ቀደም ሲል መንግስት እያለ የአሜሪካ መንግስት ከሽብረተኞች መዝገብ ውስጥ ያልፋቀውና በቅርቡ ፓርላማ ከኦነግ ሸኔ ጋር አሸባሪ ብሎ የሰየመው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ትህነግ፣ ሃያ ሁለት ዓላማውን የማይቀበሉ የአመራር አባላትን መግደሉና ሃያ ያሚሆኑትን ማገርቱ ተገለጸ።
“የተበተኑ የአሸባሪው የሕወሓት ርዝራዦች እስከ አሁን 22 የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አባላትን ገድለዋል፤ 20 የሚሆኑትን አግተዋል” ሲል ያስታወቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ ነው።

የተበተኑ የአሸባሪው የሕወሓት ርዝራዦች በተለያዩ የትግራይ ክልል አካባቢዎች እስከ አሁን ድረስ ብቻ 22 የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር አባላት መግደላቸውን ፣ ከዚህ በተጨማሪ 20 የጊዜያዊ አስተዳደሩ አባላት መታገታቸውን እና 4 የአስተዳደሩ አባላት ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸው ለሕክምና ሆስፒታል መግባታቸውን ስፍራና የስራ ሃላፊነት ጠቅሶ ይፋ አድርጓል።
“እየታገልኩ ያለሁት ለትግራይ ህዝብ ነው የሚለው አሸባሪው ሕወሓት ይልቁንም የክልሉን ሃብት እያወደመ እንዲሁም በክልሉ መረጋጋትን ለማምጣት የሚሰሩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ አባላትን እየገደለና እያገተ” ነው ሲል መረጃው አስታውቋል።
በትግራይ የሰብአዊ ዕርዳታ በወጉ እንዳይዳረስና በነጻነት እንዳይሰራጭ ህወሃት በየስርቻው እየተሹለከለከ እክል መፍጠሩን፣ ሰላማዊ ዓላማውን የማይደግፉትን አካላት መግደሉን በመጥቀስ የክልሉ ምክትል አስተዳዳሪ መናገራቸው ይታወሳል። ህወሃት ይህን ቢያደርግም የውጭ ሚዲያዎችና የመብት ተቆርቋሪዎች መረጃውን አይጠቀመኡበትም።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






