Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  በሀገራችን በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለውን ማንነት ላይ ያተኮረ ግድያን በተመለከተ ከኢዜማ የተሰጠ መግለጫ
News

በሀገራችን በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለውን ማንነት ላይ ያተኮረ ግድያን በተመለከተ ከኢዜማ የተሰጠ መግለጫ

Ethioreview newsEthioreview news—April 2, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ባለፉት ሦስት ዓመታት በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች በተለይም በኦሮሚያ እና በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ዜጎች በማንነታቸው እየተለዩ በአሰቃቂ ሁኔታ በተደጋጋሚ ጥቃት ሲደርስባቸው ቆይቷል። በአጣዬና በሌሎችም አካባቢዎች ተመሳሳይ ድርጊቶች የተፈፀሙ ሲሆን ሁሉም ዜጎች በሕይወት የመጠበቅ እና በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች በነፃነት የመንቀሳቀስ፣ ኑሮ የመመስረት እና የመሥራት ሰብዓዊ መብት እንዳላቸው በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት የተደነገገ መብት መሆኑ ይታወቃል።

ነገር ግን ይህ መብት ከምንም ነገር በላይ ሊከበርላቸው የሚገቡ ዜጎች በተደጋጋሚ በተከሰቱት ማንነት ተኮር ጥቃቶች ውድ ሕይወታቸውን ሲያጡ፣ አካላቸው ሲጎል እና ከቤት ንብረታቸው ሲፈናቀሉ ቆይተዋል። ንፁሃን ላይ የሚደርሰው ማንነት ተኮር ጥቃት መብታቸውን የሚጥስ ብቻ ሳይሆን አሰቃቂ እና ዘግናኝ በሆነ ሁኔታ የሚፈፀም መሆኑ እጅግ ልብ የሚሰብር እና በሰብዓዊ ፍጡር የሚፈፀም መሆኑን ለማመን የሚያስቸግር አድርጎታል።

በያዝነው ሳምንት መግቢያም በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ባቦ ገንቤል ወረዳ በቦኔ ቀበሌ በአካባቢው የሚኖሩ ዜጎች ላይ ማንነት ላይ መሰረት ያደረገ ጥቃት ተፈፅሞ ብዙ ንፁሃን ዜጎች መተኪያ የሌለው ሕይወታቸውን እንዲያጡ እና ለትውልዶች ከኖሩበት ቀያቸው እንዲፈናቀሉ ሆነዋል። ከዚህ ከጥቃት ከተረፉ ዜጎች ቃል ለመረዳት እንደተቻለው ጥቃቱ ከመፈፀሙ በፊት አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ አካባቢው እንዲያስተዳድሩ ኃላፊነት ከተሰጣቸው የቀበሌና ወረዳ አስተዳዳሪዎች ማስፈራሪያ ደርሷቸው ነበር። ይህም፣ ጥቃቱ ሆን ተብሎ እና ታቅዶበት ለመፈፀሙ እና እና የአካባቢው ደህንነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ያለባቸው ሰዎች ተሳትፎ አንዳለበት ማሳያ ነው። እስከአሁን በዜጎች ላይ በተደጋጋሚ የተፈፀሙ ለከት ያጡ ኢሰብዓዊ የወንጀል ድርጊቶች የተፈፀሙት በታወቁ ውሱን በሆኑ ቦታወች መሆናቸው በክልሉም ሆነ በፌደራል መንግሥት በኩል ችግሩን የሚመጥን ትኩረት ላለማግኘቱ አመላካች ነው።

More stories

“ዛሬ እኛ ነን ነገ ደግሞ እናንተ ትሆናላችሁ” ቀዳማዊ ኀይለ ሥላሤ

May 5, 2023

ሰላም፣እርጋታና የዜጎች ደህንነት ለኢትዮጵያውያን ፍትሃዊ እድገት ወሳኝ ናቸው – በአሜሪካ የህዝብ ዲፕሎማሲ አማካሪ ምክር ቤት

May 17, 2021

ትግራይ በራሷ ልጅ አንደበት ምስክርነት

June 28, 2021

“ኑ ! የወልቃይት ምድር ነጻ ወጥቷል” በስደት የሽሽት ኑሮ ላይ የነበሩ አማሮች ወደ ወልቃይት ጠገዴን ሰቲት ሁመራ ተመለሱ

June 17, 2021

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በንፁሃን ዜጎቻችን ላይ በደረሰው ግድያ እና መፈናቀል የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ በጥቃቱ ወዳጅ ዘመዶቻቸውን ላጡ እና ለመላው ኢትዮጵያዊያን ልባዊ መፅናናትን ይመኛል።

በተደጋጋሚ የተከሰቱት ማንነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች እንደሀገር እንዳንረጋጋ እና ዜጎች ከፍርሃት ተላቀው የዕለት ተለት ሕይወታቸውን እንዳይመሩ እንቅፋት ከመሆኑም በተጨማሪ ከውጭ ለሚመጣብን ሉዓላዊነታችን እና የሀገር ደህንነታችን ላይ ላነጣጠረ አደጋ ተጋላጭ አድርጎናል።

እነዚህ ጥቃቶች የሚፈጽሙት በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ያሉም ሆነ ከመንግሥት በተፃራሪ የቆሙ አካላት በድርጊቱ ማሳካት የሚፈልጉት ዓላማ በሀገራችን ውስጥ እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዳይፈጠር እንቅፋት መሆን ሲሆን ከዚህ ከፍ ሲልም የማያባራ የእርስ በርስ ብጥብጥ በማስነሳት ሀገራችን ለማፍረስ ነው። ይህን ዓላማቸውን ለማሳካት በሀገራችን ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ማኅበረሰቦች መካከል የእርስ በርስ ግጭት ሊያስነሱ የሚችሉ ጥቃቶችን ሆን ተብሎ በተቀነባበረ መንገድ እየፈፀሙ ይገኛሉ። ይህን ዕኩይ የፖለቲካ ዓላማቸውን ለማሳካት እስከመጨረሻው እስኪሸነፉ ድረስ ምንም ነገር ከማድረግ ወደኋላ እንደማይሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ አሁን ግልፅ ሆኗል።

ይህንን እና ሀገራችን ያለችበትህ አጠቃላይ ሁኔታ ከግምት በመክተት የሚከተሉት እርምጃዎች እንዲወሰዱ አጥብቀን እንጠይቃለን።

  1. የዜጎችን በሕይወት የመኖር መብት፣ ሰላም እና ደህንነት መጠበቅ የመንግሥት ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ በመሆኑም በዜጎች ላይ ጥቃት እየተፈፀመባቸው ባሉ አካባቢዎች ያለው የመንግሥት መዋቅር በጥልቅ ተፈትሾ በየደረጃው የሚገኙ ኃላፊዎች ላይ ተጠያቂነትን የሚያሰፍን የእርምት እርምጃ መንግሥት በአስቸኳይ እንዲወስድ እንጠይቃለን።
  2. ጥቃት ለደረሰባቸው ዜጎች መንግሥት ተገቢውን ክትትል፣ ካሳ እና መልሶ ማቋቋሚያ እገዛ በአስቸኳይ እንዲደረግላቸው፤ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችም ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ውስጥ አስፈላጊውን ርብርብ እንዲያደርጉ እንጠይቃለን።
  3. ጥቃት በተደጋጋሚ የደረሰባቸውን እና ሊደርስባቸው የሚችል አካባቢዎችን በመለየት በአስቸኳይ በፌደራል መንግሥት የፀጥታ አካላት ቁጥጥር ስር በማድረግ እና በአካባቢው ያሉ ጥቃት ፈፃሚዎች ላይ የማያዳግም እርምጃ እንዲወሰድ እና በእነዚህ አካባቢዎች አስተማማኝ እና ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የደህንነት ዕቅድ እንዲቀረፅ እና በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲደረግ እንጠይቃለን።
  4. ስጋት ያለባቸው አካባቢዎች የፌደራል መንግሥት ከሚሠራዉ የሰላም እና የደህንነት ማስጠበቅ ሥራ በተጨማሪ በአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመተባበር የማኅበረሰብ አቀፍ ሰላም እና ደህንነት ሥራ የሚሠራ ኃይል የማደራጀት፣ የማሠልጠን እና የማስታጠቅ ሥራ እንዲሠራ እንጠይቃለን።
  5. የፌደራል መንግሥት የፀጥታ መዋቅር በኃይል እጥረት ምክንያት ማስፈር በማይችልባቸው ቦታዎች ላይ ማኅበረሰቡ እራሱን መከላከል የሚያስችለው አደረጃጀት እና ትጥቅ እንዲኖረው እንዲደረግ፤

የተፈጠሩ ችግሮችን እና አጠቃላይ የሀገሪቱን ሉዓላዊነት እና ደኅንነት በተመለከተ ኢዜማ በቀጣይ በየደረጃው ካሉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተመሳሳይ ማንነትን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች በዘላቂነት ማስቆም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት የሚያደርግ ይሆናል። ኢዜማ በእነዚህ ውይይቶች ችግሩን በመሰረታዊነት ለመፍታት እንዲቻል ዝርዝር ማብራሪያ የሚጠይቅ ሲሆን በየጊዜው በተፈፀሙት ጥቃቶች ውስጥ አስተዋፅዖ ያደረጉ አካላት ተጠያቂ የሚሆኑበት ውሳኔ እንዲሰጥም ክትትል ያደርጋል። ለሰላም እና የዜጎች ደህንነት መረጋገጥ ማድረግ የሚችለውንም ኃላፊነትም ይወጣል፡፡

የችግሩን ጥልቀት እና ሊኬድባቸው የሚገባ መንገዶችን የሚያብራራ እና ችግሩን የሚመጥን ግብረመልስ እንዲሰጥ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የፌደሬሽን ምክር ቤት፣ ለፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት፣ ለሰብዓዊ መብት ኮሚሽን አዘጋጅተን የምንልክ መሆኑን እና አፈፃፀሙን የምንከታተል ይሆናል።

በሀገራችን ማንነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ የሚቆመው ሁሉም ዜጎች በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች በዜግነታቸው በዕኩልነት የታዩበት የፖለቲካ ሥርዓት ሲመሰረት ብቻ እንደሆነ እና ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሀገራችን ያለችበትን አስቸጋሪ ሁኔታ በመረዳት የምናደርጋቸው እንቅስቃሴዎች በሙሉ የበለጠ ችግሩን የሚያባብስ እና ወደ እርስ በርስ ግጭት የሚከተን እንዳልሆነ እንድናረጋግጥ እና ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት የሚፈጽሙ ኃይሎች መጠቀሚያ እንዳንሆን የአደራ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)
መጋቢት 24 ቀን 2013 ዓ.ም

POLITICS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ደመቀ መኮንን – የድሆችን ጭፍጨፋ መኖሪያቸው ያደረጉና ሃላፊነታቸውን ባልተወጡ ላይ አርምጃ ይወሰዳል
ወሎ አግላይ ወይስ አቃፊ? ዶ/ር ሁሴን አዳል መሐመድ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2