Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  “አሸባሪው ህወሓት ኢትዮጵያ እንድትከፋፈል፣ እንድትቆራረስ እና ህልውናዋ ጨርሶ እንዲጠፋ በውጭ ኃይሎች የተቋቋመ ድርጅት ነው” ነባር ህወሓት ታጋዮች
News

“አሸባሪው ህወሓት ኢትዮጵያ እንድትከፋፈል፣ እንድትቆራረስ እና ህልውናዋ ጨርሶ እንዲጠፋ በውጭ ኃይሎች የተቋቋመ ድርጅት ነው” ነባር ህወሓት ታጋዮች

Ethioreview newsEthioreview news—July 30, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ኢትዮጵያ በየዘመናቱ አንፃራዊ የቅርጽ እና የጂኦ ፖለቲካ ለውጥ ከማስተናገድ ውጭ ቅኝ ሳትገዛ በነፃነት ለዘመናት የዘለቀችው ልጆቿ ብሔር እና ሃይማኖት ሳይለያቸው በከፈሉት መስዋእትነት ነው፡፡ በቅኝ ግዛት ዘመን የአሜሪካ ሞግዚት ከነበረችው ላይቤሪያ ውጭ በልጆቿ ደም እና አጥንት ነፃነቷን ያስከበረች አፍሪካዊት ሀገር ብትኖር ኢትዮጵያ ብቻ ናት፡፡

ይህ የነፃነት ታሪኳ ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለመላው ዓለም ጥቁር ሕዝብ የነፃነት ቀንዲል ሆና እንድትዘልቅ አድርጓታል፡፡ ኢትዮጵያ ሁሌም በዚያ የነፃነት እና የአሸናፊነት ርካብ ላይ መወሳቷ የሚያበሳጫቸው ምዕራባውያን እና ቅጥረኞቻቸው የሀገሪቱን ውስጣዊ አንድነት የተፈታተኑበት ጊዜ ብዙ ነበር፡፡ የቅኝ ግዛት ሙከራቸው አጥንትን ዘልቆ በሚሰማ ሽንፈት የተደመደመባቸው ባዕዳን ኢትዮጵያውያንን እርስ በርስ ማባላት እና መከፋፈል የተሻለ አማራጭ ሆኖ ቀረበላቸው፡፡

አሸባሪው ትህነግም የኢትዮጵያ አፍራሽ ባዕዳን ሥሪት እና ቅጥቅጥ ውጤት አንዱ አካል ነበር፡፡ ወቅቱ የአፍሪካውያን ብቻ ሳይሆን የመላው ዓለም ጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ሰንደቅ የሆነችውን ሀገር ለመበታተን ከውጭ የተሰጣቸውን የሴራ ፖለቲካ ለማራመድ የውስጥ ባንዳዎች በከፍተኛ ሁኔታ ዘመቻ ላይ ነበሩ፤ 1960ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ፡፡

ከስድስት አስርት ዓመታት በኋላ ዛሬ የኢትዮጵያ ስትራቴጂክ ጠላቶች ሴራ አራማጅ የሆኑት የብሔር ፖለቲካ አቀንቃኞቹ በሚያራምዱት “የገንጣይ አስገንጣይ ፖለቲካ” የተቀናጀ የጥፋት ዘመቻ ዛሬ የኢትዮጵያን አንድነት ከሚፈታተኑበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል፡፡

More stories

“ዛሬ እኛ ነን ነገ ደግሞ እናንተ ትሆናላችሁ” ቀዳማዊ ኀይለ ሥላሤ

May 5, 2023

ሰላም፣እርጋታና የዜጎች ደህንነት ለኢትዮጵያውያን ፍትሃዊ እድገት ወሳኝ ናቸው – በአሜሪካ የህዝብ ዲፕሎማሲ አማካሪ ምክር ቤት

May 17, 2021

ትግራይ በራሷ ልጅ አንደበት ምስክርነት

June 28, 2021

“ኑ ! የወልቃይት ምድር ነጻ ወጥቷል” በስደት የሽሽት ኑሮ ላይ የነበሩ አማሮች ወደ ወልቃይት ጠገዴን ሰቲት ሁመራ ተመለሱ

June 17, 2021

ኢትዮጵያ በንጉሡም ሆነ በወታደራዊው መንግሥት ዘመን ለሕዝቦቿ የተመቸች ሀገር ነበረች ባይባል እንኳን በዘር የተለያዩበትን እና የሚጠፋፉበትን የከፋፍለህ ግዛ ፖለቲካ ያራመዱበት ወቅት ግን አልነበረም፡፡ በወቅቱ የነበረው ወታደራዊ መንግሥት ደርግ የኢትዮጵያ ሕዝብ በኢትዮጵያ አንድነት ውስጥ ለሚሰፍን ሰላም፣ እኩልነት እና ማኅበራዊ እድገት ያለውን ፍላጎት በማጤን ለሰላም በሚጥርበት ወቅት ነበር፡፡ በዚህ ወቅት መሰሪ ተልዕኮ ያላቸውን ምዕራባውያን እና የግብጽን ዓላማ ያነገቡ ኃይሎች ከውስጥ ጦርነት ከፈቱ ይላሉ የቀድሞው የህወሓት አባል አቶ አብርሐም ያየህ እና አቶ ገብረ መድህን አርአያ፡፡

ሁለቱ የቀድሞ የህወሓት አባላት ስለሽብርተኛው ትህነግ ሲመሰክሩ ዓላማውን ለማሳካት በሰላማዊ ሕዝብ ላይ ከሚፈጽሙት ጭፍጨፋ በተጨማሪ የሕዝቡን አንድነት እና የሀገር ፍቅር ስሜትን ለመስለብ የፕሮፖጋንዳ ጦርነት በህቡዕ ከፍተውበትም ነበር፡፡ ራሱን “ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ” ብሎ የሰየመው ጠባብ ብሔርተኛ ቡድን የተቀበለውን ኢትዮጵያን የመበታተን አደራ ለማስፈጸም በአንድነት ተሳስረው በኖሩ ብሔሮች መካከል ጥላቻን በመፍጠር የእርስ በርስ ጦርነት ለማድረግ ቆርጦ መነሳቱንም አውስተዋል፡፡

አቶ አብርሐም ያየህ እና አቶ ገብረ መድህን አርአያ “ማን ይናገር የነበረ ማን ያርዳ የቀበረ” ነውና ይህንን በሽብርተኛው ትህነግ እና በተባባሪዎቹ የተጠነሰሰውን ሀገርን የመከፋፈል ሴራ ለኢትዮጵያውያን እና ቀሪው ዓለም በተደራጀ መልኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ፍንትው አድርገው አሳይተዋል፡፡ ሁለቱ ግለሰቦች በወርሃ ጥቅምት 1982 ዓ.ም በመገናኛ ብዙኃን አማካኝነት እውነቱን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ይፋ አድርገውት ነበር፡፡

አቶ አብርሐም ያየህ በወቅቱ በኢትዮጵያ ውስጥ መሰረታዊ ለውጥ መምጣት አለበት ብለው ከሚያምኑት ተራማጆች መካከል አንዱ እንደነበሩ ገልጸዋል፡፡ ለለውጥ ሲባልም ከተማሪዎች እስከ ሠራተኞች ንቅናቄዎች ድረስ ገብተው ለመታገል ሞክረዋል፡፡ ሙከራቸው ሁሉ አልሆን ሲላቸው ደግሞ ምንም እንኳን ጥልቅ የርዕዮተ ዓለም መራራቅ ቢኖራቸውም በሂደት ይስተካከላል በሚል እሳቤ በየወቅቱ እና ሂደቱ ስሙን እና ግብሩን የሚቀያይረውን ሴረኛ ቡድን የያኔውን ማገብት (ማኅበረ ገስግስቲ ብሔረ ትግራይ) የአሁኑን ትህነግ ተቀላቀሉ፡፡ አቶ አብርሐም “ህወሓትን ኢትዮጵያዊ መልክና ቁመና ለማስያዝ የተደረገው ጥረት አልተሳካም ነበር” ብለዋል በምስክርነታቸው፡፡ በመጨረሻም ሽብርተኛው ትህነግ የኢትዮጵያን አንድነት አደጋ ላይ የመጣል ሴራ ሲገባቸው እነዚህ ነባር ታጋዮች ራሳቸውን ከድርጅቱ አገለሉ፡፡

ሽብርተኛው ትህነግ ከመነሻውም ለትግራይ ሕዝብ ችግሮች መፍትሔ ለማስገኘት የተቋቋመ ድርጅት አልነበረም ብለዋል አቶ አብርሐም ያየህ፡፡ በቀጥታ ኢትዮጵያ እንድትከፋፈል፣ እንድትቆራረስ እና ህልውናዋ ጨርሶ እንዲጠፋ በውጭ ኃይሎች የተቋቋመ ድርጅት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ድርጅቱ በሽሬ አካባቢ ደደቢት በርሃ ውስጥ ለትጥቅ ትግል ሲገባ ግብሩን መቀየሩን ይናገራሉ፡፡

እነ መለስ ዜናዊ አንድ ወቅት ሱዳን ላይ በነበረ ዝግጅት “የትግራይን ሪፐብሊክ እንመሰርታለን፤ የምንታገለውም ትግራይን ከኢትዮጵያ ነጥለን ራሷን የቻለች ታላቋን ሪፐብሊክ ትግራይን ለመመስረት ነው” ብለው ነበር የሚሉት ግለሰቦቹ ይህ በርካታ የወቅቱ አባላትን ቅራኔ ውስጥ ከትቶ እንደነበር ያወሳሉ፡፡ በወቅቱ ጉዳዩ በአባላቱ ዘንድ የመወያያ አጀንዳ እና የቅራኔ ምንጭ በመሆኑ እነአቶ መለስ “ብሔር ብሔረሰቦች እርስ በእርሳቸው ስለማይተማመኑ እና ለየብቻ መታገል ስላለባቸው ነው፤ የሪፐብሊኩ ምስረታም እስከ መገንጠል ይደርሳል” የሚል ማወናበጃ መልስ ሰጥተው ነበር ይላሉ፡፡ ይህም ሽብርተኛው ትህነግ ገና ከጅምሩ በሐሰት ትርክት፣ በሐሰት ፕሮፖጋንዳ እና በክህደት የጎለመሰ ድርጅት እንደነበር ማስረጃዎችን ጭምር ጠቅሰዋል፡፡

ማገብት በትግራይ ሕዝብ ዘንድ በጥርጣሬ እየታየ መምጣቱን ተከትሎ በወቅቱ የድርጅቱ የፖለቲካ ዘርፍ ኀላፊ የነበሩት መለስ ዜናዊ አዲስ ስያሜ እንዲቀየር አደረጉ፡፡ ተሓሕት (ተጋድሎ ሓርነት ሕዝቢ ትግራይ) ትግራይን በጠባብ ብሔርተኝነት ከሌላው የኢትዮጵያ ክፍል የተለየ አድርጎ የማንጸባረቅ እንቅስቃሴ መጀመሩን የቀድሞ አባላቱ ገልጸዋል፡፡ ይህም ድርጅቱ በሕዝብ ዓይን ውስጥ ጥርጣሬ ላይ በመውደቁ ትግራይን ነጥሎ ተጠቂ እና ተጎጂ አድርጎ የመሳል ስትራቴጅ በስፋት ለመንዛት ምቹ ሆነላቸው፡፡ ይህን መሰል የሽብርተኛው ትህነግ ሕዝብን የመጨፍጨፍ ስትራቴጂ እስከ አይደር ትምህርት ቤት ጭፍጨፋ ድረስ ስር የሰደደ እንደነበር አውስተዋል፡፡

ተሓሕት የሚለው መጠሪያም ብዙ ሳይቆይ ወደ ህወሓት (ሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ) እንዲቀየር ግድ አለው፡፡ “ወያኔ” የሚለው ቃል ከጥንት ጀምሮ በትግራይ የነበረ የትግል ስያሜ እንደነበር ነባር ታጋዮቹ ጠቅሰዋል፡፡ በወቅቱ ሌላውን የትግራይ አካባቢ “ትግሉ የአንተም ጭምር ነበር” ለማለት የቀረበ ማወናበጃ ስያሜ ነበር ነው የሚሉት፡፡ የእንደርታን ጨምሮ የኢሮብን እና የሌሎችን ትግራይ አካባቢዎች ተቃውሞ ለመሸወድ የቀረበ ስያሜ ነበር፡፡ ዳሩ ግን ሽብርተኛው ትህነግ በሦስት አስርት ዓመታት የመሪነት ቆይታው የትግራይን ሕዝብ ብሎም መላው ኢትዮጵያን አጎሳቁሎ ነው ያለፈው፡፡

በትጥቅ ትግሉ ወቅት እንኳን እታገልለታለሁ የሚለው ሕዝብ በተደጋጋሚ ድርቅ እንዲጠቃ የእርሻ ሥራውን ተረጋግቶ እንዳይሠራ አድርጓል፡፡ በስሙ በርካታ የገንዘብ እና የዓይነት እርዳታ ከምዕራባውያን እየለመነ ለራሱ ፍጆታ አቅርቦታል፡፡ በድጋፍ የሚመጣው ስንዴ እና ዘይት ሱዳን ገበያዎች ለጉድ ይቸበቸቡ ነበር፡፡ ገንዘቡን መሳሪያ ይገዛበታል፤ ተጠቃህ እያለ የደሃውን ገበሬ ልጅ በጦርነት ይማግዳል፤ ራሱን፣ ልጆቹንና ዘመዶቹን በውጭ ሀገራት እንደልቡ እየተንቀሳቀሰ ቅንጡ ኑሮውን ይመራል፡፡

እንደ ቀድሞ አባላቱ መረጃ ሽብርተኛው ትህነግ በስልጣን ዘመኑም የደገመው ያንኑ ነው፡፡ ዛሬ የምናየው የሽብርተኛው ትህነግ ክህደት ከትናንቱ የቀጠለ እንጂ በአንድ ጀምበር የተፈጠረ አልነበረም፡፡

ፕሬዚዳንት ዚያድባሬን አግዞ ኢትዮጵያን የወጋው ትህነግ ዳግም ኢትዮጵያን ሲኦልም ቢሆን ወርደን እናፈርሳለን ሲሉ መስማት አዲስ ልክፍት ተደርጎ መውሰድ የለበትም፡፡ ቀጭን የርዕዮተ ዓለም ልዩነት ያላቸውን የትግል አጋሮቹን ለመሳሪያ ሲል ጋብዞ እና አቅፎ ስሞ ምሽት ላይ ጨፍጭፎ የሄደ አካል ነው፡፡ ለዓመታት ከውጭ ጠላት ሲጠብቀው የነበረውን እና የተለያዩ ማኅበራዊ አገልግሎቶች ሲሰጠው የነበረውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ሰሜን ዕዝን በክህደት ያጎረሰ እጁን ሲነክስ ብርቅ የሆነው ለኛ ነው እንጂ ቡድኑ ክህደት ጥርሱን የነቀለበት ነው፡፡ አይደርን ጨምሮ በሌሎች የትግራይ አካባቢዎች “የዓላማ ጽናት” በሚል ክህደት የጨፈጨፈና ያስጨፈጨፈ ቡድን ህጻናትን ለጦርነት ቢያሰማራ፣ የሰብዓዊ ቁሳቁስ ቢያግድ እና ስደተኞችን ቢያጠቃ አይገርምም፤ ምክንያቱም የኖረበት ሴራ በመሆኑ ነው፡፡ አማራጩም አንድ ነው እርሱም አረሙን ከማሳው ላይ ማንሳት፡፡
ምንጭ፡- የወያኔው ሴራ በቀድሞ አባላቱ ሲጋለጥ (1982 ዓ.ም)

በታዘብ አራጋው ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 23/2013 ዓ.ም (አሚኮ)

POLITICS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ምዕራባውያን በኢትዮጵያ ደካማ መንግስት እንዲኖር አልያም የመንግስት ለውጥ ለማድረግ ስውር አጀንዳ መያዛቸው ተጋለጠ
THE SILENT MAJORITY!NEGOTIATED SETTLEMENT TO AVERT AN IMPENDING DOOM!!
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2