በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጆች በወዳጅነት አደባባይ በመገኘት የብልፅግና ፓርቲን ወክለው ለህዝብ ተወካዮች እና ለአዲስ አበባ ምክር ቤት ከሚወዳደሩ እጩ ተወዳዳሪዎች ጋር ትውውቅ ማድረጋቸው ተገለጸ።
በመርሐግብሩ የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር አብርሃም በላይ፣ የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሀፍታይ ገብረ እግዚአብሄርን እና በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩ የትግራይ ክልል ተወላጅ የብልፅግና ፓርቲ ደጋፊዎችና አባላት ተገኝተዋል ።
የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት ብልጽግና ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን ከዳር እስከ ዳር በማቀፍ በጋራ ሀገር የሚያስቀጥል ፓርቲ ነው ብለዋል ።
የትግራይ ህዝብ ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን ኢትዮጵያን በመገንባት እና ዛሬ ላይ በማድረስ ትልቅ ሚና እንደነበረው ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል ።ከለውጡ በፊት በተለያየ መንገድ በተፈጠሩ ክፍተቶች የትግራይ ህዝብ በብዙ መልኩ ተጎጂ ነበር ያሉት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ አሁንም የትግራይ ህዝብ ዳር ተመልካች እንዲሆን የሚሹ ሃይሎች አሉ፤ ያለንበት ምዕራፍ ግን እውነት ከሀሰት እየተለየ የሚወጣበት ወቅት ነው ብለዋል።ለሁሉም ነገር ሰላም ወሳኝ በመሆኑ ሰላምን የሚያደፈርስን ማንኛውም እንቅስቃሴ በጋራ መመከት እንደሚገባም ጠቁመዋል ሲል የአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ዘግቧል።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች














