Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ከተሞች የሽብር ጥቃት ለመፈፀም የተዘጋጀ የሽብር ቡድን ተያዘ፤ ምስላቸው ይፋ ሆኗል፤ ትህነግ “ክብሪት” የተባለ ገዳይ ቡድን አቋቁሟል
News

በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ከተሞች የሽብር ጥቃት ለመፈፀም የተዘጋጀ የሽብር ቡድን ተያዘ፤ ምስላቸው ይፋ ሆኗል፤ ትህነግ “ክብሪት” የተባለ ገዳይ ቡድን አቋቁሟል

Ethioreview newsEthioreview news—May 10, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በአዲስ አበባና በአንዳንድ የኦሮሚያ ከተሞች የተቀናጀ የሽብር ጥቃት ለመፈፀም አቅደው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የሽብር ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደህንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ፡፡

የደህንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ በአዲስ አበባና በአዳንድ የኦሮሚያ ከተሞች ሁከት፣ ሽብርና ትርምስ በመፍጠር ድብቅ የፖለቲካ አጀንዳቸውን ለማሳካት በሚንቀሳቀሱ የውጭ እና የውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች የሚደገፉ የሸብርተኞቹ የህወሓትና የሸኔ ቡድን አባላት በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ ሴራ ወጥነው ወደ እንቅስቃሴ ለመግባት በዝግጅት ላይ እንዳሉ በጋራ ግብረ ኃይሉ በተደረገባቸው ጥብቅና የተቀናጀ ክትትል በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ይህን እኩይ የጥፋት ሴራ ለመፈጸም ከውጭ በተለያዩ አካላት በሚደረግላቸው የገንዘብና የሎጅስቲክስ ድጋፎች ተልዕኮ ተቀብለው ሲንቀሳቀሱ የነበሩት የሸብርተኞቹ የህወሓትና የሸኔ ቡድን አባላት ከከባድ እስከ ቀላል የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን ከመሰል ጥይቶች፣ ቦምቦችና ተቀጣጣይ ቁሶች ጋር ለጥቃት ሊጠቀሙባቸው ያዘጋጇቸው ቢሆንም፤ የታቀደውን የጥፋት ተልዕኮ ማክሸፍ መቻሉን መግለጫው አትቷል።

መግለጫው አክሎም ለሽብርተኞቹ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያና በሌሎችም አካባቢዎች ጭምር የተለያዩ ሀገራት የገንዘብ ኖቶች በህገወጥ መንገድ ሊተላለፉ እንደነበር ጠቁሞ፥ በተደረገ ጥብቅ ክትትልና ፍተሻም ለጥፋት ተልዕኮ መፈፀሚያቸው ሊጠቀሙበት የነበረ ከ305 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላር እና ከ2 ሚሊየን በላይ የኢትዮጵያ ብር መያዙን አስታውቋል፡፡

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

መግለጫው እንዳብራራው ይህንን የጥፋት ተግባር ለመፈፀም ቀደም ሲል ትግራይ ድረስ ታጣቂዎቹን መልምሎ በመላክ ከሽብርተኛው የህወሓት ቡድን ስልጠና እንዲወስዱ በማድረግ በንፁሃን ዜጎች ላይ ብሄር ተኮር ጥቃቶችን ሲፈፅም የቆየው የአሸባሪው የሸኔ ቡድን የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ጨምሮ የገንዘብና የሎጅስቲክስ ድጋፎችን ሲያገኝ እንደቆየና በቡድኑ ላይ የመንግስት ፀጥታ አካላት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እየወሰዱት ባለው ተከታታይ እርምጃ እየተዳከመና ከባድ ኪሳራ እያጋጠመው መምጣቱን ተከትሎ መሰረተ ልማቶችን እንዲያወድሙ እንዲሁም በታዋቂ ሰዎች፣ በከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችና በዜጎች ላይ በተደራጀና በተጠና መንገድ ግድያ እንዲፈፀሙ አባ ቶርቤ በሚል የሰየማቸውን የከተማ ክንፍ አሸባሪዎች ወደ ተለያዩ ከተማዎች አሰማርቶ ነበር ብሏል፡፡

RELATED POST

የደህንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል አገር ለማተራመስ በህቡዕ የተደራጁ በርካታ ግለሰቦችን ከነመዋቅራቸውና መስሪያዎቻቸው በቁጥጥር ስር አዋለ፤

የደህንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል አገር ለማተራመስ በህቡዕ የተደራጁ በርካታ ግለሰቦችን ከነመዋቅራቸውና መስሪያዎቻቸው በቁጥጥር ስር አዋለ፤

በተጨማሪም በውጭ በተለያዩ ሀገራት ሆነው ይህንን ህቡዕ አደረጃጀት ሲያስተባበሩ እንዲሁም…

Keep reading
by Ethioreview news May 10, 2021May 11, 2021

ለእነዚህ የሽብር ቡድኖች የተለያዩ የጦር መሣሪያዎችን፣ ቦምቦችን፣ ለፍንዳታ የሚውሉ ተቀጣጣይ ቁሶችን እንዲሁም ሰነዶችን በስውር ለመስጠት ሲያጓጉዙ የነበሩ በርካታ የቡድኑ ተጠርጣሪ አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጋራ ግብረ ኃይሉ በመግለጫው አመላክቷል፡፡

ከተጠርጣሪዎች መካከልም አብዲሣ ጣፋ ቆጮልቴ እና ኤብሣ ተረፋ ቶኮሣ የተባሉት ግለሰቦች ከአማራ ክልል ሁመራ አካባቢ በኮድ ሁለት የታርጋ ቁጥር A70977-አ.አ ሚኒባስ መኪና የውስጥ አካል የተለያዩ የጦር መሳሪዎችንና ጥይቶችን ሰግስገውና ደብቀው መዳረሻቸውን ምዕራብ ኦሮሚያ አድርገው በደሴ በኩል አዲስ አበባ ሊገቡ ሲሉ ለገጣፎ ላይ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጿል።

በተመሳሳይ አርጆ አለማየሁ ዋቆ የተባለች የሸኔ ቡድን አባል ሶላር የተገጠመላቸው ዓለም አቀፍ የሳተላይት ስልኮችን በሞያሌ በኩል በማስገባት ወደ ተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች በድብቅ ለማሰራጨት ስትሞከር ቡራዩ ከታ ላይ በቁጥጥር ስር መዋሏን የጠቆመው የጋራ ግብረ ኃይሉ መግለጫ፥ ራቢራ ዊርቱ ሞሲሳ፣ ደረጄ ዱጋሳ ሆርዶፋ እና ወንደሰን መግራ ታደሰ የተባሉ ሌሎች የሽብር ቡድኑ አባላትም ተጨማሪ የሳተላይት ስልኮችን ከአዳማ ወደ አዲስ አበባ ለማስገባት ሲሞክሩ በነበረው ሚስጥራዊ ክትትል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቅሷል፡፡

ሸብርተኛው የሸኔ ቡድን በተደራጀና በተጠና መንገድ ግድያ እንዲፈፅሙ አዲስ አበባና በአንዳንድ የኦሮሚያ ከተሞች ያሰማራቸው የአባ ቶርቤ ቡድን አባላት ተመሳስለው ጥቃት የሚፈፅሙባቸው የመከላከያ ሰራዊት የቀድሞ ደንብ ልብሶችንና እና የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ጭምር በድብቅ ሲጓጓዙ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን መግለጫው አትቷል።

አበራ ሙለታ፣ለሊሳ አዳሙ፣ አበራ ጌታ፣ ሙሌ ስዩሜ እና አብርሃም አቡ የተባሉ የቡድኑ አባሎችና የድርጊቱ ተዋናዮች እንዲሁም አሽከርካሪውና ረዳቱ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን መግለጫውም ጠቁሟል፡፡

የሽብር ቡድኑ በጅማ ከተማ ጥቃት ለመፈጸም ስምሪት የሰጣቸው ኢያሱ ለማ፣ ካሊድ ሰይድ፣ አብደላ አባ በላይ፣ ሰይፉ በላይ እና ነጋሳ ኬኔሳ የተባሉ ተጠርጣሪዎችም ከታጠቋቸው የእጅ ቦምቦችና እና ሽጉጦች እንዲሁም ከሌሎች የጥፋት ተልዕኮ መፈጸሚያ ቁሶች ጋር መያዛቸውንም ነው ያመላከተው፡፡

በተለያዩ የውጭ ሀገራት የሚኖሩና ለአሸባሪው የሸኔ ቡድን የገንዘብና የሎጅስቲክስ ድጋፎች የሚያደርጉ ኢትዮጵያውያንና ትውልድ ኢትዮጵያውያን መኖራቸውን ያመላከተው የደህንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይሉ፥ እነርሱም ጀምበሩና አበበ አሜሪካ፤ ገመቹ፣ አብደላ እና ተርፋ አውስትራሊያ ዱጋሳ ኖርዌይ እንዲሁም ቶለሺ ታምሩ ወይም ገቢሴ፣ ገመቹ አቦዬ፣ ለማ ረጋሳ ወይም ቢቂላ እና ጃራ ቱለማ ኬንያ እንደሚኖሩም አውስቷል፡፡

እነዚህን የሽብር ቡድኑን እንቅስቃሴ እየደገፉ ያሉትን በድምሩ 15 ተጠርጣሪዎችን ማንነት በማጣራትም ለህግ ለማቅረብ ከወዳጅ ሀገራት ጋር እየተሰራ መሆኑን ገልጾ፥ በሀገር ውስጥ እስካሁን የቡድኑን የሽብር እንቅስቃሴ ለመግታት በተወሰደው እርምጃ የቡድኑን የከተማ ህዋስ አባላትን ጨምሮ 71 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል ብሏል፡፡

መግለጫው አያይዞም ለሽብር ቡድኑ የገንዘብ ድጋፍ ሲያደርጉ የነበሩ የ80 ተጠርጣሪ ግለሰቦች የገንዘብ ስርዓት እንዲቋረጥ የተደረገ መሆኑን እያሳወቀ፥ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የቡድኑ ዋና ዋና የገንዘብ አስተላላፊ ተብለው የተጠረጠሩ 6 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቋል፡፡

ሌሎችንም በህግ ተጠያቂ የማድረግ ስራ እየተሰራ መሆኑን አመላክቷል፡፡

ከአሸባሪው የሸኔ ቡድንና ከሌሎች ፀረ-ሰላም ሃይሎች ጋር በመቀናጀት ሀገር የማፍረስ ተልዕኮ ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረው የሽብርተኛው የሕወሓት ቡድን ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በኢፌዴሪ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሰሜን ዕዝ አባላት ላይ የፈፀመውን የሀገር ክህደት ወንጀል ተከትሎ፥ መንግስት በወሰደው የህግ ማስከበርና የህልውና ዘመቻ የቡድኑ ቁልፍ አመራሮች እርምጃ ሲወሰድባቸውና ገሚሶች ደግሞ እጃቸውን በሰላማዊ መንገድ ሲሰጡ ጥቂት የታጠቁ የቡድኑ ሃይሎች በተንጠባጠበ መልኩ በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች እንደሚንቀሳቀሱም ነው የገለጸው፡፡

ቡድኑ የተወሰደበትን ተከታታይ እርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ “ክብሪት” የሚል መጠሪያ የሰጠውን ገዳይ ቡድን በክልሉ ዋና ዋና ከተሞችና በአዲስ አበባም ጭምር ለማሰማራት መሞከሩንም አትቷል፡፡

በአሜሪካ የሚኖሩ ጀኔራል ፍስሃ ማንጁስ ካህሳይና ወዲ ምጉላት የተባሉ ግለሰቦች በሆላንድ የሚኖሩ ተክላይ እና አታክልቲ፣ እንግሊዝ የሚኖረው ታከለ፣ ስዊድንና ደቡብ ሱዳን የሚኖሩት ተስፋይ ንጉስና ሰይፈ አምባዬ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ሽብርተኛውን የሕወሓት ቡድን በገንዘብ የሚደግፉ መሆናቸው በማስረጃ የተረጋገጠ መሆኑን በመግለጽ የጋራ ግብረ ኃይሉ ግለሰቦቹን በህግ ተጠያቂ የማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩንም ነው ያስታወቀው፡፡

በሀገር ውስጥ ሆነው ለቡድኑ የገንዘብና የሎጅስቲክስ ድጋፎችን ሲያደርጉ የነበሩ 32 የቡድኑ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም እና በቡድኑ ለሽብር ድርጊቱ ሊውሉ የነበሩ የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች፣ የሬዲዮ መገናኛዎች እና ሌሎች ተቀጣጣይ ቁሶችም መያዛቸውን ጠቁሟል፡፡

እነዚህ ሽብርተኛ ቡድኖች ድብቅ የፖለቲካ አጀንዳቸውን ለማሳካት ሀገሪቱን ወደ ሽብርና ትርምስ ውስጥ በማስገባት የህዝቡን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ሴራ ወጥነው ለመንቀሳቀስ እየሞከሩ ቢሆንም የደህንነትና የፀጥታ አካላት ከህዝቡ ጋር በቅንጅት በመስራት ሴራቸውን አስቀድሞ ማክሸፍ መቻሉን የጋራ ግብረ ሃይሉ ገልጿል።

የሸኔና የህወሓት ሽብርተኛ ቡድን አባላት በመንግስት ጸጥታ ሀይሎች እየተወሰደባቸው ባለው ተከታታይ እርምጃ፥ በርካታ የቡድኑ አባላት መደምሰሳቸውንና መያዛቸውን እንዲሁም ለሽብር ተልዕኮ የሚጠቀሙባቸው የተለያዩ የጦር መሣሪያዎች፣ የእጅ ቦምቦች፣ ለፍንዳታ የሚውሉ ተቀጣጣይ ቁሶችና ሰነዶች መያዛቻውን አስታውቋል።

ይህን ተከትሎም የሽብር ቡድኖቹ ከፍተኛ ኪሳራና የስነልቦና ጫና ውስጥ መግባታቸውን መግለጫው አንስቷል፡፡

የጋራ ግብረ ኃይሉ የውስጥና የውጭ ጸረ ኢትዮጵያ ኃይሎች ከመቼውም ጊዜ በላይ ተቀናጅተው ሀገሪቱን ወደ ለየለት ትርምስ ለመክተትና ለማፍረስ እየሰሩ ቢሆንም፥ በርካታ ሴራዎችን አስቀድሞ በማወቅ ማክሸፍ መቻሉንና የትኛውም ሴራ ከመንግስት እንዲሁም ከደህንነትና ጸጥታ አካላት እይታ የተሰወረ አለመሆኑንም አስታውሷል፡፡

ሀገራችን ኢትዮጵያ በያዝነው ወር መጨረሻ ላይ ሀገራዊ ምርጫ ለማከናወን እንዲሁም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት ለማካሄድ ከፍተኛ ዝግጅት እያደረገች ባለችበት በአሁኑ ጊዜ በአንዳንድ የውጭ ሀይሎች በቀጥታ ከሚደርስባት ጫና ባሻገር፤ ከተመቻቸው በጥቂት ተላላኪዎቻቸው የሸኔና የህወሓት ሽብርተኛ ቡድኖች ጥቃት በመሰንዘር ካልተመቻቸው በህቡዕ የተለያዩ አጀንዳዎችን በመፍጠር ሀገሪቱ ወደ ትርምስ እንድትገባ የተለያዩ እኩይ ሴራዎች እየተጠነሰሱ መሆናቸውን ህዝባችን ሊገነዘብ ይገባል ብሏል የጋራ ግብረ ኃይሉ በመግለጫው፡፡

በመሆኑም ህዝባችን ሰላሙንና ደህንነቱን ለመጠበቅ እንዲሁም የሀገሪቱን ብሄራዊ ጥቅም ለማረጋገጥ ሴራዎቹን በማክሸፍ ለአፍታም አይን በማያስከድን ስራ ላይ የተሰማሩ የመረጃና ደህንነት እንዲሁም የጸጥታ ተቋማትና አካላትን የተቀናጀ እንቅስቃሴ በመደገፍ እያደረገ ላለው ትብብር የጋራ ግብረ ኃይሉ ላቅ ያለ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡

ተመሳሳይ ሀገር የማፍረስ እኩይ ሴራዎችን በማክሸፍ በኩል እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችን በቀጣይ ለህዝቡ የማሳወቅ ስራው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን መግለጫው አረጋግጧል፡፡

[jetpack_subscription_form show_subscribers_total=”false” button_on_newline=”false” custom_font_size=”16px” custom_border_radius=”0″ custom_border_weight=”1″ custom_padding=”15″ custom_spacing=”10″ submit_button_classes=”” email_field_classes=”” show_only_email_and_button=”true”]

    NEWS
    FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
    ዐቃቤ ሕግ በአክሱም ደረሰ የተባለውን ጥፋት መርመሮ ይፋ አደረገ፤ አነጋጋሪ አሃዞችና የጥፋቱ መንስኤዎች ይፋ ሆኑ
    “አቡነ ማቲያስ የሰጡት መግለጫ የግላቸው እንጂ የቅዱስ ሲኖዶስ ወይም የቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ አይደለም”
    Related posts
    • Related posts
    • More from author
    News

    ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

    April 26, 2026
    News

    “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

    April 26, 2026
    News

    ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

    April 13, 2026
    Load more
    Read also
    News

    ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

    April 26, 2026
    WORLD

    ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

    April 26, 2026
    News

    “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

    April 26, 2026
    WORLD

    አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

    April 26, 2026
    WORLD

    የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

    April 26, 2026
    WORLD

    የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

    April 26, 2026
    Load more
    Recent Posts
    • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
    • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
    • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
    • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
    • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
    • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
    • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
    • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
    • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
    • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
    • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
    • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
    • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
    • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
    • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
    Social networks
    FacebookLikes
    X TwitterFollowers
    PinterestFollowers
    InstagramFollowers
    YoutubeSubscribers
    VimeoSubscribers
      VOE
      The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

      MENU

      NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
      © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
      • CONTACT
      • law
      • INTERVIEW
      • ያበደው
      • ECONOMY
      • Home demo times
      • VOE VIDEO
      • ENGLISH PAGE
      • Home Demo default 2