Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የቀይ ሽብር አዋጅ እንዲወጣ ምክንያት የሆነው መመሪያ
News

የቀይ ሽብር አዋጅ እንዲወጣ ምክንያት የሆነው መመሪያ

Ethioreview newsEthioreview news—April 25, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

አብርሃም ተወልደ

 የዛሬው ቀን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የተከሰቱ አያሌ ምሁራንና ወጣቶች ቀርጥፎ የበላው “ቀይ ሽብር” አዋጅ እንዲታወጅ ምክንያት የሆነው “የብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ አብዮት መመሪያ” ይፋ የተደረገበት ዕለት ነበር።ቀኑ ሚያዝያ 12 / 1968 ዓ.ም ነበር ።ወታደራዊ መንግስት “ደርግ” የብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ አብዮት መመሪያ አድርጎ ያወጀበት ቀን፡፡

ከቻይና አብዮት የተኮረጀው ይህ ቀመር በሶስተኛው ዓለም የሶሻሊስት ለውጥን ለማምጣት ፍቱን ነው ተብሎ የታመነበት ሲሆን፤ መሰረታዊ ይዘቱም “በወዝአደሩ፣ በአርሶአደሩና በተራማጅ ንዑስ ከበርቴ አብዮታዊ ጥምረት የሰፊው ህዝብ ጠላቶች ተብለው የተለዩትን “ፊውዳሊዝምን” “ኢምፔሪያሊዝምንና” “ቢሮክራሲያዊ ካፒታሊዝምን” መደምሰስ ነው፡፡

ይህ ዓላማም ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ በመስከረም ወር 1980 እውን ሆነ።ለተመለከተውና ነገሩን ላጤነው ሁሉ እውር ድንብሩን “ኢትዮጵያ ትቅደም!” ብሎ ሰኔ 1966 የተነሳውን ደርግ እዚህ ጣራ ላይ ለመድረስ ምን ያህል አስደናቂ ረጅም ጉዞ እንደተጓዘ ግልጽ ነው፡፡

More stories

“ዛሬ እኛ ነን ነገ ደግሞ እናንተ ትሆናላችሁ” ቀዳማዊ ኀይለ ሥላሤ

May 5, 2023

ሰላም፣እርጋታና የዜጎች ደህንነት ለኢትዮጵያውያን ፍትሃዊ እድገት ወሳኝ ናቸው – በአሜሪካ የህዝብ ዲፕሎማሲ አማካሪ ምክር ቤት

May 17, 2021

ትግራይ በራሷ ልጅ አንደበት ምስክርነት

June 28, 2021

“ኑ ! የወልቃይት ምድር ነጻ ወጥቷል” በስደት የሽሽት ኑሮ ላይ የነበሩ አማሮች ወደ ወልቃይት ጠገዴን ሰቲት ሁመራ ተመለሱ

June 17, 2021

የብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ አብዮት ከታወጀበት በኋላ ቀጣዩ ርምጃ የፕሮግራሙ አስፈጻሚ አካል የሆነውን ጊዜያዊ የህዝብ ድርጅት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ማደራጀት ሆነ።የአዋጁ መታወጅ እና የጽህፈት ቤቱ መቋቋም ወቅቱ “አበይት ተግባር ሰፊውን ህዝብ ማንቃት እና ማደራጀት ነው” እያሉ ይወተውቱት ለነበሩት እንደ “መኢሶን” ላሉ የግራ ክንፍ ሀይሎች ትልቅ ድል ነበር።

ጽህፈት ቤቱን እንዲመራ የተሰየመው አስራ አምስት አባላት ባሉት ኮሚሲዮን የሊቀ መንበርነቱን ስፍራ ከመያዝ አንስቶ ግልጽ የሆነ የበላይነት የነበረው “መኢሶን” የጽህፈት ቤቱን መዋቅር ድርጅታዊ አቅሙን ለማፈርጠም ተጠቀመበት።ጽህፈት ቤቱ በተቋቋመ በጥቂት ወራት ውስጥ የድርጅት ቁሳዊ ሆነ ሰብአዊ ኃይል ቀላል የማይባል እመርታ አሳየ፡፡

በተጓዳኝም ከተሞችን ለመቆጣጠር ቁልፍ የሆነውን “የከተማ ልማት እና ቤት ሚኒስቴር” በመቆጣጠሩ እና በ1968 መጨረሻ ላይ በተደረገው የቀበሌ ምርጫ ደጋፊዎቹን ለማስመረጥ በመቻሉ ትልቅ የመደላደል ስሜት ተሰማው።ስለሆነም የመንግስት ስልጣን ወደ ሰፊው ህዝብ ተወካዮች የሚተላለፈው እንደ “ኢሕአፓ” በሐሳብ ግትርነት ደርግን በመጋፈጥ ሳይሆን ደርግ የፈጠረው መዋቅር በዘዴ በመጠቀም ነው ብሎ ቢያስብ እምብዛም አይገርምም፡፡

ይሁን አንጂ ደርግ “የመኢሶንን” ስሌት ሳይረዳው ይቀራል ብሎ ማሰብ የፖለቲካ የዋህነት ነበር።ደርግ ሌላው ሁሉ ነገር ቢቀር በፖለቲካ ስልጣን ጉዳይ ቆቅ መሆኑን ከአንዴም ሁለቴ አሳይቷል።በዚያ ላይ ደግሞ የሁለት አመት የአብዮት ትምህርት ቤት “የግራ ክንፉን ማርክሲስታዊ” ዘይቤን ድርጅቱ እንዲጨብጥ አስችሎታል።ስለዚህም ነገሩ “ብልጥ ለብልጥ” ሆነና የጉልበት ፍተሻውን አይቀሬ አደረገው።አይቀሬ እየሆነ የመጣው ድራማም በአብዛኛው በ1969 ዓ.ም መጀመሪያ ተጀምሮ በዓመቱ ማብቂያ ላይ ተጠናቀቀ፡፡

የደርግ እና የኢሕአፓ ክረት

በመጀመሪያ ደርግ ለዘብተኛ የሆነውን የግራ ክንፍ አጋር በማድረግ የእድገት እመርታው ባስደነገጠው እና ማዕቀብ የሌለው ተቃውሞ ባበገነው “በኢሕአፓ” ላይ ዘመተ።በዚህ ረገድ አያሌ የሰራተኛውና የብዙሃን ድርጅቶች የ“ኢሕአፓ”ን መፈክር አንግበው ሰልፍ የወጡበት የ1968ቱ “ሜይ ዴይ” በዓል ወሳኝ ወቅት ነበር።በዚያን ወቅት ደርግና የግራ ክንፍ አጋሮቹ ኢሕአፓ እስካለ ድረስ እነሱ መኖር እንደማይችሉ በቅጡ ተረዱ።ከዚያን ጊዜ ጀምሮም ሁለቱ ባላንጣዎች ሰይፋቸውን መሳል ጀመሩ።በክረምቱ ወራት የታየው አንጻራዊ ዝምታም ዶፍ ያዘለ ዳመና ነበር፡፡

ሰው ሰራሽ የሆነው የሽብር ክረምቱ ጅማሮ

የተፈጥሮ ክረምት ሲያባራ ሰው ሰራሹ የሽብር ክረምት መስከረም ላይ ጀምሮ ዓመቱን ሙሉ ቀጠለ።ደርግ የኢሕአፓ ታጋዮችንና ደጋፊዎችን በመግደል ኢሕአፓ በደርግ አቀንቃኞችና ባለሟሎች ላይ የሽምቅ ጦርነት በማወጅ ፉክክር ተያያዙ።ከሁለቱም ወገን ታሪኩን ለመጻፍ (እንደ እውነቱ ከሆነ ግን ግድያውን ማን ጀመረው ብሎ መጠየቅ) መሳሪያቸውን ስለው ከተፋጠጡ ሁለቱ ባላንጣ ሰራዊቶች መካከል የመጀመሪያውን ተኩስ ማን ከፈተ ብሎ የመጠየቅ ያህል ነው።በዚህም ሆነ በዚያ ፍልሚያው አይቀሬ እየሆነ መጥቷል።አንዴ ከተጀመረ ወዲያም እያሻቀበ እንጂ እየለዘበ አልሄደም፡፡

የመገዳደሉ አበይት ምዕራፎች ከሞላ ጎደል ይህን ይመስሉ ነበር።መስከረም 13 ኢሕአፓ እንደ ቀንደኛ ጠላት ያየው የነበረው በደርጉ አንደኛ ምክትል ሊቀ መንበር በሌተናል ኮሎኔል መንግስቱ ሃይለማሪያም ላይ የግድያ ሙከራ አድርጎ ሳይሳካላት ቀረ።እንዲያውም ከሙከራው ያመለጠው የመንግስቱ ቡድን በአንድ በኩል ለራሱ ተወዳጅነት ለማትረፍ በሌላ ወገን ደግሞ “የኢሕአፓን” ክስረት ለማሳየት ተጠቀመበት፡፡

በዚያው ወር ውስጥ “ኢሕአፓ” “የመኢሶን” አመራር አባል እና የህዝብ ድርጅት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ባልደረባ የነበረውን ዶክተር ፍቅሬ መርዕድን ሰንጋ ተራ መኪና ውስጥ ቁጭ ብሎ ሚስቱን በመጠበቅ ላይ ሳለ አድፍጦ በመግደል የመጀመሪው አብይ ሰላባ አገኘ።በድርጊቱ በጣም የተበሳጨውም ደርግ “አንድ አብዮታዊ ህይወት በሺህ ፀረ ህዝቦች ህይወት ይመነዘራል” የሚል መግለጫ ካወጣ በኋላ የኢሕአፓ አባሎችንና ደጋፊዎችን በገፍ በማሰርና ከታሰሩትም መካከል መርጦ በመረሸን የበቀል ርምጃውን ወሰደ፡፡

ደርግ በአባላቱ ላይ የወሰደው “አብዮታዊ ርምጃ”

የመንግስት የማጥቃት ርምጃ አፍቃሬ “ኢሕአፓ” ተብለው በተፈረጁት የደርግ አባላት ላይ ጥር 26 ቀን 1969 “አብዮታዊ ርምጃ” ከተወሰደባቸው በኋላ ተጠናክሮ ቀጠለ።በተለይ በሚቀጥሉት ወራት አከታትሎ በወሰዳቸው ሁለት አሰሳዎች በህቡዕ ገብተው የነበሩትን አንዳንድ “የኢህአፓ አባላት” መሪዎችን በተለይ ቀንደኛ አባላቱን ከመግደሉና ከማሰሩ ባሻገር ሲቪሉን ትጥቅ በማስፈታት መቅኔውን ሰለበው።

እነዚህ “የአሰሳና ድምሰሳ” ርምጃዎች “በቀይ ሽብር” ስም በኋላ ለታወጀው ዘግናኝ የታሪክ ምዕራፍ መቅድም መሆናቸው ነው።“ቀይ ሸብር” በዋነኛነት ያነጣጠረው “በኢሕአፓ” ላይ ሲሆን፤ ቀስ በቀስ ግን “የኤርትራ ህዝባዊ አርነት ግንባር እና ህዝባዊ ወያኔ አርነት ትግራይ” ብሎም ከደርግ ጎራ ያፈነገጠው “መኢሶን” ሳይቀር የሽብሩ ዒላማ ሆኑ፡፡

ሌሎች የግራ ክንፍ ቡድኖች ኢሕአፓን በክፉ አይን እንዲመለከቱት ካደረጋቸው ምክንያቶች አንዱ ተሸቀዳድሞ ራሱን “የላብ አደሩ ፓርቲ ነኝ” ብሎ በማወጁ ነው።የሁሉም አላማ በወቅቱ ገንኖ የነበረው “ማርክሲስታዊ ሌኒናዊ” አስተሳሰብ የሌኒን ጽንሰ ሀሳብ ማዕከል የነበረውን ግንባር ቀደም “የሰራተኛው መደብ ፓርቲ” ሆኖ ለመገኘት ነበር፡፡

በሰራተኛው ማህበራት እና በህዝባውያን ድርጅቶች የኢሕአፓን ያህል ሰርገው ለመግባት ያልቀናቸው እነዚህ ቡድኖች ኢሕአፓን “የጅብ ችኩል ቀንድ ይነክሳል” ብለው አጣጣሉት።በእነሱ ስሌት የፖለቲካ ፓርቲ ባህል ባይተዋር በሆነባት ኢትዮጵያ የወዝ አደሩ ግንባር ቀደም ፓርቲን ተጣድፎ ማወጅ ወይ ድንቁርናን ወይ ስግብግብነትን አመላካች ነበር።ስለዚህም ይመስላል በኋላ የኢትዮጵያ ማርክሲስት ሌኒኒስት ድርጅቶች ህብረትን (ኢማሌድኀ) ከፈጠሩት ከእነዚህ ፀረ ኢሕአፓ ከነበሩት የግራ ክንፍ ቡድኖች መካከል አንዳቸውም ቢሆኑ ራሱን ፓርቲ ብሎ ያልሰየመው።

ከስማቸው እንደምንረዳው የመረጡት ስያሜ “ንቅናቄ” ፣ “ሊግ” ፣ “ትግል” ፣ “ድርጅት” ወይም “ሰደድ” ነበር።ሐቀኛ ግንባር ቀደም ፓርቲ ሊመሰረት የሚችለው ሰፊው ህዝብንና ተራማጅ ኃይሎችን ያለመታከት በማንቃት እና በማደራጀት ነው ብለው በአጽንኦት ተከራከሩ።ኢማሌድኀን በየካቲት 1969 ያቋቋሙት ወደዚህ የመጨረሻ ግብ አስተማማኝ በሆነ መንገድ ለመድረስ ነበር፡፡

አዲስ ዘመን ሚያዝያ 17/2013


    POLITICS
    FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
    የልጅ እንዳልካቸው መኮንን የጠቅላይ ሚኒስትርነት ሹመትና የተማሪዎች አመጽ
    መንግሥታችን ሆይ! ስምህን የተሸከሙ ተቋማትን ፈትሽልን -ዳግላስ ጴጥሮስ
    Related posts
    • Related posts
    • More from author
    News

    ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

    April 26, 2026
    News

    “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

    April 26, 2026
    News

    ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

    April 13, 2026
    Load more
    Read also
    News

    ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

    April 26, 2026
    WORLD

    ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

    April 26, 2026
    News

    “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

    April 26, 2026
    WORLD

    አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

    April 26, 2026
    WORLD

    የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

    April 26, 2026
    WORLD

    የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

    April 26, 2026
    Load more
    Recent Posts
    • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
    • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
    • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
    • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
    • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
    • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
    • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
    • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
    • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
    • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
    • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
    • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
    • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
    • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
    • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
    Social networks
    FacebookLikes
    X TwitterFollowers
    PinterestFollowers
    InstagramFollowers
    YoutubeSubscribers
    VimeoSubscribers
      VOE
      The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

      MENU

      NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
      © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
      • CONTACT
      • INTERVIEW
      • law
      • ECONOMY
      • Home demo times
      • ያበደው
      • VOE VIDEO
      • ENGLISH PAGE
      • Home Demo default 2