Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  SOCIETY  የአሸባሪው ህወሓት አሰቃቂ ግፎች
SOCIETY

የአሸባሪው ህወሓት አሰቃቂ ግፎች

Ethioreview newsEthioreview news—August 20, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

አቶ ተስፋሁን ብጡል ውልደታቸውም እድገታቸውም ሰሜን ወሎ ወልድያ ከተማ ነው። የሰሜን ወሎ መናገሻ በሆነቸው ወልድያ ክፉውንም ደጉንም አይተዋል። ወልደዋል ከብደዋልም። በከተማዋ ጉባ ላፍቶ ወረዳ በህብረት ሥራ ማህበር የገንዘብ ብድርና ቁጥባ የቡድን ኃላፊ ሆነውም እስከቅርብ ጊዜ ድረስ አገልግለዋል። ከዚሁ በሚያገኙት ገቢ ቤተሰባቸውን ሲደጉሙ ቆይተዋል።

አሸባሪው የህወሓት ቡድን ሰሜን ወሎን በተለይ ደግሞ የወልዲያን ከተማን ለመያዝ ባደረገው ትንኮሳ ባደረባቸው ስጋት ባለቤታቸውን፣ የባለቤታቸውን አባት፣ እህቶቻቸውና ወንድሞቻቸውን ትተው ሕፃናት ልጆቻቸውን ብቻ ይዘው ከሳምንት በፊት ደሴ ገቡ። ሁለት ሕፃን ልጆቻቸውን ይዘውም ደሴ ከሚገኙት እህታቸው ዘንዳ በጊዜያዊነት ተጠለሉ። ሆኖም እረፍት የነሳቸው ጉዳይ ቢኖር ወልድያ ጥለዋቸው የመጡት የቀሪ ቤተሰቦቻቸው ሁኔታ ነው።

የመንግሥት ሠራተኛ እንደመሆናቸው መጠን እስካሁን ድረስ የሐምሌ ወር ደመወዝ እንዳልተከፈላቸውና አሸባሪ ቡድኑ ተጨማሪ ቦታዎችን እንደሚቆጣጠር ብሎም የመንግሥት አመራሮችንም እንደሚገድል የሀሰት ፕሮፓጋንዳ የሚያሰወራ በመሆኑ እርሳቸውም ልክ እንደሌላው ዜጋ ከስጋት አልተላቀቁም።

ስጋታቸው እንዲቀረፍ፤ በተለይ ደግሞ የቤተሰባቸውም ሆነ የሰሜን ወሎ ነዋሪ ህልውና እንዲረጋገጥ ደግሞ የአገር መከላከያ ሠራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ እንዲሁም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በጋራ ሆነው ይህን አሸባሪ ቡድን ከያዘባቸው አካባቢዎች ጠራርገው እንዲያስወጡ ድምፃቸውን ያሰማሉ።

More stories

ወገኛ ምርኮዎች !!

August 27, 2021

በዓለም ባንክና በኢትዮጵያ መንግሥት የሚተገበር የ550 ሚሊዮን ዶላር ፕሮጀክት ዛሬ በይፋ ይጀመራል

January 29, 2022

በድንገተኛ የሞተር ብልሽት የፖላንድ አውሮፕላን አዲስ አበባ አረፈ

September 18, 2021

ኤርትራዊያን ስደተኞች “አሸባሪው ወራሪሃይል ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ፈጽሞብናል” ሲሉ የዓለም ሕብረተሰብ ተማጸኑ

February 23, 2022

ይህ ድምፅ ታዲያ የአቶ ተስፋሁን ብቻ አይደለም። የበርካታ ኢትዮጵያውያን እንጂ። አዎ አሸባሪው ህወሓት ባለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት በፈፀማቸው አይረሴ ግፎች በርካታ ዜጎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል። ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብታቸውም ተጥሷል፤ በዚህች ምድር  ለመኖር ያልተፈቀደላቸውም ለዘላለም አሸልበዋል። ግፍና መከራ የበዛባቸው ደግሞ አገራቸውን ለቀው እስከመሰደድ ደርሰዋል።

አሸባሪው ኃይል በሕዝባዊ እምቢተኝነት ከአራት ኪሎ ቤተመንግሥት ተሰናብቶ ወደ መቀሌ ከተሸኘ በኋላ ከዚያም በሰሜን ዕዝ ላይ ታሪካዊ ክህደት ፈፅሞ በመከላከያ ሰራዊት ከተደቆሰ በኋላ ቆላ ተንቤን እስከወረደበት ጊዜ ድረስ በትግራይ ሕዝብና በሌሎችም የኢትዮጵያ ሕዝቦች ላይ በርካታ መከራዎችን አዝንቧል።

በምዕራብ ወለጋ በተለያዩ አካባቢዎች በአሸባሪው ኦነግ ሸኔ ዘርን መሠረት ላደረጉ ጥቃቶችና የዜጎች መፈናቀል እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን በጉሙዝ ታጣቂዎች በተለይ በአማራ ተወላጆች ላይ ለደረሱ ጥቃቶችና ከቤት ንብረት መፈናቀል የህወሓት ሽብር ቡድኑ የእጅ አዙር ድጋፍ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል።

በሕግ ማስከበር ዘመቻው ወቅት አሸባሪ ቡድኑ በማይካድራ የፈፀመው ግፍ በዓለምአቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ጆሮ ዳባ ልበስ የተባለ ቢሆንም በርካታ ኢትዮጵያውያንን ያሳዘነና የተጎጂ ቤተሰቦችን ቅስም የሰበረ ድርጊት ሆኖ አልፏል። ከዚሁ አስቃቂ ጭፍጨፋ ጋር በተያያዘም ነፍሳቸውን ያተረፉና ካዳጉበትና ንብረት ካፈሩበት ቀዬ ተፈናቅለው ወደ አማራ ክልል የተመሙም ጥቂት የሚባሉ አይደሉም።

ከስምንት ወር የሕግ ማስከበር ዘመቻው በኋላ መንግሥት የተናጠል የተኩስ አቁም ስምምነት በማድረግ በትግራይ ክልል በተለይ አርሶ አደሩ የክረምቱን ወቅት ተከትሎ እርሻ እንዲያርስ የጥሞና ጊዜ ሰጥቶ መቀሌን ለቆ ቢወጣም አጥፊው የህወሓት ቡድን ስምምነቱን በመጣስ በትግራይ አዋሳኝ በሚገኙ የአማራና አፋር አካባቢዎች ላይ ጥቃት በመሰንዘር በርካቶች እንዲሞቱና እንዲቆስሉ፤ አብዛኞቹ ደግሞ አካባቢያቸውን ለቀው እንዲሰደዱ ምክንያት ሆኗል። የበርካታ ዜጎች ቤት ንብረትና የእርሻ መሬቶችም በጥቃቱ እንዲወድሙ ሆኗል።

መንግሥት ያስቀመጠውን የተኩስ አቁም ስምምነት በመጣስ በአሸባሪው ቡድን በቀጠለው በዚሁ ጦርነት በተለይ በመጀመሪያው ሳምንት በአማራ ክልል ከቆቦ ከተማ ዙሪያ ከአላማጣ ወረዳ 829 ዜጎች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል። በቀጣናው ግጭቱ እየተስፋፋ በመምጣቱም በዚሁ አካባቢ የተፈናቃዮች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል። በሰሜን ወሎ ወልዲያም 150 ሺ ሰዎች በጥቃቱ ምክንያት ተፈናቅለዋል። በሰሜን ጎንደር ደባርቅ ደግሞ 37 ሺ የሚሆኑ ሰዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል።

ከሰሞኑም አሸባሪ ቡድኑ በአፋር ጋሊኮማ ጊዜያዊ የመጠለያ ጣቢያ ላይ በከፈተው ጥቃት ከ240 በላይ የሚሆኑ ዜጎች ሕይወት በአሰቃቂ ሁኔታ አልፏል። ከነዚህ ዜጎች ውስጥ 107ቱ ሕፃናት መሆናቸው ደግሞ የአሸባሪ ቡድኑን የጭካኔ ጥግ አሳይቷል። በዚሁ ክልል በዞን አራት ፋንቲ ረሱ አውራ በሚባለው አምስት ወረዳዎች ላይ 76 ሺ የሚሆኑ ዜጎች ከቤት ንብረታቸው በአሸባሪው ቡድን ግፍ ተፈናቅለዋል። በአጠቃላይ በሽብር ቡድኑ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር 700ሺ ደርሷል።

ይህ ሁሉ የአሸባሪው ቡድን ግፍ ያስመረራቸውና በቃኝ ያሉ ከሰሜን እስከ ደቡብ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ የተነቃነቁ ኢትዮጵያውያን ታዲያ ከአገር መከላከያ ጎን በመሰለፍ አሸባሪ ቡድኑን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመደምሰስ ቆርጠው በመነሳታቸው በድል ላይ ድልን በመጎናጸፍ ላይ ይገኛሉ። ድሉ አይቀሬ በመሆኑም አቶ ተስፋሁን ብጡልን የመሳሰሉ ሰዎች በአገራቸው ተረጋግተው የሚኖሩበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም።

አስናቀ ፀጋዬ

አዲስ ዘመን ነሐሴ 14 ቀን 2013 ዓ.ም

SOCIETY
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
‹‹በአሸባሪው ህወሓት ተይዘው የነበሩ የንግድና የመኖሪያ ቤቶችን የማጣራት ሥራ እየተሰራ ይገኛል››
Economists warn of economic sabotage by terrorist TPLF
Related posts
  • Related posts
  • More from author
SOCIETY

አስጨናቂዋን ሰዓት ወደ ደስታ የቀየረው የኢትዮጵያዊያን የሕክምና ባለሙያዎች ስኬት

August 23, 2025
News

በ2018 ጓደኞቼ ዩኒቨርስቲ ይገባሉ፤ በድህነት ከተማ ሄዶ መማር ይልቻለው ታዳጊ ለቅሶ!

August 22, 2025
SOCIETY

“በጠለምት ወረዳ በዝናብ እጥረት ሳቢያ እንስሳት እየሞቱ ነው፤ ሕዝብ እየተሰደደ ነው”

August 18, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2