Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  POLITICS  የ3ኛ መብረቅ ኮማንዶ ሻለቃ የግዳጅ ውሎ
POLITICS

የ3ኛ መብረቅ ኮማንዶ ሻለቃ የግዳጅ ውሎ

Ethioreview newsEthioreview news—September 3, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በልዩ ዘመቻዎች ሃይል 2ኛ ኮማንዶ ብርጌድ 3ኛ ኮማንዶ ሻለቃ በትግራይ በተደረገው ህግን በማስከበር ዘመቻ ጠላት የሚመከባቸውን ምሽጎች በሶሮቃ ፣ በዳንሻ ፣ በባአካር ፤ በቅራቅር ፤ በሁመራ ፤ በመሶበር ፤ በጨርጨርና በአይደፈር ተራሮች ላይ የተገነቡ የጠላት ምሽጎችን በመስበር የጠላትን ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን በመቆጣጠር የሰሩት ታሪክ የማይረሳው ገድል ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሸጋር በደም የተፃፈ ወርቃማ መዝገብ ነው።

ይህ ኮማንዶ ሻለቃ በመጀመሪያው ዘመቻ ቅድሚያ መቀሌ ከተማን ከመቆጣጠር በተጨማሪ በከተማዋ ውስጥ የነበረውን የጠላት የጦር መሳሪያ ግምጃቤት በመቆጣጠር ለመንግሥት ገቢ አድርጓል።

በከተማዋ መሽገው የነበሩ የጁንታን ሴሎች ከመልቀም ጀምሮ የትግራይ ሚዲያ ሃውስ ጋዜጠኞች ጋዜጠኛ ፍፁም ብርሃኔና የአይጋ ፎሮም ጋዜጣ ኢዲቶሪያልና የኢትዮጵያ ተወካይ ጋዜጠኛ ታምራት የማነን ጨምሮ በርካታ የሚዲያ ባለሙያዎችን ከየተደበቁበት በማውጣት ለህግ እንዲቀርቡ አድርጓል።

በመቀሌ ከተማ ለ24 ሰዓት ፖትሮሊንግ በማድረግ ህዝብን በማረጋጋት ከመላው ከኢትዮጵያ ህዝብ የሚደረገውን እርዳታ እጀባ በማድረግ ለህብረተሰቡ እንዲደርስ የራሱን ሚና ተጫውቷል።

More stories

ጥናቶች ከመደረደሪያ ወደ ተግባር …

January 8, 2023

…ጽንፈኝነት ወደ መካከል እንዳይመጣ … ታዬ አጽቀስላሴ

December 28, 2022

How to Avert Catastrophe in Ethiopia

November 16, 2021

Ethiopia to honor victims of November 3, 2020

November 2, 2021

በሚያዚያ 29 ቀን 2013 ዓ/ም ከሱዳን ሃምዳይት ግዛት የተነሳው የጠላት ታጣቂ ቡድን በአከባቢው ከተሰማራው ከልዩ ዘመቻዎች ሃይል ከ2ኛ ኮማንዶ ብርጌድ 3ኛ ሻለቃ ጋር ውጊያ በመግጠም ከነበረው 320 ጠላት የጁንታ ብርጌድ አዛዥ ኮ/ል በህረ ተበጄ እና የሻለቃው ዋና አዛዥ ሻምበል ተክለወይኒ ታረቀኝን ጨምሮ 100 ታጣቂ ማርኳል። ቀሪዎቹ ደግሞ በተደረገው ውጊያ ሙሉ በሙሉ ተደምስሰዋል።

ከጠላት የተማረኩ ንብረቶች 103 ዘመናዊና አዲስ ሞቶሬላ ወታደራዊ መገናኛ ከእና ሙሉ አክሰሰሪና ቅያሪ ባትሪ ፣ 01 አይኮም ፤ ቶሪያ ስልክ 01 ፣ አለም አቀፍ ጥሪ ተቀባይ ሳምሰንግ ስልክ 02 ፣ ብሬን 01 ፣ ክላሽ 05 ፣ ማካሮቭ ሽጉጥ 01 ፣ በርካታ ጥይቶችና የህክምና ቂሳቁሶች በቁጥጥር ስር ውሏል።

የኮማንዶ ሻለቃው የግዳጅ ጉዞ በአንፀባራቂ ድሎች የታጀበ ሲሆን በሁመራ ኮሪደር በራውያን በተሰጠው ግዳጅም በሁመራ ፤ በሰላሲል ፤ በባዕከር ፤ በማይ ሎሚ ፤ በአዲረመፅ ፤ ለ24 ሰዓት በቀንና በሌሊት ፖትሮሊንግ ጥበቃ በማድረግ የጠላትን መግቢያ መውጫ በመከታተል የተሳካ ስራዎችን ሰርቷል።

ጠላት በድንገት በማይፀብሪ ግምባር ማጥቃት በመክፈት በአከባቢው በነበረው አማራ ልዩ ሃይል 24ኛ እግረኛ ክ/ጦርና 31ኛ እግረኛ ክፍለጦሮችን ለማጥቃት በቆረጣ ገብቶ አድርቃይን ሲቆጣጠር ፣ ለሻለቃው አስቸኳይ ግዳጅ ተሰጥቶት ከሁመራ ራውያን ከምሽቱ 5:00 ሰዓት በመነሳት በጎንደር በቀንና በሌሊት ተጉዞ ጨው በር ደርሰ።

በጨው በር ጠላት ጊዜያዊ ድል አግኝቶ ሲፈነጭ እስከ ደባርቅ እየገሰገሰ የነበረውን ጠላት የመከላከል ቁመና በመያዝ ውጊያ ገጠመ። ጠላት ያላሰበው አይቀጡ ቅጣት ተቀጣ። በጨው በር በቴሌ ታወር ተራራ ላይ ደፈጣ የያዘውን ጠላት የሻለቃው ሁለተኛ ሻምበል ደመሰሰ።

የሻለቃው 1ኛ እና 3ኛ ሻምበሎች ተራራውን በመያዝ ሁለተኛ ሻምበል ደግሞ እስፓልቱን በመዝጋት ከምሽቱ 12 ሰዓት የተጀመረው ውጊያ ጠላት በየሰዓቱ የሰው ሃይሉን እየተካ እየገበረ የጀግናው 3ኛ ኮማንዶ ሻለቃ አባላት ደግሞ በጠንካራ መከላከል በሃሺሽ ሰክሮ እየተለፈለፈ የሚመጣውን ጠላት በማነጣጠር እየለቀመ ቁጥር የሌለው ጠላት ረገፉ ፡፡ ሌሊቱ ነግቶ ያለማቆረጥ እስከ ጧቱ 2 ሰዓት ዘልቆ ለ13 ስዓት በተደረገው ውጊያ የጠላትን ቅስም በመስበር ጠላት ባለበት እንዲቆም አደረገ።

በዚሁ ውጊያ ከክፍላቸው ተለይተው ከኮማንዶ ሻለቃው ጋር በመሆን ለ4 ሰዓት በመዋጋት የጠላትን ሲናይፐር የማረኩና የላቀ ጀብዱ የሰሩ የአማራ ልዩ ሃይል 03 አባላትን ክፍላቸውንና በስም ባላውቃቸውም 01 ሴትና 02 ወንዶች የፅናት ተምሳሌት ናቸው።

አሁንም ለ4 ቀናት ጠላትን እንቅስቃሴ በመከላከል ከተገተገ በኋላ ግምባሩን ለእግረኛ ተዋጊ ለምዕራብ ዕዝ በማስረከብ ጉዞ ከጎንደር ከአየር ማረፊያ በአውሮፕላን ወደ ሰመራ ሆነ።

ከሰመራ ወደ ጭፍራ ተጉዞ ለአዳር ባረፉበት ተለዋጭ ትዕዛዝ መጣ። እሱም ጠላት በወልዲያ በኩል ማጥቃት በመክፈት ከተማዋን በከባድ መስሪያ እየደበደበ ስለሆነ በፍጥነት ድረሱ የሚል ነው። አይበገሬዎቹ በጉዞ የደከመው ሰውነታቸው ምንም ሳያርፉ በሽንጣ ረጅሞቹ አውቶብሶች ጉዞ ወደ ውጫሌ ተጀመረ።

ውጫሌ ታሪካዊዋ ከተማ በእጅጉ ተረብሻለች። ይስማ ንጉሥ የውጫሌ ውል ታሪካዊዋ ከተማ በተፈናቃዩ ህዝብና በተዋጊው ጦር እየተርመሰመሰች ነው። ጠላት መርሳን ሰላም አምባንና ልብሶን ከተሞችን በመቆጣጠር ግስጋሴውን ቀጥሏል።

ሁሉም የሻለቃው አባላት በአንድ ቃል ተስማምተዋል ፡፡ እኛ በህይወት እያለን እንዴት ጁንታ በወሎ ምድር ገብቶ በነፃነት ይጓዛል አሉ ፡፡ በፍፁም በጭራሽ አንፈቀድለትም በሚል ደመደሙ።

ሁሉም የሻለቃው አባላት ትጥቃቸውን አጠባበቁ። ተጫማሪ ሎዳቸውንም ከመደበኛ ውጭ ተረክበው ለቀጣይ ግዳጅ እራሳቸውን አዘጋጁ።

ነሐሴ 12/12/2013 ጉዞ ተጀመረ ፡፡ ተጨማሪ ጥይቶችን በግመል በመጫን በኡርጌሳ በመቁረጥ የሊቢሶ ከተማ ፤ ደራ ፤ ሰላም አምባ ፤ ኒኒ በር ፤ የመርሳን ሰንሰለታማ ተራሮችን በማቆራረጥ በመርሳ ከተማ በስተጀርባ በመግባት የወልዲያ መውጫ መንገድ በመዝጋት በጠላት ማዘዣ ጣቢያ ላይ ጥቃት በመሰንዘር የጠላትን ደጀን በማደባየት ሲጠቀምበት የነበረውን 02 ኮብራ የትግራይ ሚዲያ ሃውስ ጊዜያዊ ስቱዲዮ ፤ 02 ኦባማ አይሱዙ የህክምና ቁስቁስና ትጥቅ ፤ 03 ሲኖትራክ ቀለብና ሲመካበት የነበረውን 02 ታንክ ፤ 02 ዙ-23 አየር መቃወሚያ እጅ በእጅ ውጊያ በቦምብ ሙሉ በሙሉ ወድመዋል።

በዚህ ግዳጅ የልዩ ዘመቻዎች ሃይል ተጨማሪ ሻለቆችም ታሪክ ሰርተዋል። ጉና እና 3ኛ አየር ወለድ ሻለቆች የወልድያ መንገድ በመዝጋት ፤ ውጋጋን ኮማንዶ ሻለቃ ደግሞ በተራራው በመሆን ለ3ኛ ኮማንዶ ሻለቃ ለከተማ ለምታደርገው ውጊያ ሽፋን በመስጠት የሪፐብሊካን 01 ሻለቃ ደግሞ 3ኛ ሻለቃ ላይ በመደረብ ፈንቅል ሻለቃና ሁሉም በአንድነት በመናበብ በጠላት ላይ ያላሰበውን ጥቃት በመሰንዘር መርሳ ከተማን ተቆጣጥረውታል።

የደቡብ እና ሰሜን ዕዝ እግረኛ ክፍለጦሮች ደግሞ በውርጌሳ በኩል በመዋጋት እስከመርሳ ደርሰዋል። በዚህ ውጊያ አንድ የገረመኝ 3ኛ ሻለቃ 1ኛ እና 2ኛ ሻምበሎች ጥምረት ነው። ሁሉቱም በጋራ በመናበብ የመርሳ ከተማን ሙሉ በሙሉ ከመቆጣጠር በተጨማሪ የጠላትን ታንኮችንና አየር ማቆሚያዎችን ያቃጠሉት እነሱ ናቸውና!

መቶ አለቃ ታሪኩ ሻሜቦ
ከልዩ ዘመቻዎች ሃይል 2ኛ ኮማንዶ ብርጌድ ከ3ኛ ሻለቃ defence Facebook

INTERVIEWOPINION
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
Sudan: Economist – Sudan Govt Set the Wrong Priorities
TPLF Sacrificing Entire Youth Generation of Tigray for Terror Ambitions
Related posts
  • Related posts
  • More from author
POLITICS

ኢራን እኛ ላይ ምን ልታደርግ ትችላለች?

March 28, 2026
POLITICS

አስቸኳይ የአርበኛነት ጥሪ ለኢትዮጵያን

March 4, 2026
POLITICS

ትራምፕ ኢራንን እንደሚወጉ ፍንጭ ሰጡ

January 28, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2