Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ማጣራቱ ሱዳን የተሰደዱ ዜጎችን እንደሚያካትት አስታወቀ፤ መንግስትና አማራ ክልል በማይካድራ ጉዳይ ተኝተዋል
News

ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ማጣራቱ ሱዳን የተሰደዱ ዜጎችን እንደሚያካትት አስታወቀ፤ መንግስትና አማራ ክልል በማይካድራ ጉዳይ ተኝተዋል

Ethioreview newsEthioreview news—May 17, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የማይካድራን ጭፍጨፋ የመጀመሪያ ሪፖርት ካደረገ በሁዋላ የሚከተለው አካሄድ በበርካቶች ዘንድ ጥያቄ ውስጥ እየገባ ነው። ያለ በቂ ምክንያት የማይካድራው ጭፍጨፋ የጥቅል ሪፖርቱ መዘገየት እየነጋገረ ባለበት በአሁኑ ሰዓት ኮሚሽነሩ ጫፍጫፉን ሲወራ የነበረውንና ኢትዮ 12 በተደጋጋሚ ስታስገነዝብ የነበረውን ጉዳይ ይፋ አውጥተዋል። መንግስትና አማራ ክልል በማይካድራ ጭፍጨፋ ጉዳይ ዘግይተዋል ይባላሉ።

የሰብአዊ መብት ኮሚሽን “የግፍ ደረጃ መዳቢ” – የማይካድራ ምርመራ ላይ ደባ እየተሰራ መሆኑ ተሰማ፤ ኮሚሽኑ ምላሽ ከለከለ

ኮሚሽነሩ ዶክተር ዳንኤል በቀለን ጠቅሶ ሪፖርተር ” … በትግራይ ክልል ተፈጽመዋል የተባሉትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለማጣራት የሚደረገው ምርመራ በርካታ ኢትዮጵያውያን ተጠልለው የሚገኙበትን ሱዳን ይጨምራል” ሲል ዘግቧል። ዶክተር ዳንኤል ከኢትዮ ቲዩብ ጋር ባካሄዱት ቃለ መልልስ በተለያዩ አገራት ሩዋንዳና ኮንጎን ጠርተዋል፣ የዘር ማጥፋት ወነጀል የፈጸሙ ወንጀለኞች ከሰላማዊው ስደተኛ ጋር ተቀልቀለው በስደት ወደ ጎረቤት አገሮች እንደሚሄዱ ደጋገመው አስታወቅው ነበር።

በሌላ ዘገባ ደግሞ ” በማይካድራው ጭፍጨፋ የትህንግ አመራሮች ቀጥተኛ ትዕዛዝ ስለመኖሩ መረጃ የለም ” ሲሉ በአርት ቲቪ በአርትስ ወቅታዊ ፕሮግራሙ ላይ ቀርበው ተናግረው ነበር። ቀደም ሲል ወነጀል ሰርቶ ከስደተኞች ጋር ተቀላቅሎ የመኮብለለ ባህሪ መኖሩንና ወንጀለኞች በዚህ መልኩ ራሳቸውን እንደሚሸሽጉ እንዳስረዱት ሁሉ በአርት ቲቪ ቀርበው ሁለት እርስ በርስ የሚጣላ አስተያየት ሰጥተው ነበር።

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

በውቀቱ የቲቪው ጠያቂ በግልጽ በሚታወቅ ደረጃ የተፈጸመ ወንጀልን ይህን ያህል ማቆየቱ ለመን አስፈለገ የሚል ይዘት ያለው ጥያቄ ነበር የሰነዘረው። እሳቸውን በተደረገው ማጣራት ክልሉን የሚያስተዳድረው አካል የፖሊስ፣ የሚሊሻና ሳምሪ በሚባል አደረጃጀት መፈጸሙን ማረጋገጣቸውን፣ ሪፖርቱም ይህንን አረጋግጦ ማቅረቡን ካስታወሱ በሁዋላ ” ትዕዛዙ በቀጥታ ከትህነግ ስለመውረዱ የሚታወቅ ነገር የለም” የሚል መልስ ነበር የሰጡት። በዚህ ንግግራቸው መሰረት “ሱዳን ተሸሽገዋል” የሚባሉትን ወገኖች በማካተት አዲስ ሪፖርት ሊወጣ እንደታሰበ በጓሮ ሲነገር የነበረውን ጉዳይ እውን እንደሚሆን ፍንጭ ሰጠተው ነበር።

Related stories   ወደ ድርደር ? ከታንክ ወደ አህያ የወረደው ትህንግ በማን ሊወከል?

በመጨረሻ – ኮሚሽነር ዳንኤል እንደ ትህነግና ኦነግ ዓይነት የሽግግር መንግስት ጥያቄ እንዳላቸው አመላከቱ

ሪፖርተር በእሁድ ዘገባው እሳቸውኑ አነጋግሮ እንዳሰፈረው በትግራይ ተፈጸመ የተባለውን የሰብአዊ መበት ጥፈቶች ለማጣራት የሚደረገው ምርመራ ሱዳን ድርረስ እንደሚደርስና የምርመራው አካል ሊሆን እንደሚችል ተመልክቷል። በአጭር ጊዜ፣ በሺህ የሚቆጠሩ ዜጎች የተጨፈጨፉበት፣ በዝግጅትና እቅድ የተከናወነ፣ አጥፊዎቹ የሚታወቁበት፣ በጥፋቱ መተን በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው ማይካድራ፣ የተቸፈቸፉት ሰዎች በስም የሚታወቁ፣ በአድራሻ የሚለዩ ሆነው ሳለ እንደዚህ ለመከዳደን መሞከር በሌሎች አካባቢ የተፈጸሙ ወነጀሎችን ሕዝብ እኩል እንዳያወግዝ እንቅፋት እንደሆኑበት በርካቶች እየተቀሱ ነው። ሪፖርተር በዘገባው እንዲህ ያሉትን ጉዳዮች አጥርቶ በዘገባው ባያካትትም ሃላፊውን ጠቅሶ ምርመራው ወደ ሱዳንም እንደሚዘልቅ ማረጋገጫ ሰጥቷል።

መንግስትና የአማራ ክልል መስተዳድር፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ አክቲቪስት ነን የሚሉ አካሎች በማይካድራ ጉዳይ መፋዘዝ በማሳየታቸው ምን አልባትም የመጀመሪያው ሪፖርት ሊቀለበስ እንደሚችል ስጋት የገባቸው አሉ። በየትኛውም አካባቢ የተፈጸሙ ወንጀሎች እንዲመረመሩ መደረጋቸው አግባብ ሆኖ ሳለ የማይካድራውን ግልጽ ጭፍጨፋ ለማለሳለስ መሞከር ከምን የመነቸ እንደሆነ ለበርካቶች ግልጽ አይድለም። ኮሚሽነሩም ቢሆኑ በየጊዜው እርስ በርሱ የሚቃረን መረጃ መስጠታቸውን ገለልተኛ ወገኖች አልወደዱላቸውም። ዶክተር ዳንኤል ሲኖሩበት የነበረችው ሁለተኛ አገራቸው እንግሊዝ እንዳለቸው ” የሽግግር መንግስት ይቋቋም” የሚል ይዘት ያለው ሪፖርት ማቅረባቸውም አይዘነጋም።

Related stories   የኢትዮዽያ የቁርጥ ቀን ልጅ “ስለአባይ እውነቱን እንካችሁ” – መካ አደም አሊ

የሪፖርተር ዘገባ እንዳለ ሙሉውን ከታች ያንብቡ።

ሰላሳ አባላት ያሉት የምርመራ ቡድን በቅርቡ ሥራ ይጀምራል ተብሏል

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ መብቶች ተቋም ጋር በመሆን፣  በትግራይ ክልል ተፈጽመዋል የተባሉትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለማጣራት የሚደረገው ምርመራ በርካታ ኢትዮጵያውያን ተጠልለው የሚገኙበትን ሱዳን ሊጨምር እንደሚችል ተገለጸ፡፡

ሁለቱ ተቋማት በመጋቢት ወር 2013 ዓ.ም. አጋማሽ ከመንግሥት የሕግ ማስከበር ዘመቻ በኋላ፣ በትግራይ ክልል ተፈጽሟል የተባለውን የመብት ጥሰት በጋራ ለማጣራት ስምምነት ላይ መድረሳቸው የሚታወስ ነው፡፡

ከሁለቱም ወገን ከእያንዳንዳቸው ስድስት የመርማሪ አባላትን ያካተተ የባለሙያዎች ቡድን በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ወደ ተመረጡ የትግራይ ክልል አካባቢዎች እንደሚያመራ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

ስምምነቱ ከተደረገ ጀምሮ የመርማሪ ቡድኑ አባላት ለምርመራ የሚያስፈልጉ የቅድመ መረጃ ማሰባሰብ፣ የቦታ ልየታ፣ የምርመራ ሥልቶችን መለየትና የትራንስፖርት ሁኔታዎች ላይ ሲመክሩ መቆየታቸውን ዋና ኮሚሽነሩ አስረድተዋል።

ከ12 የመርማሪ ቡድኑ አባላት በተጨማሪ የሕግ፣ የሥርዓተ ፆታ፣ የደኅንነትና የትርጉም ባለሙያዎችን ጨምሮ የምርመራ ቡድኑ 30 ያህል አባላት ሊኖሩት እንደሚችል ዳንኤል (ዶ/ር) ገልጸዋል።

ዋና ኮሚሽነሩ የምርመራውን ነፃነትና ገለልተኝነት ለማረጋገጥ ሲባል የመርማሪ ቡድኑ አባላት የሚሄዱበትን ቦታና አካባቢ ከመጥቀስ ቢቆጠቡም፣ እንዳስፈላጊነቱ ምርመራው በሱዳን የተጠለሉ ኢትዮጵያዊያንንም ሊያካትት እንደሚችል ግን ጠቁመዋል።

ምርመራውን ለማከናወን ሦስት ወራት እንደሚያስፈልግ ገልጸው፣ ካለው ሁኔታ አኳያ ከእዚያም በላይ ሊጨምር እንደሚችል አስታውቀዋል።

የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽነር ሙሳ ፋኪ መሃማት ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጋር በመጋቢት ወር ባደረጉት ውይይት፣  የአፍሪካ ኅብረት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በትግራይ ክልል ተፈጽሟል በተባለው የመብት ጥሰት ምርመራ ለመሳተፍ ፍላጎት ማሳየቱ ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጂ ከአፍሪካ ኅብረት በኩል ምንም ዓይነት ጥያቄ እንዳልቀረበላቸው ዳንኤል (ዶ/ር)  ተናግረዋል፡፡

‹‹የኢትዮጵያ መንግሥት ምርመራው እንዲከናወን በተስማማው መሠረት፣ በምርመራ ወቅት እንቅፋት እንዳይፈጠር ከፌዴራልና ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር መልካም ፈቃድ አግኝተናል፤›› ብለዋል።

በትግራይ ውጊያ ከተቀሰቀሰበት ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ፣ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንና ተመድ የትግራይ ክልልን የሰብዓዊ አያያዝ ሁኔታ በቅርበት ሲከታተሉ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ቀደም ሲልም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በማይካድራና በአክሱም ከተማ አካሄድኩት ባለው ገለልተኛ ምርመራ፣ በርካታ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መፈጸማቸውን እንዳረጋገጠ ማስታወቁ አይዘነጋም፡፡

በመንግሥት አነሳሽነት ላለፉት ሁለት ወራት ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽንና ከፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ በተውጣጡ አባላት የተቋቋመ የምርመራ ቡድን፣ በትግራይ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አቶ ፈቃዱ ፀጋ ግንቦት 2 ቀን 2013 ዓ.ም. በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተናግረው ነበር፡፡ በተለይም በአክሱም ከተማ የተከናወነውን የመጀመርያ ምዕራፍ የምርመራ ውጤት ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ይፋ ማድረጉ ተዘግቧል፡፡

በትግራይ ክልል በአክሱም ከተማ መንግሥት በጥቅምት ወር ከጀመረው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ጋር በተገናኘ 99 ሰዎች በኤርትራ ወታደሮች፣ በሕወሓት ኃይሎችና በመከላከያ ሠራዊት ውጊያ ሰበብ መገደላቸውን ማረጋገጡ ይታወሳል፡፡


  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
    by Ethioreview news
    April 26, 2026
    ቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የእኛ ሰው በጋዛ
ማዕድን ቀጣዩ የኢትዮጵያ ጉሮሮ – “የሕዝብ ሃብት ለሚያባክኑ ዝምታ የለም” ታከለ ኡማ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2