በኃይል ለማስወገድ ማቀዳቸውን በቃል፤ ወታደራዊ ዝግጅቱን በተግባር እያሳዩና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ጦርነት ለማስነሳት ዕቅድ መኖሩን በአጋሮቻቸው አማካይነት ያስነግሩ እንደነበር ይታወሳል።

ምርጫ መደረግ እንደሌለበት ሲሰብኩ የነበሩት እነ ልደቱ አያሌው ሳይቀሩ በመናበብ “መንግሥት ከመስከረም 30 በኋላ የለም” የሚለውን ዘመቻ ሲያራግቡ ወ/ሮ ኬሪያ በእነ ጃዋር ግፊትና ትዕዛዝ አስፈጻሚነት ወደ ትግራይ አቅንተው መንግሥትን በገሃድ ተቃወሙ። የህገ መንግሥት ተርጓሚ አካል የሆነውን ትልቁን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሥልጣን መልቀቃቸውን ይፋ ሲያደርጉ ጃዋር የሚመራቸው ሚዲያዎች፣ የትህነግ ልሳኖችና በውጭ አገር ያሉ ተከፋይ ሚዲያና ወስዋሾች ዜናውን በስፋት አዳርሰውት ነበር።  

በወቅቱ ወ/ሮ ኬሪያ መቀሌ ተገደው እላፊ መናገራቸው ሲሰማ የትግራይ ቲቪ የመዝናኛ ክፍለጊዜ አዘጋጅቶ ኬሪያ ደስተኛ እንደሆኑ ለማስመለስ ተሞክሮ ነበር። በወቅቱ ጎልጉል በደረሰው መረጃ ግን ኬሪያ ተገደው ትግራይ ከሄዱ በኋላ ደስተኛ አልነበሩም።

በወቅቱ በትህነግ፣ እነጃዋርና ሌሎች ተባባሪዎች አማካይነት መንግሥት በኃይል ሲወገድ የውጭ ማኅበረሰብና መንግሥታትን ቅቡልነት ለማግኘት ወ/ሮ ኪሪያ አስፈላጊና ቁልፍ ሰው በመሆናቸው ነው ወደ ትግራይ እንዲሄዱና እንዲከዱ የተደረጉት የሚሉት የጎልጉል መረጃ ምንጭ፣ ትግራይ ከገቡ በኋላ ህገ መንግሥት እንደተጣሰ፣ በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት ህጋዊ እንዳልሆነ ጠቅስው መረጃ እንዲያሰራጩ ተደርጓል። ይህ ዓለምን የዞረ መግለጫና መረጃ ከተሰራጨ በኋላ መንግሥት በኃይል ሲቀየር የዓለም አቀፍ ተቋማትንና አገራትን ቅቡልነት ለማስገኘት የሕገመንግሥት ተርጓሚው ምክርቤት አፈጉባዔ የነበሩት ወ/ሮ ኬሪያ ተዘጋጅተው እንደነበር የመረጃው ምንጭ የኦፌኮን ከፍተኛ አመራሮች ጠቅሰው ተናግረዋል።

የታሰበው ሳይሆን ቀርቶ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ወዲያው ትህነግን ከድተው እጅ የሰጡት ኬሪያ እነ ስብሃት ነጋ ታስረው እስኪመጡ ድረስ ክስ ሳይመሰርትባቸው መቆየታቸው ይታወሳል። በዚሁ ቆይታቸው ምን መረጃ እንደሰጡና ለህግ ማስከበሩ ዘመቻ የሚጠቅም ግብዓት እንዳበረከቱ በግልጽ የተቀመጠ መረጃ የለም። ዛሬ በዋስ ከላይ በተቀመጠው መሰረት መፈታታቸውን ተከትሎ አንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ተቃውሞ ሲያሰሙ እየታየ ነው።

ጎልጉል ያነጋገራቸው የመንግሥት ኃላፊ ከላይ በተዘረዘሩት ጉዳዮች ላይ መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ እንዳልሆኑ ጠሰው “ተቃውሞ በመረጃና በጭብጥ ላይ መከራከሪያ በማቅረብ ሲሆን አግባብ ነው፤ ከዚያ ውጭ አንድ ነገር ሲሆን በጥቅል መሳደብ፣ ማውገዝ፣ እኔን ስሙኝ ብሎ መወራጨት ህግን መጣስ ብቻ ሳይሆን ንግግር ከማብዛት የሚመጣ የልብ መደፈን ነው” ሲሉ በሰሙት ለጆሮ የሚቀፍ ስድብ ማዘናቸውን አስታውቀዋል። አግባብነት ያለውና መሰረታዊ መከራከሪያ የሚቀርብበት ትችት አስፈላጊ መሆኑንን ጠቅሰው “አሁን አሁን እላፊ መሳደብና እኔ እኔ … የሚል የትህነግ አይነት አመለካከት መግራት አስፈላጊ እየሆነ ነው” ብለዋል።

አንድ የህግ ባለሙያ “ወ/ሮ ኬሪያ አልተፈቱም። ወይዘሮ ኬሪያ ቀዳሚ ምርመራ እስከሚሰማ ድረስ የሚቆዩት በሰርቪስ ማረፊያ ነው። ውጭ ሆነው ክሳቸውን መከታተላቸው ሃጢያት የለውም። ነጻ አልተባሉም። የቤት ውስጥ እስር አይነት ወይም በረጅም ገመድ ማሰር እንደማለት ነው” የሚል አስተያየት ሰጥተዋል። አያይዘውም “በነጻ ቢለቀቁም መንግሥት ምን ያገባዋል? ጣልቃ ገብነት ይቁም እየተባለ እንደገና በፍርድ ቤት ሥራ መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ መጋበዝ አያስኬድም፣ ወይስ ጣልቃ ገብነቱን የምንቃወመው እኛ “ንጹህ ነው” ባልነው ሰው ላይ ሲፍጸም ብቻ ነው” ብለዋል።

በዛሬው ችሎት የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት ወይዘሮ ሕርቲ ምህረተአብ እና የክልሉ መንግሥት አማካሪ የነበሩት ወልደጊዮርጊስ ደስታ፣ እንዲሁም በእነ አባይ ወልዱ የክስ መዝገብ ላይ ከሚገኙ ተከሳሾች ውስጥ አምደማርያም ተፈራ በ30 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ መወሰኑ ተሰምቷል

Via – በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም በዋስ እንዲለቀቁ ተወሰነ
ዶክተር አዲስ አለም ባሌማ፣ አቶ ስብሃት ነጋ፣ አምባሳደር አባይ እና ሌሎችም ተጠርጣሪዎች ማረሚያቤት እንዲወርዱ ታዘዘ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2