ያለምንም ቅደም ሁኔታ የተኩስ ማቆም በመታወጁ ምክንያት ከመከላከል ባለፈ ሙሉ ወጊያ ውስጥ ከመሳተፍ የታቀበው የአገር መከላከያ ሰራዊት በድንገት ሙሉ ሃይሉን እኒጠቀም ሊታዘዝ እንደሚችል የኢትዮ12 የመረጃ ሰዎች አስታውቀዋል።
“መቼና እንዴት?” የሚለውን ጉዳይ ወደሁዋላ በመተው መረጃውን ያካፈሉን እንዳሉት የዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ መንግስት በድጋሚ ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ሳቢያ ወደ ሙሉ እምሶ ማጥቃት ሊዛወር እንደሚችል ተድጋጋሚ ማሳሰቢያ እያቀረበ ነው።
አውሮፓ ኮሚሽንና አሜሪካ በተደጋጋሚ በወኪሎቻቸው አማካይነት መንግስት እጅግ መታገሱን አስመልክቶ መረጃ ተሰጥቷቸዋል። የመረጃው ሰው እንዳሉት ከታክቲክም አንጻር የትህነግ ሃይልም ላይ እርምጃ ለመውሰድ ጊዜ ደርሷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ባለፈው ሳምንት ” በጥብቅ ሚስጢር እየተዘጋጀን ነው። ጁናታው ይነቀላል። ይህን ህዝብም ዓለምም ያየዋል” በማለት ጊዜው ሩቅ እንዳልሆነ መናገራቸው አይዘነጋም።
የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ መኮንኖችና የህዝብ ግንኙነት ክፍሉም በየመድረኩ ” ስንታዘዝ ሁሉንም የማድረግ አቅም አለን” በማለት ለህዝብ ቃል እየገቡ ነው። የኢትዮጵያ አየር ሃይል አዛዥ በበኩላቸው ” ከመቼውም ጊዜ በላይ ታትቀንና ተዘሃጅተን ማናቸውንም ትቃት በተፈለገው ቦታ ለመፈጸም ትዕዛዝ እየተተባበቅን ነው” ማለታቸው አይዘነጋም።
በገለልተኛ ካል ባይረጋገጥም በራያ ግንባር ትሀን አንዳንድ ቦታዎችን መያዙ ቢነገርም ” ታገሱ” የሚሉ ድምጾችም እየተሰሙ ነው። የአማራ ክልል በማይጸብሪ አቅጣጫ ጥቃት ለመጀመር ዝግጅት ማተናቀቁን የአካባቢውን ፋኖ አመራሮች በማቅረብ በትናንትናው ዕለት አስታውቋል። የአርበኛ ጎቤ ልጅ ” ያውቁናል እኛ ስንመጣ ይሸሻሉ” ሲል በተድመጠበት ቪዲዮ ሰፊ ቁጥር ያለው የአካባቢው አርበኛ ስንቁን ሰንቆ እየገባ ነው።
በከፍተኛ ጀነራሎችና አመራሮች ራሱን መልሶ ያደረጀው የአማራ ልዩ ሃይ በማይጸብሪ ከገፋ ነገሮች እንደሚቀያየሩ ባለሙያዎች ይገምታሉ። በትግራይ ከፍተኛ በደል ደርሶበታል የተባለው ሰራዊት አሁን ላይ ከድካምና ከብስጭት መዳኑንን የሚናገሩት ምንጮች ሰፊ ቁጥር ያለው ሃይል ስለተቀላቀላቸው ሃይላቸው መገንባቱን ገልጸዋል። መንግስት ለመከላከያ ሙሉ መመሪያ ስለመስጠቱ ይህ እስከታተመ ድረስ በይፋ ያለው ነገር የለም። የግጭቱ መስፋትና ግጭቱን አስመልክቶ ከአንድ ወገን የሚወታው ሪፖርት ግን ግርታ ፈጥሯል። ” ታገሱ” የሚሉ ወገኖች ደግሞ ሰፊ ኦፕሬሽን እንደሚከናወን ያምናሉ።
- Egypt and Eritrea Ink Maritime and Security Deals: What It Means for EthiopiaVOE NEWS CAIRO — Egyptian President Abdel Fattah el-Sisi and visiting Eritrean President Isaias Afwerki have agreed to launch practical cooperation programs in port… Read more: Egypt and Eritrea Ink Maritime and Security Deals: What It Means for Ethiopia
- ONLF Rejects Claims of Affiliation With Armed GroupsVOA NEWS – The Ogaden National Liberation Front (ONLF) categorically rejects claims of affiliation with armed groups and reaffirms its unwavering commitment to the… Read more: ONLF Rejects Claims of Affiliation With Armed Groups
- Beyond the Ballot: How Professor Alemayehu G. Mariam Explains Ethiopia’s Democratic ‘Escape Velocity’ on ETVIn an incisive broadcast on EBC English analyzing the architectural shifts of Ethiopia’s 7th General Election, renowned scholar Professor Alemayehu G. Mariam declared that… Read more: Beyond the Ballot: How Professor Alemayehu G. Mariam Explains Ethiopia’s Democratic ‘Escape Velocity’ on ETV
- Dr. Jote Tafese: “Curing Incurable Diseases Through Science”VOE June 06, 2026 – Although genetic engineering is a relatively new field of science—spanning no more than 40 years—it is currently transforming the… Read more: Dr. Jote Tafese: “Curing Incurable Diseases Through Science”
- ዶ/ር ጆቴ ታፈሰ- መድኃኒት አልባ ሕመሞችን በሳይንስ መፈወስሰዎችን – ከሞት አፋፍ መመለስቪኦኢ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም – የዘረ መል ምህንድስና (Genetic Engineering) ዕድሜው ከ40 ዓመታት የማይበልጥ አዲስ የሳይንስ ዘርፍ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት የሕክምናውን ዓለም… Read more: ዶ/ር ጆቴ ታፈሰ- መድኃኒት አልባ ሕመሞችን በሳይንስ መፈወስሰዎችን – ከሞት አፋፍ መመለስ







