የራያ አዘቦ ህዝብ በአሸባሪው ሕወሃት ዋጋ እየከፈለ መሆኑን የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አስታወቀ።የአገር መከላከያ ሰራዊት ትግራይን ለቆ ከወጣ ጀምሮ የራያ አዘቦ ተወላጆች የሆኑ በርካታ ሰዎች መገደላቸውንም ፓርቲው አስታውቋል።
በተጨማሪም ከ30 ሺህ በላይ ከአካባቢያቸው ተሰደዋል።የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የወጣቶች ዘርፍ ሃላፊ አቶ ጥጋቡ ጎበና እና በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የራያ አዘቦ መኾኒ ከንቲባ አቶ አለ በርዎ ከኢዜአ ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ውይይት አድርገዋል።የራያ አዘቦ ህዝብ ባለፉት ሶስት ዓመታት አገራዊ ለውጡን ተቀብሎ የህዝቡን ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ሲሰራ እንደነበር አስታውሰዋል።
ህዝቡ በአሸባሪው ሕወሃት ከማንም በላይ ጭቆና ሲደረስበት እንደነበር አስታውሰው፤ ክልሉን መከላከያ ከያዘው ጀምሮ በተለይ አርሶ አደሩ ተረጋግቶ ወደ እርሻው መግባቱን ተናግረዋል።ሆኖም በአሁኑ ወቅት መንግስት በትግራይ ክልል የወሰደውን የተናጠል ተኩስ አቁም ውሳኔ ተከትሎ ህዝቡ በአሸባሪው ሕወሃት ዋጋ እየከፈለ መሆኑን ገልጸዋል።
የትግራይ አርሶ አደር ተረጋግቶ የእርሻ ስራውን እንዲያከናውንና ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደርስ መንግስት ያደረገው መልካም ተግባር የራያ አዘቦ ህዝብ በአሸባሪው ሕወሃት ግድያና ሰቆቃ እየደረሰበት መሆኑን ጠቁመዋል።
ክልሉ በመከላከያ ቁጥጥር ስር እያለ የራያ አዘቦ አርሶ አደር ተረጋግቶ የእርሻ ስራውን ሲሰራ እንደነበር አስታውሰው፤ “አሁን ከአካባቢው መልቀቁን ተከትሎ ችግር ውስጥ በመግባቱ መፍትሄ ያስፈልገዋል” ብለዋል። የራያ አዞቦ ህዝብ ከዚህ የከፋ ጉዳት ከማስተናገዱ በፊት መንግስትና መከላከያ እንዲደርስለትም መጠየቁን ኢዜአ ዘግቧል።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






