Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  SOCIETY  በአላማጣና ሃራ – ትህነግ የፈጸመው ግፍ
SOCIETY

በአላማጣና ሃራ – ትህነግ የፈጸመው ግፍ

Ethioreview newsEthioreview news—August 14, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

”አሸባሪው የህወሃት ቡድን በሰው ልጅ ላይ ሊፈፀም ይችላል ተብሎ የማይጠበቅ ዘግናኝ ግፍና በደል ፈፅሞብናል” ሲሉ ከሰሜን ወሎ ዞን ተፈናቅለው በደሴ ከተማ የተጠለሉ ዜጎች ተናገሩ። የደሴ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ከሰሜን ወሎ ዞን ተፈናቅለው በከተማው የተጠለሉ ዜጎች የእለት ምግብ እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።

የአላማጣ ከተማ ነዋሪ የነበሩት ወይዘሮ ትርሃስ ከበደ አሸባሪው ህወሃት በከፈተው ጦርነት ተፈናቅለው በደሴ ከተማ ቅዳሜ ገበያ ትምህርት ቤት ተጠልለው እንደሚኖሩ ተናግረዋል፡፡

ቡድኑ በማንነታቸው ብቻ አሰቃቂ ግፍና መከራ እንደፈፀመባቸው ጠቁመው፤ ሃብት ንበረታቸውን ትተው ነፍሳቸውን ለማትረፍ ጥረት ቢያደርጉም የ16 ዓመት ልጃቸው የት እንደገባ እስካሁን እንደማያውቁ ገልፀዋል፡፡

ቡድኑ በደረሰበት አካባቢ ሁሉ ወጣቱን እያፈነ በመውሰድ ወደ ጦርነት ከመማገዱ ባለፈ ሃብት ንብረት እየዘረፈና እያወደመ መሆኑ እንዳሳዘናቸው ተናግረዋል፡፡

More stories

ወገኛ ምርኮዎች !!

August 27, 2021

በዓለም ባንክና በኢትዮጵያ መንግሥት የሚተገበር የ550 ሚሊዮን ዶላር ፕሮጀክት ዛሬ በይፋ ይጀመራል

January 29, 2022

በድንገተኛ የሞተር ብልሽት የፖላንድ አውሮፕላን አዲስ አበባ አረፈ

September 18, 2021

ኤርትራዊያን ስደተኞች “አሸባሪው ወራሪሃይል ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ፈጽሞብናል” ሲሉ የዓለም ሕብረተሰብ ተማጸኑ

February 23, 2022

አንድ ልጃቸውን ይዘው እስከ ውጫሌ ድረስ ጫካ ለጫካ በእግራቸው እንደመጡ የሚናገሩት ወይዘሮ ትርሃስ የደሴ ህዝብ ላደረገላቸው ድጋፍና አቀባበል ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ሌላው የሃራ ከተማ ነዋሪ የነበሩት ተፈናቃይ አቶ ይመር ጌታቸው በበኩላቸው አሸባሪው ቡድን ያልፈፀመው ግፍና መከራ የለም ብለዋል፡፡

ወደ ከተማችን እንዳይገባ ተደራጅተን ለ15 ቀን ከፍተኛ ትግል ብናደርግም በከባድ መሳሪያ ጭምር ጭካኔ ክንዱን አሳርፎብናል፤ በርካቶችን ጨፍጭፏል፤ የተወሰኑ ወጣቶችን አፍኖ ወስዷል፤ ሃብት ንብረታችንን ዘርፏል ሲሉ ተናግረዋል።

ከጦርነቱ የተረፉ 6 ልጆቼንና ነፍስ ጡር ባለቤቴን ይዤ ጫካ ለጫካ እንደምንም ተሽሎክልኬ ደሴ ከተማ መድረስ ችያለሁም፤ ያሉት አቶ ይመር ወጣቱ ከመንግስት ጋር ተቀናጅቶ የእለት ደራሽ ምግብ እያቀረበልን በመሆኑም መደሰታቸውን ገልፀዋል።

የግብርና ስራቸውን በሚያከናውኑበት በዚህ ወሳኝ ወቅት ያላሰቡት መከራ እንደደረሰባቸው ጠቁመው፤ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚፍጨረጨረውን ቡድን ተረባርበን ለመጨረሻ ጊዜ መቅበር አለብን ይላሉ።

”አሸባሪው ቡድን ሴቶችን በመድፈር፣ ወጣቶችን በመረሸን፣ ሃብት ንብረታችን በመዘርፍ የጭካኔ ለምዱን በተግባር አሳይቶናል” ያሉት ደግሞ ጉባ ላፍቶ ወረዳ የተፈናቀሉት ወይዘሮ በለጡ አስማረ ናቸው፡፡

የሚገድላቸውን ንጹሃን ዜጎች እንኳ እንዳንቀብር በመከልከል ለአውሬና ለአሞራ በመስጠት ለአማራ ያለውን ጥላቻ በተግባር እንዳሰየ ተናግረዋል።

”አንድ ልጃቸውንና ደካማ ባለቤታቸውን ይዘው በደሴ ጊዜያዊ መጠለያ ነን” ያሉት ወይዘሮ በለጡ የደሴ ህዝብ፣ ወጣቱ፣ ነጋዴውና አመራሩ ያደረገልን ትብብር የወሎን ባህልና እሴት ከማስጠበቁም ባለፈ ተስፋ ሰጥቶናል”ብለዋል።

ቡድኑ ወጣቱን እያፈነ ወደ ማይታወቅ ቦታ ከመውሰዱም ባለፈ ሴቶችን አሰገድዶ እየደፈረ እንደሆነም ተናግረዋል።

ከደሴ ከተማ ወጣቶች መካከል ብርሃኑ ይመር በሰጠው አስተያየት ለተፈናቃዮች የእለት ደራሽ ምግብና ቁሳቁስ ለማቅረብ ወጣቱ ተደራጅቶ ከመንግስት ጋር እየሠራ ነው፡፡

ህብረተሰቡንም አስተባብረው ሽሮ፣ በርበሬና እንጀራ በማሰባሰብ ከተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው የመጡ ሰዎችን እየመገቧቸው መሆኑንም ተናግሯል፡፡

የደሴ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ምሳየ ከድር በበኩላቸው አሸባሪው ቡድን በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት እየፈጸመ በመሆኑ ለመጨረሻ ጊዜ በጋራ ማጥፋት ይጠበቅብናል”ብለዋል።

በሰሜን ወሎ ዞን ንጹሃን ዜጎች ላይ በከፈተው ጦርነት ህይወታቸውን ካጡት በተጨማሪ ከቤት ንበረታቸው ተፈናቅለው ደሴ የተጠለሉ ተፈናቃዮች ቁጥር ከ55 ሺህ ማለፉን ገልጸዋል፡፡

ትምህርት ቤቶችን ለጊዜያዊ መጠለያነት በማዘጋጀት የእለት ደራሽ ምግብ ህብረተሰቡን፣ ወጣቱን፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችንና ሌሎችን በማስተባበር ለማቅረብ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

የተፈናቃች ቁጥር በየስዓቱ በመጨመሩ ከፍተኛ መጨናነቅ መፍጠሩን ጠቁመው፤ ሁሉም በሚችለው የምግብና የቁሳቁስ ድጋፍ እንዲያርግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ከተፈናቃዮች መካከል አብዛኞች ሴቶችና ህጻናት እንደሆኑ ጠቁመው፤ የአሸባሪው ህወሓት ቡድን አባላት ከተፈናቃዮች ጋር ሰርገው እንዳይገቡም ከፍተኛ ቁጥጥርና ክትትል ከመድረጉም ባለፈ የሰዓት ገደብ መጣሉን ሃላፊዋ ጨምረው አስታውቀዋል። ምንጭ – ኢዜአ

SOCIETY
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ “በጸረ ሰላም ኃይሎች” ላይ በጣምራ እርምጃ እንዲወሰድ ታዘዘ
“…የማይተኩስ ነገር ግን ወደ ጠላት ምሽግ ሰተት ብሎ ለመግባት የሚሞክር ተዋጊ” የትህነግ “ስልጡን” የውጊያ ስልት
Related posts
  • Related posts
  • More from author
SOCIETY

አስጨናቂዋን ሰዓት ወደ ደስታ የቀየረው የኢትዮጵያዊያን የሕክምና ባለሙያዎች ስኬት

August 23, 2025
News

በ2018 ጓደኞቼ ዩኒቨርስቲ ይገባሉ፤ በድህነት ከተማ ሄዶ መማር ይልቻለው ታዳጊ ለቅሶ!

August 22, 2025
SOCIETY

“በጠለምት ወረዳ በዝናብ እጥረት ሳቢያ እንስሳት እየሞቱ ነው፤ ሕዝብ እየተሰደደ ነው”

August 18, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2