“ሠራዊታችን በስነ ልቦና ፣ በትጥቅ ፣ በሎጀስቲክስ ፣ በሰው ሀይል የተሟላ ዝግጁነት ላይ የሚገኝ በመሆኑ ፣ ትዕዛዝ ሲሰጠው አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ በሚያስችል ተጠንቀቅ ላይ ሆኖ እየተጠባበቀ ይገኛል” የሚለው መግለጫ ማለዳ ተሰጠ። አስከትለው አጅግ በተለሳለሰ ቋንቋ “ሁሉ ከግምት በማስገባት መንግሥት አስፈላጊውን ሁሉ ነገር በተገቢው መንገድ ያደርጋል” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታወቁ። ተከትሎም አማራ ክልል በይፋ ማጥቃት መጀመሩን አስታወቀ።
የኦሮሚያ ክልል መንግስት የጸጥታ ኃይል ህወሓትን የከፈተውን ወረራ ለመመከት እግዳጅ ማዕከል መሰማራቱ የተሰማው ከክልሉ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ነው።የቢሮ ኃላፊው አቶ ጌታቸው ባልቻ “የክልሉ ጸጥታ ኃይል በትግራይ ክልል ሕግ የማስከበር ዘመቻውን ተቀልቅሏል” ብለዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የሲዳማ ክልል በሃሰት የተሰራጨውን ዜና ለማጋለጥ በሚመስል ሃይሉን መላኩ ተሰምቷል።
የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ደስታ ሌዳሞ ፥ ዛሬ ምሽት የሲዳማ ክልል ልዩ ሀይል አባላት ይሸኛሉ ሲሉ በይፋ ተናግረዋል። በመንግስት መገናኛ እንደታየው የሲዳማ ክልል ልዩ ሃይል ግንባሩን ሊቀልቀል ያቀናል። ይህ ከተባለ በሁውላ ነው። አሁንም በሰከነ መንገድ ሌተናል ጄነራል ባጫ ደበሌ፣ የመከላከያ ሠራዊት በየት ቦታ እና መቼ ማጥቃት እንዳለበት ወስኖ እየሰራ ነው” ሲሉ መግለጫ የሰጡት።
ከመከላከያ ሕዝብ ግንኙነት፣ ከጄራሉና ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሰጡት መግለጫዎች ወይም መረጃዎች ፉከራ አልታዩባቸውም። ነገር ግን የአማራ ክልል መንግስት፣ ኦሮሚያን ጨምሮ ክልሎች እንዲሁም መከላከያ ድጋፍ እንደሚያደርግ በይፋ መናገራቸውን ተከትሎ አንድ ይፋ ሊሆን ያልተፈለገ ነገር ግን መንግስት አድብቶ የሚፈጽመው አንድ ጉዳይ ስለመኖሩ አመልካች መሆኑ እየተነገረ ነው።
ሌተናል ጀነራል ባጫ ደበሌየኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የሠራዊት ግንባታ ሥራዎች ዋና አስተባባሪ ሌተናል ጀነራል ባጫ ደበሌ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ህዝቡ መረዳት ያለበት ወታደራዊ ስራ በወታደሮች እንጂ በአክቲቪስቶች የሚከናወን አይደለም፤ ሠራዊቱ ደግሞ በየት ቦታ፣ መቼ ማጥቃት እንዳለበት ወስኖ እየሰራ መሆኑን መናገራቸው የዚሁ ማሳያ ሆኖ ታይቷል።
መንግስት በወሰነው የተናጥል የተኩስ አቁም ስምምነት መሰረት ሠራዊቱ ከትግራይ ክልል መውጣቱን ያስታወሱት ሌተናል ጀነራል ባጫ በመንግስት ውሳኔ መሰረት ሠራዊቱ እንቅስቃሴ ማድረጉን ገልፀዋል።የመከላከያ እና የአካባቢ የፀጥታ አካላት አነስተኛ ኃይል በማስቀመጥ ጥበቃ ይደረግ እንደነበር እና አሸባሪው ቡድን በተለያየ አጋጣሚ ይህንን ኃይል ለማጥቃት በመሞከር በተለያዩ አካባቢዎች ትንኮሳ ማድረጉን ሌተናል ጀነራል ባጫ ገልፀዋል።
የተናጥል የተኩስ አቁም ስምምነቱን አሸባሪው ኃይል ለመቀበል ባህሪው አይፈቅድለትም ያሉት ሌተናል ጀነራል ባጫ የተኩስ አቁም ስምምነቱን መቀበል ያልቻለው ጁንታው ከትግራይ ህዝብ የሚቀርብለትን የሰላም ጥያቄ ለመመለስ ስለማይችል እና ከህዝብ የሚነጥለው ጉዳይ ስለሆነም ጭምር ነው ብለዋል።የሚደረገው ጦርነት ኢትዮጵያን እንደሀገር የማስቀጠልን ጉዳይ ለማረጋገጥ እና ጁንታው የያዘውን ሀገር የመበታተን እቅድ እንደማይሳካ እና እንደማይቻል ለማሳየት ነው ብለዋል።
ሠራዊቱ እየተዋጋ ያለው ለኢትዮጵያ ድንበር ነው፤ ድንበሩ ደግሞ መረብ ነው ያሉት ሌ/ጄ ባጫ ደበሌ ሠራዊቱ የተቀመጠበትን ቦታ እና የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ለማንም ግልፅ አለመደረጉንም ገልፀዋል።መከላከያ ሠራዊቱ የአገሪቱን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆኑን የገለፁት ሌተናል ጀነራል ባጫ ደበሌ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ ከመከላከያ ሠራዊቱ ጎን እንዲቆም እና ድጋፉን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






