Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  law  የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና አመሰራረታቸው
law

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና አመሰራረታቸው

Ethioreview newsEthioreview news—April 6, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

1. መግቢያዜጎች የተለያዩ መብቶችና ነፃነቶች ያሏቸው ሲሆን ከእነዚህ መብቶች መካከል ተደራጅተው መብትና ጥቅማቸውን ማስጠበቅ አንዱ ነው፡፡ ዜጎች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፤ ማህበራዊና ባህላዊ መብታቸውን በመደራጀት መከወን ይችላሉ፡፡ በሀገራችን ህገ መንግስት አንቀጽ 31 ላይ እንደተደነገገው ማንኛውም ሰው ለማንኛውም ዓላማ በማህበር የመደራጀት መብት አለው፡፡ ነገር ግን ለህገ ወጥ ዓላማ መደራጀት ወይም ህገ መንግስታዊ ስርአቱን በህገወጥ መንገድ ለማፍረስ የተመሰረቱ ወይም የተጠቀሱትን ተግባራት የሚያራምዱ ድርጅቶች የተከለከሉ ይሆናሉ፡፡ እንዲሁም በመደራጀት መብት ምክንያት ሌላ ሶስተኛ ወገንን ለመጠበቅ የወጡ ህጎችን ወይም የሌላ ሰውን መብት በሚጥስ ሁኔታ መንቀሳቀስ የማይችልና የተከለከለ ነው፡፡

2. ሲቪል ማህበሰረብ ድርጅቶች ምንነት፣ አይነት እና የህግ ማዕቀፍየመደራጀት መብት ከሚገለጽባቸው መንገዶች መካከል ዜጎች በሙያና በብዙሃን ማህበራት መደራጀት አንዱ ነው፡፡ በሀገራችን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የረጅም ጊዜ ታሪክ ያላቸው ሲሆን ለትርፍ ያልተቋቋሙ ቦጎ አድራጎት ድረጅቶች ከጥንት ጀምሮ በማህበረሰቡ ዘንድ የዳበረ የእርስ በእርስ መረዳጃ ባህላዊ የሆኑ እንደ ደቦ የመሳሰሉ አደረጃጀቶች እንዲሁም እንደ እቁብና እድር ያሉ አደረጃጀቶች ማህበረሰቡ እርስ በእርሱ የሚተጋገዝባቸውና ገንዘብ መቆጠቢያና መበደሪያ መንገዶች ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡ የእርስ በእርስ መረዳጃ ማህበራት ውጭ በኢትዮጵያ መጀመሪያ የተቋቋሙ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የኢትዮጵያ ቀይ መስቀልና የስዊዲሽ ሴቭ ዘ ቺልድረን ሲሆኑ በኋላም እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ1990 መጀመሪያ ጀምሮ በርካታ የሲቪል ማህበራት ተመስርተዋል፡፡

በህገ መንግስቱና ሌሎች ህጎች ለመብቱ የተሰጠው ጥበቃ እንደተጠበቀ ሆኖ የመደራጀት መብት ከሚገለፅባቸው መንገዶች አንዱ የሆኑትን በሙያና ብዙሃን የሚደራጁ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የሚገዛ አዋጅ ቁጥር 621/2001 ወጥቶ ሲተገበር ቆይቷል፡፡ ይህ አዋጅ የመደራጀት መብትን ይበልጥ ከማስከበር አንፃር ገደቦች/ውስንነቶች የነበሩበት በመሆኑ አዋጁ ተሻሽሎ አዋጅ 1113/2011 ሆኖ እንዲወጣ ተደርጓል፡፡ በአዋጅ መሰረት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ቢያንስ ሁለትና ከዚያ በላይ በሆኑ ሰዎች በፍቃደኝነት የሚመሰረት፣ የመንግስት አካል ያልሆነ፣ ለትርፍ ያልተቋቋመ፣ ከማናቸውም የፖለቲካ ድርጅት ያልወገነ እና ህጋዊ ዓላማን ለማሳካት ተመዝግቦ የሚንቀሳቀስ አካል ሲሆን የሞያ ማህበራትን፤ የብዙኃን ማህበራት እና የድርጅቶች ህብረቶችን ይጨምራል፡፡

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሀገር በቀልና የውጭ ድርጅት በሚል በሁለት የሚከፈሉ ሲሆን ሀገር በቀል ድርጅት በኢትዮጵያ ወይም ከኢትዮጵያ ውጭ ህጋዊ ስራ ለመስራት በኢትዮጵያዊያን፤ በኢትዮጵያ ነዋሪ በሆኑ የውጭ ሀገር ዜጎች ወይም በሁለቱም የሚመሰረት ድርጅት ሆኖ መስራቾቹ ሁለትና ከዚያ በላይ መሆን አለባቸው፡፡ የውጭ ድርጅት በውጭ ሀገር ህግ መሰረት የተቋቋመና በኢትዮጵያ ውስጥ ተመዝግቦ የሚንቀሳቀስ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ነው፡፡በሌላ በኩል አገር በቀል ድረጅቶች በአምስት አይነት አደረጃጀት የሚቋቋሙ ሲሆን እነዚህም ማህበር፣ ቦርድ መር ድርጅት፣ የዘለቄታ በጎ አድራጎት ድርጅት፣ የአደራ በጎ አድራጎት ድርጅት እና የበጎአድራጎት ድርጅት ናቸው፡፤

More stories

በኮበለሉት ዶ.ር ፍስሐ እሸቱና ባልደረቦቻቸው ላይ የተመሰረተው ተደራራቢ ክስ

October 15, 2024

የ17 አመት ታዳጊ አዶናይት ይሄይስ ላይ የአስገድዶ መድፈርና የግድያ ወንጀል የፈፀመው የሞት ቅጣት ተወሰነበት

February 19, 2025

የመኪና ሌቦቹ ተፈረደባቸው

April 15, 2022

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ዝርዝር

November 2, 2021

3. የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምስረታ የሲቭል ማህበረሰብ ድርጅቶች አመሰራረት በሚከተሉት መርሆች እንደሚመራ አዋጁ ይደነግጋል፡፡ አነዚህ መርሆችም፤-

• ድርጅቶች ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ሊቋቋሙ መቻላቸው • በድርጅቱ ውስጥ አባል ለመሆን ፍቃደኝነት የግድ ሲሆን ከድርጅቱ በፈለገው ሰአት መውጣት ይቻላል

• አግባብነት ያለውን ህግ መሰረት በማድረግ የአባላት መቀበያ ፎርም ማዘጋጀት • ማንኛውም ሰው መስፈርቱን ካሟላ የድርጅቱ አባል መሆን መብት አለው

• እያንዳንዱ አባል እኩል ድምጽ አለው• ድረጅቶች ለአባላት ትርፍ በማሰብ ሊቋቋሙ ኤችሉም • የድርጅቱ አመሰራረትና ውስጣዊ አሰራር ዴሞክራሳዊ መርሆችን የተከተለ፤ ከአድሎአዊነት የጸዳ፤ ነጻና ገለልተኛ ሊሆን ይገባል፡• ድርጅቱ የሚመራው በመተዳደሪያ ደንቡ ስልጣን በተሰጣቸው አካላት ሙሉ ተሳትፎ በተመረጡሰዎች ነው፤

• ድርጅቱ በመተዳደሪያ ደንቡ ካልሆነ በስተቀር አባላትን ሊቀበልና ሊያሰናብት አይችልም፡፤

3.1. የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምዝገባ እና መስፈርቶችማንኛውም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት የፌደራል መስሪያ ቤት በሆነው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ኤጀንሲ መመዝገብ እንዳለበት በህግ ተቀምጧል፡፡ ለሀገር በቀል ድርጅቶች ምዝገባ በድርጅቱ መስራቾች ሰብሳቢ የተፈረመ ማመልከቻ መቅረብ ያለበት ሲሆን ከማመልከቻው ጋር ተያይዘው መቅረብ ያለባቸው ሰነዶች፤-

• የምስረታ ቃለ-ጉባኤ የመስራቾችን ስምና አድራሻ የያዘ፤

• የመስራቾች መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ኮፒ፤

• የድርጅቱ ስም እንዲሁም አርማ፤• የድርጅቱ አርማና ሊሰራ ያሰበበት የስራ ዘርፍ፤

• የስራ ቦታ፤

• በመስራቾች የጸደቀ መተዳደሪያ ደንብ፤

• የድርጅቱ አድራሻ፡፡ በሌላ በኩል በውጭ ሀገር የተመሰረተ ድርጅት በኢትዮጵያ ለመመዝገብ ከላይ የተዘረዘሩትን ጨምሮ የሚከተሉትን ሰነዶች ማሟላት ይኖርበታል፡• ድርጅቱ መቋቋሙን የሚያሳይ ከተቋቋመበት አገር የተሰጠው በአግባቡ የተረጋገጠ ሰነድ፤

• ስልጣን ያለው የድርጅቱ አካል ድርጅቱ በኢትዮጵያ ውስጥ እንዲሰራ ያሳለፈው በአግባቡ የተረጋገተ ውሳኔ፤

• በአገር ውስጥ ተወካዩ የተሰጠው በአግባቡ የተረጋገጠ የውክልና ስልጣን፤ ከተቋቋመበት ሀገር ስልጣን ባለው አካል የተሰጠ የድጋፍ ደብዳቤ ወይም በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተሰጠ የድጋፍ ደብዳቤ፤

• ከሁለት አመት ላላነሰ ጊዜ የሚተገበር የስራ እቅድ ይዞ መቅረብ የግድ ይላል፡፡ከላይ የተዘረዘሩት ቅደመ ሁኔታዎች አሟልቶ ያቀረበ ሀገር በቀል ድርጅት በኤጀንሲው ማመልከቻውን ባቀረበ በ30 ቀን ውስጥ እና የውጭ ድርጅት የምዝገባ ማመልከቻውን ከስራ እቅድ ጋር ባቀረበ በ45 ቀን ውስጥ ኤጀንሲው መዝግቦ የምስክር ወረቀት መስጠት ይኖርበታል፡፡ የምዝገባ ማመልከቻ አስገብቶ በተባለው ቀን ውስጥ የምስክር ወረቀት ያልተሰጠው ድርጅት ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ቦርድ በ30 ቀን ውስጥ ቅሬታውን ማቅረብ ይችላል፡፡ ቦርዱ ምዝገባው ያለአግባብ የተከለከለ መሆኑን ከተረዳ ምስክር ወረቀቱ እንዲሰጠው ያደርጋል፡፡

3.2. ምዝገባ ውድቅ የሚሆነበት ሁኔታማንኛውም ሰው በማንኛውም አላማ የመደራጀት መብት ያለው ቢሆንም ህግ በመጣስ መደራጀት ክልክል ነው፡፡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከላይ በተቀመጠው መሰረት ምዝገባ ለማድረግ የሚያስፈልጉ ሰነዶችን ይዞ ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ኤጄንሲ ካቀረቡ በኋላ ኤጀንሲው የቀረበለትን የምዝገባ ጥያቄ ከሚከተሉት ምክንያቶች አንዱ መኖሩን ካረጋገጠ ድርጅቱ ያቀረበውን ምዝገባ ውድቅ ሊያደርግ ይችላል፡-

• የቀረበው ማመልከቻ ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የማያሟላ ሆኖ ሲገኝና ይህንንም እንዲያስተካክል የአመልካቹ ተወካይ ተጠይቆ ለማስተካከል ካልቻለ፤

• የድርጅቱ ዓላማ ወይም በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ የተመለከተው የሥራ ዝርዝር ለሕግ ወይም ለሕዝብ ሞራል ተቃራኒ ከሆነ፤

• ድርጅቱ የሚመዘገብበት ስም ወይም ዓርማ ከሌላ ድርጅት ወይም ከማንኛውም ሌላ ተቋም ስም ጋር የሚመሳሰል ከሆነ ወይም ሕግን ወይም የሕዝብን ሞራል የሚቃረን ከሆነ፤

• ድርጅቱ ለምዝገባ ያቀረበው ሰነድ በሐሰት የተዘጋጀ ወይም የተጭበረበረ ከሆነ ሲሆን ከነዚህ ምክንያቶች ኤጄንሲው ምዝገባ መከልከል እንደማይችል በህጉ ላይ ተቀምጧል፡፡ ምዝገባው ውድቅ የተደረገበት ድርጅት በ30 ቀን ውስጥ የጎደለውን ነገር አሟልቶ እንዲያቀርብ ኤጀንሲው ለድርጅቱ በጽሁፍ ማሳወቅ አለበት፡፡ የጎደለውን ነገር አስተካክሎ እንዲቀርብ በጽሁፍ የተሰጠው ድርጅት በተባለው ቀን ውስጥ ለኤጀንሲው ካላቀረበ ምዝገባው ውድቅ ይሆናል፡፡ ምዝገባው ውድቅ የተደረገበት ድርጅትም ቅሬታ ካለው በ30 ቀን ውስጥ ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ቦርድ ቅሬታውን ማቅረብ ይኖርበታል፡፡ ቦርዱ ቅሬታው በቀረበለት በ60 ቀናት ውስጥ ቅሬታውን መርምሮ ውሳኔ መስጠት ይኖርበታል፡፡ አንድ ድርጅት በማታለል ወይም በማጭበርበር የምዝገባ የምስክር ወረቀት አግኝቶ ከሆነ ይኸው በኤጀንሲው ሲረጋገጥ ቦርዱ ድርጅቱ እንዲፈርስ ሊወስን የሚችል ሲሆን በተሰጠ ውሳኔ ቅሬታ ያለው ድርጅት የቦርዱ ውሳኔ በደረሰው በ30 ቀናት ውስጥ ይግባኙን በመስራቾቹ አማካኝነት ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ማቅረብ ይችላል።

3.3. የድርጅቶች የምዝገባ ውጤትከላይ የተጠቀሱትን ቅድመ ሁኔታ አሟልቶ የተመሰዘገበ ድርጅት ህጋዊ ሰውነት ይኖረዋል፣ መብትና ግዴታ ይኖረዋል፡፡ በስሙ ውል መግባት፣ ክስ ማቅረብ እና መከሰስ ይችላል፡፡ እንዲሁም ለስራ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን አሟልቶ ህጋዊ የስራ መስክ ላይ መሳተፍ ይችላል፡፡


  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
“3000 ሌሊቶች” Andwalem Arage
በሱዳን እንቅፋትነት የኪንሻሳው ድርድር ያለ ውጤት ተጠናቀቀ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
law

ህገወጥ የውጭ ምንዛሪ ወንጀል የፈጸሙ 123 ተጠርጣሪዎች የባንክ ሒሳብ ታገደ

September 20, 2025
law

እነ ቀሲስ በላይ በሙስና ወንጀል ሊፈርድባቸው እንደማይገባ ጠቅሰው ያቀረቡት ይግባኝ ውድቅ ሆነ

July 26, 2025
law

የአዲስ አበባ የከንቲባ ፅ.ቤት ፕሮቶኮልን ጨምሮ 12 ተከሳሾች በሌብነት ተከሰው ተፈረደባቸው

July 23, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2