ከትግራይ ክልል በስምንት መኪናዎች ተጭኖ በህገ ወጥ መንገድ ሊወጣ የነበረ 800 ኩንታል የዕርዳታ እህል አዲ ጉደም ኬላ ላይ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሰተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
በድርጊቱ የተሳተፉ ተጠርጣሪዎችን በህግ ጥላ ስር አድርጎ እያጣራ እንደሚገኝም ኮሚሽኑ ገልጿል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሰተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መንግስትአብ የማነ ለኢቢሲ እንደገለጹት፤ በክልሉ ለስብዓዊ ድጋፉ የመጣውን የእርዳታ እህል ከተረጂው ሰው ጎሮሮ ቀምተው ለግል ጥቅማቸውና ብልፅግናቸው ሲሯሯጡ የነበሩ ነጋዴዎች ናቸው፡፡
ከእነዚህ ሰዎች ጀርባ የነበሩ እነማን እንደሆኑ ፖሊስ በምርመራ እያጣራ ይገኛል። በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፀጥታና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር የማነ ገሰሰው በበኩላቸው ተደራጅተው እህልን ከዚህ አከባቢ በመግዛት ወደ ተለያዩ ቦታዎች በመውሰድ እጥረት በመፍጠር በትግራይ ረሃብና ችግር እንዲፈጠር የሚያደርጉ አካላት መኖናረቸውን ገልጸዋል፡፡
የወንጀል አፈጻጸሙ በተደራጀ መንገድ መሆኑንም የገለጹት ረዳት ኮሚሽነሩ፤ በዚህ ህገ ወጥ ድርጊት ውስጥ በየዋህነት የሚሳተፉ ባለሞያዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉም አሳስበዋል፡፡ ከዚህ በፊት በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረው ሶስት ሺህ ኩንታል የእርዳታ ዕህል መያዙን የገለጸው ፖሊስ በወንጀል ድርጊቱ የተሳተፉ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ሆነው ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡
እንደ ኮሚሽነሩ ገለጻ፣ ከዚህ የከፋ ችግር ስለሌለ ህብረተሰቡ በንቃት መሳተፍ ይኖርበታል፡፡ ከህገ ወጥና ስግብግብ ነዳዴዎች በስተጀርባ ያለ ማንኛውም አካል ከህግ ተጠያቂነት እንደማያመልጥ ማወቅ ይኖርበታል ብለዋል፡፡ የመቀለ ከተማ ጊዜያዊ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ግዛው ሐጎስ በበኩላቸው፣ ይህ ህገ ወጥ ተግባር በመጀመሪያው እርዳታ አሰጣጥ ላይ መከሰቱን ጠቅሰው በሁለተኛው ዙር ላይ ይሄ እንዳይደገም በጥብቅ ቁጥጥር እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






