የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ዕርዳታን ለጦርነት እንዴት እንደተጠቀመበት የሚያውቁ ዜጎች ዛሬም መንግስት ከደረግ ስህተት በመማር ለአፍታም ቸል እንዳይል ጥሪ እያሰሙ ነው። በእርዳታ ስም የገቡ ድርጅቶቻቸው አቋማቸውና አካሄዳቸው የማይምር መሆኑንን የሚያሳዩ ምልክት በመታየታቸው አንዳንዶች ስጋት እንዳላቸውም እየጠቀሱ ነው።
በማህበራዊ ሚዲያ፣ በተለያዩ አውዶችና በጎንዮሽ ሕዝብ ” የእርዳታ ቁሳቁስ ሊፈተሽ ይገባል። መፈተሽ ከደህንነታችን አንጻር ለነገ የሚባል አይደለም። ለጋሾችም ቢሆኑ ፍተሻን የሚቃወሙበት አንዳች ህጋዊ መሰረት የላቸውም” ብለዋል። ኢዜአ ያነፋገራቸው ባለሙያ የሚከተለውን ብለዋል።
የተራድኦ ድርጅቶች ከተፈቀደላቸው ተግባር ውጭ እንዳይንቀሳቀሱ መንግስት ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ እንዳለበት የህግና የታሪክ ምሁር ዶክተር አልማው ክፍሌ ተናገሩ።የተራድኦ ድርጅቶች ከአድሎ በጸዳ መልኩ ሰብዓዊነት፣ ገለልተኝነትና ነጻነታቸውን ጠብቀው በችግር ውስጥ ያሉ ሰዎችን ለመርዳት የተቋቋሙ ናቸው።
ዓለም አቀፋዊ የሰብዓዊ ድርጅቶች ደግሞ በየትኛውም የዓለም ጥግ ያሉ አገሮች ተፈጥሯዊም ሆነ ሰው ሰራሽ ችግሮች ወይም ግጭት ሲገጥማቸው ድጋፍ ለማድረግ ይገባሉ።በኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርስቲ የህግና የታሪክ ምሁር ዶክተር አልማው ክፍሌ፤ አገሮች ቀውስ በሚገጥማቸው ጊዜ የተራድኦ ድርጅቶች የሚያደርጓቸው ሰብዓዊ ድጋፎች ትልቅ ፋይዳ እንዳላቸው ያስረዳሉ።ነገር ግን እነዚህ ድርጅቶች በአንድ አገር ውስጥ ለሰብዓዊ ድጋፍ ሲንቀሳቀሱ መከተል የሚጠበቅባቸው መብቶችና ግዴታዎች መኖራቸውን ተናግረዋል።
የተራድኦ ድርጅቶቹ ሥራቸውን ሲያከናውኑ የአገር ሉዓላዊነትን ባከበረ መልኩ መሆን እንዳለበት አመልክተው፤ በውስጣዊ ፖለቲካ እንዲሁም ህዝብንና አገርን ከሚጎዱ እንቅስቃሴዎች መታቀብ እንዳለባቸውም አንስተዋል።መንግስት በትግራይ የወሰደውን የህግ ማስከበር እርምጃ ተከትሎ ዓለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅቶች ወደ አካባቢው መግባታቸውን ጠቅሰው፤ የድርጅቶቹ ሰራተኞች ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ተገቢ ባለሆነ እንቅስቃሴዎች ውስጥ እየታዩ መሆኑን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት አንዳንድ የተራድኦ ድርጅት አባላቶች ተገቢ ባልሆነ መልኩ በህዝብና መንግስት ላይ የሽብር እንቅስቃሴን አንግበው ለሚንቀሳቀሱ ሃይሎች የመወገን አዝማሚያ እንደሚታይም ጠቅሰዋል።በአሸባሪነት የተፈረጀው ድርጅት አባላት በተራድኦ ድርጅቶች ቅጥር ግቢ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ በማህበራዊ ሚዲያዎች መሰራጨቱንም ለአብነት አንስተዋል።
አሸባሪው “ህወሃት ደርግን ለመጣል ባደረገው የትጥቅ ትግል የተራድኦ ድርጅቶች የጦር መሳሪያ በማቀበል ሲያግዙ ነበር” ያሉት የህግና ታሪክ ምሁሩ፤ መንግስት ከደርግ ዘመን ሂደቶች ትምህርት በመውሰድ የተራድኦ ድርጅቶች የሚያደርጉትን ያልተገባ እንቅስቃሴ መከታተል እንዳለበት ገልጸዋል።በእርዳታ ስም ሌሎች የአገሪቱን ህግ የሚጥሱ ተግባራት እንዳይከናወኑ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸው፤መንግስት አስፈላጊውን ፍተሻ የማድረግና እርዳታው ለተገቢው አካል መድረሱን ማረጋጋጥ እንዳለበትም ተናግረዋል።መንግስት ግብረ ሃይል በማቋቋም የቁጥጥር ስራውን ማከናወን እንደሚችልም ዶክተር አልማው ተናግረዋል።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ እስከታተመ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ታዋቂ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላም… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በድንገተኛ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ ባለሙያዎች ስህተት”… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






