“አሸባሪ” የሚል መዕረግ ተሸልሞ ወደ መቀለ የተመለሰው የትህነግ ቡድን ” ፈሪና ጀግና” በሚል እተፈራረጁ መሆኑንን በአሜሪካ የድርጅቱ ዋና ደጋፊ መናገራቸው ተሰማ። በረሃ የወረዱት ” ጅግና” ሲባሉ፤ ከተማ ተደብቀው የነበሩ ” ፈሪ” እየተባሉ ነው።
ትህነግ ከበረሃ ወጥቶ ወደ መቀለ ሲገባ ከተደበቁበት ከወጡት መካከል ዳንዔል ብርሃኔ ይገኝበታል። የድርጅቱ ዋና ደጋፊ እንዳሉት እነ ዳንኤል የሳተላይት ስልክ እንዳይጠቀሙ ተከልክለዋል። ለዚህም ምክንያቱ ” ፈሪ” በመሆናቸው ነው።
ለወትሮው ከማህበራዊ ገጽ የማይጠፋውና ወደ መቀለ ከሄደ በሁዋላ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን በመስደብ፣ በማሽሟጠጥና በማውገዝ ስራ ተሰማርቶ የነበረው ዳንዔል፣ መንግስት እንዴት እንደሚቀየር፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዴት የዓለሙ የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ቤት እንዴት እንደሚቀርቡ፣ ጦርነቱ ከሁለት ሳምንት በላይ እንደማይፈጅ በተደጋጋሚ በማስረዳት ቀዳሚ ነበር።
ተደብቆ ሕይወቱን ያተረፈው ዳንዔል ስልክ ፈልጎ ማጣቱን ከላይ የተገለጹት የትህነግ ዋና አባል በስሞታ ደረጃ ከሌሎች መስማታቸውን አስታውቀዋል። ቀደ ባለው ጊዜ ዳኒ የጌታቸው አሰፋ ወገን እንደነበር በተደጋጋሚ ሲነገር ነበር። “የደህንነቱ ሹም አለመኖራቸው ዳኒ ስልክና ኢንተርኔት ብርቁ ሆነ” ሲል የሰማውን ወሬ ያጋራን የአሜሪካ ተባባሪያችን ነው።
እንደ ዳኒ ሁሉ በርካታ የተደበቁ የነበሩ ” ፈሪ” ተብለው ፊት እንደተነሱ ከመቀለ መረጃ ያላቸው አስታውቀዋል።
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም።… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
- የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለችቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች






