Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  የ”በጀት ይለቀቅልን ቅድመ ሁኔታና” ክተት በትግራይ! የአሜሪካ አማራን ማሳደድ
News

የ”በጀት ይለቀቅልን ቅድመ ሁኔታና” ክተት በትግራይ! የአሜሪካ አማራን ማሳደድ

Ethioreview newsEthioreview news—July 7, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር / ትህነግ መንግስት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ የተኩስ አቁም በማድረግ ትግራይን ለቆ ሲወጣ ወደ ነበረበት ቁመና ተመልሷል። ይህንኑ አጋጣሚ በድል አዋጅ አጅቦ ደጋፊዎቹን በአዲስ አበባ፣ በመላው ዓለምና በትግራይ አስጨፍሯል። የድሉ ዓይነትና ይዘት፣ እንዲሁም የውስጥ ለውስጥ ሴራዎች ላይ መግባባት ባይኖርም፣ ትህነግ አሁን ትግራይን እጁ አድርጓል።

ትህነግ የመንግስትን የተናጠል የተኩስ አቁም እርምጃ ተከትሎ ሰባት ቅድመ ሁኔታዎችን ያስቀመጠ ሲሆን አብዛኞቹ አሜሪካ፣ አውሮፓ ህብረትና በርካታ ታዋቂ ሚዲያዎች ላይ ሲባሉ የነበሩ ቢሆንም አዲስ የተሰማው ” በጀት ልቀቁ” የሚለው፣ የታሰሩ በሙሉ ይፈቱና ዓለም ዓቀፍ በረራ በቀጥታ ወደ መቀለ የሚሉት ናቸው። መንግስት የተናጠል ተኩስ አቁሙን ከሰብአዊነት መርህ አንጻር ሲያውጅ በህግ የሚፈለጉ የአገር መከላከያ ላይ ጭፍጨፋ የፈጸሙና ያዘዙ ላይ እንደማይላዘብ ይፋ ቢያስታውቅም ጫናው እንዳየለበት ከበቂ በላይ ምልክቶች አሉ። መንግስትም በይፋ እየገለጸ ነው።

የበጀት መለቀቅ ጉዳይን አስመልክቶ የተለያዩ አስተያየቶች፣ ፍርሃቻ፣ እንዲሁም ገንዘቡን የሚያስተላለፉ ተቋማትየሉም። የገንዘብ ሚኒትር አሕመድ ሸዴን የጠቀሰው ሪፖርተር “መንግሥት የትግራይ ክልል በጀት እንዴት መለቀቅ አለበት የሚለው አዲስ ክስተት በመሆኑ፣ አሁን ላይ ሁኔታውን ማንም መገመት አይችልም” ማለታቸውን አስነብቧል።

የ2014 ዓ.ም. ካፀደቀው በጀት 203 ቢሊዮኑ ለክልሎች ድጋፍ የሚውል ነው። በዚሁ የድልድል ሰሌዳ መሰረት ኦሮሚያ 69 ቢሊዮን ፣ ለአማራ 43 ቢሊዮን፣ ደቡብ32 ቢሊዮን፣ ሶማሌ 20 ቢሊዮን፣ ትግራይ 12 ቢሊዮን፣ ሲዳማ 8 ቢሊዮን ፣ አፋር 6 ቢሊዮን ፣ ቤኒሻንጉል ጉምዝ 3.6 ቢሊዮን ፣ ጋምቤላ 2 ቢሊዮን ፣ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 3.3 ቢሊዮን ፣ ሐረሪ 1.5 ቢሊዮን ፣እንዲሁም ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር 1.7 ቢሊዮን ብር  የድጎማ በጀት ተሰፍሮላቸዋል።   

More stories

ሩሲያ የቀጠናውን ደህንነት ለማስጠበቅ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ጥረት እንደምትደግፍ አስታወቀች

April 11, 2021

ባሕር ዳር – በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት በበርሜል የተከማቸ ነዳጅና ቤንዚን ተያዘ

February 3, 2021

በትህነግ ሽንፈት ዋዜማ- የአሜሪካ ወታደሮች ከወር ተኩል በኋላ ወደ ጅብቲ ይጓዛሉ

November 29, 2021

ከታሪክ ተምረን በክብርና በአንድነት እንኖራለን!

April 27, 2021

በጀቱ ድርሻዋን ያስቀመጠላት ትግራይ ዛሬ ምንም ዓይነት የገንዘብ ተቋማት የላትም።የግልም ሆኑ የመንግስት ባንኮችም ነቅለው ወጥተዋል። በክልሉ የገንዘብ ችግር መኖሩ ቢጠቆምም አቶ ሬድዋን በአሁኑ ወቅት መንግስት ማንንም አስገድዶ ትግራይ መመደብ ወይም ባንኮች ስራ እንዲጀምሩ መግፋት እንደማይችል አመልክተዋል። ነገር ግን ትግራይ ገብቶ አገልግሎት መስጠት የሚወድ ካለ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

ሪፖርተር አስተአየት የተየቃቸው አቶ የገንዘብ ሚኒስትሩ ” የበጀት አለቃቀቅና አፈጻጸሙ ገና ውይይት አንደሚፈልግና በሒደት እንደሚታወቅ ገልጸዋል፡፡ በጀትን አስመልክቶ ያለው የመጨረሻው ጉዳይ የህግም ትንተና የሚያስፈልገው ቢሆንም፣ የትግራይ ክልል ህገ መንግስቱን በሚጻረር መልኩ በራሱ ውሳኔ ምርጫ ማካሄዱን ተከትሎ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በጀት መከልከሉ ይታወሳል። ያ ክልከላ ስለመነሳቱ የተባለ ነገር የለም።

ከዚህ ውጭ ግን አሁን አስጊ የሆነው ትህነግ በወልቃይት መስመር ውጊያ ለመክፈት ሰፊ ቁጥር ያለው ሚሊሻ በክተት መልክ ማንቀሳቀሱ ነው። ሰሞኑንን በወልቃይት በኩልና በራይ የማጥቃት ሙከራ ማድረጉና መክሸፉ ቢሰማም በሚመከታቸው አካላት ማረጋገጫ አልተሰጠበትም። ሆኖም ግን “አፍሪካ ሕብረት መንግስትን አላወገዘም” የሚለውን ሃረግ ለማሰማት ሲል አምነስቲ፣ ለትህነግ ቅርብ የሆኑ የእንግሊዝን ሚዲያዎች፣ የአሜሪካ ደጋፊ ሚዲያዎችና ባለስልጣናት ትህነግ ሰፊ ቁጥር ያለው ሃይል ወደ አማራ ክልል ግንባሮች ማዝመቱን አረጋግጠዋል።

የህዳሴው ግድብ ሙሌት ይፋ በሆነበት ቅጽበት የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አይሁዳዊው አንቶኒ ብሊንከን ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ስልክ ደውለው የኤርትራና የአማራ ሃይሎች እንዲወጡ ማዘዛቸውን አስታውቀዋል። ይህ ብቻ ሳይሆን ለተፈጸሙት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ጭካኔ የተሞላባቸው አድራጎቶች የሚጠየቁትን ወደ ህግ የመውሰዱ ተግባር እንዲጀመር ማሳሰባቸው አመልክተዋል። አሜሪካንን ጨምሮ የትህነግ ሃይል ወደ አማራ ክልል ድንበሮች ለውጊያ እያመራ ባለበት ሰዓት ይህን ማለታቸው በሌሎች ወገን እሳት እይፈጠረ ነው።

የአማራ ክልል መሪ አቶ አገኘሁ ” በርበሬና ገጀራ ይዞ አማራ ክልል ለመጨፍጨፍ መሞከር አይቻልም። ከተሞከረ የዛኔ የከፋው ይሆናል” ሲሉ ክልላቸው ማናኛውንም ጥቃት ለመመከት ዝግጁ መሆኑንን አመልክተዋል። በሌላ በኩል ከትግራይ ክልል ” ደጀን ወዳለበት” ማፈግፈጉ የተገለጸለት የአገር መከላከያ ሰራዊት ” ቁስላችን ተጠገነ፤ በወገን ኮራን” ሲል ዝግጅቱን እያስታወቀ ይገኛል።

የትህነግ ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ ” እምቢ ካሉ በጠብ መንጃ” እናናግራቸዋለን ሲሉ ለጀርመን ድምጽ ተናግረዋል። በዚህ ሃይለኝነታቸውን በገለጹበት አንደበታቸው በጀት እንዲለቀቅ ጠይቀዋል። በይፋ ባይነገርም ለጦርነት እየተዘጋጀ ያለ ሃይል እንዴት በጀት ይለቀቅለታል? የሚለው ጉዳይ በመንግስት በኩል ለውጭ ዲፕሎማቶች የሚቀርብ ሆኗል።

አንቶኒ ብሊንከን ” ትግራይን ለቆ ይውጣ” ያሉት የአማራ ሃይልን ሲሆን ከማይካድራ ጭፍጨፋ በሁዋላ በስጋት ያለውን ህዝብ ” ዳግም ትህነግ ያስተዳድርህ” ሲሉ ማወጃቸው አጀንዳቸው የተለየ እንደሆነ አመላካች ስለመሆኑ በተደጋጋሚ አስተያየት እየተሰጠ ነው።

ትህነግ በመከላከያ ሰራዊት ላይ ክህደት የፈጸሙ መኮንኖች እንዲፈቱ መጠየቁና፣ አሜሪካ በተለይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ላይ የያዘችው አቋምና አሜሪካ ከጀርባ ሆና የተዘጋጀው አዲስ የሽግግር መንግስት አዋጅ ምንም እንኳን ኦነግና ኦፌኮ አዘጋጁት ቢባልም፣ ሁሉም የተያያዘላቸው ክፍሎች ከወዲሁ ግምታቸውን እያስቀመጡ ነው። እንደ እነዚህ ሃይሎች ግምት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን በሃይል የማንሳት ሙከራ ሊደረግ ይችላል።

በሰሞኑ የፓርላማ ንግግራቸው ” ውረዱ የሚሉን ሃይሎች አሉ” ማለታቸው፣ ጉዳዩ የግለሰብ መውረድና አለመውረድ ሳይሆን በኢትዮጵያ ተላላኪ መንግስት የመትከል እቅድ መሆኑን መጠቆማቸውን የሚያነሱ ” አሜሪካ ጠ/ሚ አብይን የፈራችው ምን አልባትም በአፍሪካ ፓን አፍሪካኒዝም ዳግም ሊያቀጣጥሉ ይችላሉ” ከሚል ስጋት የተነሳ እንደሆነ ይገልጻሉ።

“ምርጫ አይካሄድም፣ የኔቶ ሃይል ትግራይ ይገባል፤ የሽግግር መንግስት ይቋቋማል” ሲሉ የትህነግ አውራ ሚዲያዎችና ደጋፊዎች፣ እንዲሁም እነ 360፣ ርዕዮት፣ መረጃና አባይ ሚዲያ ይህንኑ ሃሳብ ሲደጋግሙ ነበር። በደርግ ጊዜ የተካሄደውንና ኢትዮጵያ አሉኝ የምትላቸውን ጀነራሎች እንድታጣ የተደረገችበትን ሆን ተብሎ እንዲከሽፍ ተደርጎ የተሰራውን መፈንቅለ መንግስት የመሩት ሻለቃ ዳዊት ( ራሳቸው ናቸው ሱዳን ድረስ በሄድ መፈንቅለ መንግስቱን እከታተል ነበር” ያሉት ሁሉም ይህን አሳብ በተደጋጋሚ ሲያነሱ ይሰማ ነበር።

ሁሉም ወገኖች ዛሬ ትህነግ ስለሚያዘጋጀው ጦርና ክተት፣ የአማራ ክልልም ጥቃቱን ለመመከት የሚያደርገው ዝግጅት ወደ እልቂት እንዳያመራ ውሎ አድሮ ምን እንደሚሉ ባይታወቅም በርካቶች ስጋታቸውን እየገለጹ ነው።

ስጋታቸውን እየገለጹ የሽግግር መንግስት የሚሉ ወገኖች ከ100 በላይ ፓርቲ ሰብስበው ለመሸጋገር መስማማት ቢችሉ እንኳን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትን ካረደ ሃይል ጋር ማበራቸው በዜጎች ዘንድ የተወደደ አይመስልም። ትህነግ ግን በዚህ ግርግር ተመልሶ ደህንነቱንና መከላከያውን ለመያዝ እንዲያስችለው በልዩ ድጋፍ እየሰራ ነው። ድጋፍ የምታደርገለትም በግንባር ቀደምትነት አሜሪካ ናት። የህዳሴው ግድብ ሁለተኛ ሙሌት አሁን ስለሚጠናቀቅ ፖለቲካውን የሚቀይረው ይሆን?

ጀነራል ጻድቃን ” ፖለቲካዊ መፍትሄ ያስፈልጋል” ሲሉ ከማይታወቅ ቦታ ሆነው ለሮይተርስ በሳተላይት ስልክ አስታውቀዋል። ፖለቲካዊ መፍትሄው ከቅድመ ሁኔታው በዘለለ ምን እንደሆነ በደን ብ አልተብራራም። ቀና አሳቢዎች የኢትዮጵያ ጉዳይ በድርድር እንደሚፈታ ያምናሉ። ችግሩ ግን “ፍትህስ” የሚለው ነው። የአገር መከላከያ ሰራዊትን ያረዱ፣ ጡት የቆረጡ፣ የከዱ፣ የጨፈለቁ … ሁሉም እንዲሆን ያዘዙ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ መሪ ሆነው እንደገና የሚመጡበትና የሚፏልሉበት ዘመን እንዲመጣ ልብ ያላቸው አይፈቅዱም ። እርቅ መልካም ቢሆንም እንዲህ ያለ ወንጀል ይድበስበስ ማለት ከባድ እንደሆነ ግራ በመጋባት የሚናገሩ ብዙ ናቸው። ለዚህ ይመስላል “ትግራይ ትሂድ” የሚሉ እየበዙ የመጡት!!


[jetpack_subscription_form show_subscribers_total=”false” button_on_newline=”false” custom_font_size=”16px” custom_border_radius=”0″ custom_border_weight=”1″ custom_padding=”15″ custom_spacing=”10″ submit_button_classes=”has-text-color has-white-color has-background has-vivid-red-background-color” email_field_classes=”” show_only_email_and_button=”true”]
    NEWS
    FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
    ከጤና ሙያ ጋር የተያያዙ ጥፋቶች የአስተዳደርና የፍትሐብሔር ኃላፊነት
    የሩሲያና የኢትዮጵያ ወታደራዊ የቴክኒክ ትብብር ውይይት እየተካሄደ ነው
    Related posts
    • Related posts
    • More from author
    News

    ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

    April 26, 2026
    News

    “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

    April 26, 2026
    News

    ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

    April 13, 2026
    Load more
    Read also
    News

    ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

    April 26, 2026
    WORLD

    ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

    April 26, 2026
    News

    “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

    April 26, 2026
    WORLD

    አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

    April 26, 2026
    WORLD

    የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

    April 26, 2026
    WORLD

    የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

    April 26, 2026
    Load more
    Recent Posts
    • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
    • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
    • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
    • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
    • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
    • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
    • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
    • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
    • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
    • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
    • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
    • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
    • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
    • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
    • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
    Social networks
    FacebookLikes
    X TwitterFollowers
    PinterestFollowers
    InstagramFollowers
    YoutubeSubscribers
    VimeoSubscribers
      VOE
      The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

      MENU

      NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
      © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
      • CONTACT
      • law
      • INTERVIEW
      • ያበደው
      • ECONOMY
      • Home demo times
      • VOE VIDEO
      • ENGLISH PAGE
      • Home Demo default 2