Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ትህነግ በ”ተክደናልና መገንጠል” ቀውስ ተወጥሯል – ሪፖርት
News

ትህነግ በ”ተክደናልና መገንጠል” ቀውስ ተወጥሯል – ሪፖርት

Ethioreview newsEthioreview news—September 18, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በትግራይ ፖለቲካ ገና ከጅምሩ ቸግሮችን በውይይት ለመፍታት ፋልጎት ያላቸውን ” ጸረ ትግራይና ባንዳ” የሚል ስም ይሰጥ ነበር። ወደ አገረ ማሪያም ዋሻ አምርቶ ከስምንት ወር በሁዋላ ወደ መቀለ የተመለሰው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር አመራር፣ ትግራይን ማስተዳደር ሲጀምር በርካታ ሰዎችን ስፍራ መርጦ ማጥቃቱ ይፋ መሆኑም ይታወሳል። ” ብልጽግናን አግዛችዃል፤ ባንዳ” በሚል ስም መሆኑ ነው። ለዚህ ክስ ትህነግ ይፋዊ መልስ አልሰጠም። የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ግን ስምና ማንነት፣ እንዲሁም አካባቢ ጠቅሰው ብዙ ብለዋል።

በመከላከያ ሰራዊት ላይ ” በክህደት የተፈጸመ” በተባለው ጥቃት ሳቢያ ” የህግ ማስከበር ዘመቻ” ተብሎ እጅግ ፈጣን ማጥቃት ተደርጎ የትህነግ ሃይል ሲሸነፍ፣ ከሞት የተረፉና ያልተማረኩት አመራሮች ወደ አገረ ማሪያም ሲያመሩ ተቀናቃኝ የነበሩ የፓርቲ አመራሮችም ” ቅድሚያ ትግል” በሚል ተቀላቅለዋቸው ነበር። የትግራይ ነጻነት ፓርቲ አመራር አቶ መሓሪ ዮሃንስ በቅርቡ በትግርኛ ባደረገው ቃለ ምልልስ ” ተክደናል” የሚል ሙሉ ይዘት ያለው ጉዳይ አንስቶ መነጋገሪያ ሆኖ ሰንብቷል።

አቶ መሓሪ የትህነግ አመራሮች ወደ መቀለ ከተመለሱ በሁዋላ እንደገፉዋቸው ወይም ” እኛ የተመረጥን ነን” በሚል የጠበቁትን ያህል በክልሉ የአመራር ተሳትፎ እንደተነፈጉ አምርረው ተናግረዋል። የትግራይን መጻዒ እድል አስመክቶ ” ትህነግ ሪፈረንደም ቢባል ምን እንደሚልና እንደሚቀሰቀስ በግልጽ ይንገረን” ሲሉም በትህነግ ውስጥ የትግራይ የመገንጠል ጥያቄ እንዴት እንደተያዘ መረጃ እንዲጠራ ጠይቀዋል።

ሰሞኑንን ይፋ የሆነውና በምስከረም 2013 የተዘጋጀ እንደሆነ የተነገረለት 88 ገጽ የትግል ስትራቴጂ ሰነድ እንደሚያስረዳው ከተቻለና የትህነግን ምኞት የሚያስጠብቅ ከሆነ ከኢትዮጵያ ጋር መቀጠል፣ ካልሆነ አገር የመሆን አጀንዳን ተግባራዊ ለማድረግ በተያዘው ዕቅድ መሰረት ነገሮች አልሄዱም። 2ሚሊዮን ሰራዊት እንዳዘጋጀ የሚጠቅሰው ስትራቴጂ ባሰበው መልኩ ባለመሄዱ ይመስላል አሁን ላይ ሁለት ሃሳብ እየተነሳ ነው። ስትራቴጂው አለመሳካቱ ስትራቴጂውን ማዕከል አድርጎ ለህዝብ ሲነገር በነበረው የቅስቀሳ ፕሮፓጋንዳ ሳቢያ ነው ልዩነቱ የተነሳው።

More stories

“ዛሬ እኛ ነን ነገ ደግሞ እናንተ ትሆናላችሁ” ቀዳማዊ ኀይለ ሥላሤ

May 5, 2023

ሰላም፣እርጋታና የዜጎች ደህንነት ለኢትዮጵያውያን ፍትሃዊ እድገት ወሳኝ ናቸው – በአሜሪካ የህዝብ ዲፕሎማሲ አማካሪ ምክር ቤት

May 17, 2021

ትግራይ በራሷ ልጅ አንደበት ምስክርነት

June 28, 2021

“ኑ ! የወልቃይት ምድር ነጻ ወጥቷል” በስደት የሽሽት ኑሮ ላይ የነበሩ አማሮች ወደ ወልቃይት ጠገዴን ሰቲት ሁመራ ተመለሱ

June 17, 2021

ለዚህ ሪፖርት ያናገርናቸው እንደሚሉትና “የትግራይ መከላከያ ሃይል” የሚባለው ሰራዊት አመራሮች በዚህ ሁለት ሃሳብ ውስጥ አሉበት። እንደሚታወቀውና ከስሙ መረዳት እንደሚቻለው፣ ከሁሉም በላይ ደግሞ በማኒፌስቶ በግልጽ እንደተቀመጠው ትህነግ ኢትዮጵያን እየመራም ቢሆን ዓላማው ትግራይን አገር ማድረግ ነበር። በተቋቋመለት ዓላማው መሰረት አገር ለመሆን ካስቀመጠው ጊዜ ፈጥኖ ለውጥ የገነደሰው ትህነግ፣ በፍጥነት ወደ ስልጣን ለመመለስ በየአቅጣጫው ሲረባረብ እንደነበር ይፋ የሆነበት ስትራቴጂው ምስክር ይሆናል። ይህ ስትራቴጂ ኢትዮጵያ ላለፉት ሶስት ዓመታት ስቃይዋን እንድታይ፣ ዜጎች ሰላም እንዲያጡ፣ አገሪቱ እንድትበጠበጥ፣ ዙሪያው እንዲናጋ ሲሰራ የነበረው ትህነግ ስለመሆኑም ማረጋገጫ መሆኑ እዚህ ላይ ይሰመርበታል።

ዛሬ ላይ በትግራይ ሃይል መሪዎችና አዋጊ መኮንኖች ዘንዳ የሃሳብ ልዩነት ያስነሳው ጉዳይ የትግራይ መገንጠል ጉዳይ ነው። ለጊዜው ስማቸው የማይገለጹ የትጋይ አካባቢዎች ስለ መገንጠል መስማት እንደማይፈልጉ ይሰማል። መገንጠልን በገሃድ ሲሰብክ የነበረው ትህነግም ቢሆን በውስጡ መገንጠልን አስመልክቶ ተመሳሳይ አቋም እንደሌለው ይነገራል። አብዛኛው ወጣት መገንጠልን ይደግፋል እየተባለ ነው። ይህ ክፍል ግን መገንጠል ማለት ምን ማለት እንደሆነ፣ ለመገንጠልና አገር ለመሆን ቢያንስ መሟላት የሚገባቸውን መሰረታዊ ጉዳዮች በውል ያልተረዳና በፕሮፓጋንዳ የሚገፋ እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ። ከትህነግ ውጭ ያሉ አብዛኛው ፓርቲዎች የዛሬ አቋማቸው ሙሉ በሙሉ ባይታወቅም መገንጠልን የሚያቀነቅኑ እንደነበሩ በተደጋጋሚ ይፋ አድረገው ነበር።

ያነጋገርናቸውና የክልሉን ወቅታዊ ሁኔታ የሚከታተሉ ሲናገሩ ትህነግ አመራሩ ወደ መቀለ ከመመለሱ በፊት ከሁሉም ተቀናቃኝ ፓርቲ አመራሮች ጋር በቁርኝት ይሰራ ነበር። አቶ መሓሪ እንዳሉት መቀለ ከተመለሰ በሁዋላ ፊት ነስቷቸዋል። በዚህ ሳቢያ ስማቸውን የማይጠቅሷቸው ክፍሎች ከተወሰኑት የትግራይ ወታደራዊ ሃይል መሪዎች ጋር የሃሳብ ስምምነት አድርገዋል። ይህም ማለት ትግራይ አገር እንድትሆን አቋም ይዘዋል።

ትህነግ አሁን ላይ መገንጠልን ማቀነቀን ዋጋ እንደሌለው በውስጥ ያምናል። ከወታደር ክንፉ የተወሰኑ አመራሮች ይህን ይደግፋሉ። ትህነግ አደባባይ ለቅስቀሳ ሲል እንደሚለው ሳይሆን ” አሁን ስለመገንጠል ከውሰን ከያዝናቸው ስፍራዎች ተነቅለን ትግራይ እንቀረቀራለን” ሲል በውስጥ ምክንያት እንደሚያቀርብ ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ይገልጻሉ። በሌላ አነጋገር አሁን ባለው ሁኔታ መገንጠልን ማቀነቀን አዋጪ እንደማይሆን ተህነግ ውስጥ ዕምነት አለ።

ሕዝቡን ለማነሳሳት ሲቀርቡ የነበሩ የአገርነት እሳቤዎች እነሱ በሚፈልጉት መልኩ ሳይሆን በሌላ መንገድ ተግባራዊ ይሁን ከተባለ ራሱ ትግራይ ውስጥ አንዳንድ አካባቢዎች ተቃውሞ ሊገጥመው እንደሚችል የሚገምቱም አሉ። ሰለሞን ሃይሌ እንደሚለው “ትግራይ ዛሬ ምንም ነገር የመሸከም አቅም የላትም” ሰለሞን ሲቀጥል ” የምፈራው የጥላቻው መካረር ሌላው ሕዝብም አንፈልግም ወደሚልበት ደረጃ እንዳይደርስ ነው” ይላል። ሰለሞን “ትግራይ ራስዋን ትቻል” የሚል እንቅስቃሴ ሊጀመር እንደሆነ መስማቱን ገልጾ ሁሉም ወደ ቀልቡ እንዲመለስ ይመክራል።

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ከተቋቋመ ጀምሮ በበረሃ በቆየባቸው፣ ከኤርትራ ጋር ዳግም በተካሄደ ጦርነት፣ አሁን ደግሞ የመከላከያ ሰራዊት ላይ በተፈጸመ ጥቃት ሳቢያ በተደረግ ጦርነት በርካታ ቤተሰቦች ልጆቻቸውን አጥተዋል። በትግራይም ዛሬ ድረስ ቤሰብ ልጅ እየጎደለበት ነው። ወደ አማራና አፋር ክልል የሰፋው ጦርነት ያስከተለው ድፍን ቀውስ ለሰሚ ግራ የሚጋባ ነው።

በትግራይም ሆነ በአማራና አፋር ክልል የደረሰው ቀውስና ውድመት፣ ሰብአዊ ጥፋት አገሪቱን ወደ ከፋ ጎዳና እያመራት፣ በየአቅጣጫው እየፈጠረ ያለው ስሜት መበላሸት አሳሳቢ ሆኗል። ትግራይ ከሚያዋስኗት አማራ፣ አፋር፣ ኤርትራ ጋር ያላት ግንኙነት ተበላሽቷል። በመሃል አገርም ያለው ስሜት ጥሩ አይደለም። አሁንም ስሜትን የሚያበላሹ በልዩነት አብሮ መኖር እንዳይቻል የሚያደርጉ ተግባራት እየተፈጸመ ነው። ሁሉም ወገን እገሌ ከገሌ ሳይባል እንዴት ከዚህ ቀውስ መውጣት እንደሚቻል አይገባውም።

ሰለሞን እንደሚለው ” በትህነግ የግማሽ ምዕተ ዓመት ሴራ መረረን” የሚሉ ድምጾች ገነዋል። በትግራይም ” በቃን አገር እንሁን” የሚሉ ይበዛሉ። ከሁሉም ወገን ፖለቲከኞች የህዝቡን ስሜት መግታት የሚችሉበት አቅም ያላቸው አይመስልም። እርቅም ሊሆን የሚችል የማይመስለው ለዚህ ነው። ኢትዮጵያ በህግ የምትፈልጋቸውም ዕርቅን አይመኙም። ዕርቅ ፍትህም ስላለበት።

አሜሪካ በጃጁት መሪዋ ፊርማ ይፋ ያደረገችው የተጨማሪ ማዕቀብ ጉዳይ ድርድርን ማዕከል ያደረግ ቢሆንም ” እንዴት?” የሚለውን ጥያቄ አይመልስም። ጦርነቱን የሚያባብሱትን እንደሚቀጣ የሚያትተው የአሜሪካ ዛቻ ” የአገር መከላከያ ያረደና ፣ ማረዱን በጀግንነት በፊትለፊት ያወጀውን አካል” ጭራሽ አያነሳቸውም። አንድ ወታደር ተነካ ብለው ከተማና ህዝብ የሚያወድሙት ኢምፔሪያሊስቶች ” ስለምን ኢትዮጵያን እንዲህ እንደሚጫኑ አይገባንም” ሲሉ ዜጎች ቢጠይቁም ቁርጥ ያለ ምላሽ የለም።

ኤርትራ፣ አማራ፣ መንግስትና ትህነግን ቀውስ በማስፋፋት እንደሚጠይቅ ይፋ ያደረገው የጆ ባይደን ማስፈራሪያ ውጤት ወደፊት የሚታይ ቢሆንም፣ ብዙም ትኩረት ያልሳበው በትግራይ መገንጠልና አለመገንጠል አጀንዳ ላይ የሚንሸራሸረው አቋም ” ለጊዜው ይቆይ፣ ይከፋፍለናል” በሚል ቢታሸግም እየበሰለ መሆኑ ይሰማል። የትግራይ ዳያስፖራ ” ለጊዜው እንተወው” ያለውና አቶ መሃሪ ይፋ ያደረጉት ጉዳይ በመሃል አገር ህዝብ ተደግፎ ” ትግራይ ትገንጠል” የሚለው ግፊት መንግስት ላይ እንዳይጠና ስጋት አለ። ምክንያቱም አብዛኞች በገሃድ እንደሚሉት በሁሉም አቅጣጫ የሚሰራጨውና ሲሰራጭ የኖረው የፕሮፓጋንዳው ክፋት አብሮ ያያዘውን ስር ቆራርጦታል። የአብሮነት ስሜቱን ገድሎታል። በሁሉም ወገኖች ” እንዴት አንድ ገበታ እንቀመጣለን” የሚሉም ጥቂት አይደሉም።

“ኢትዮጵያዊ አይደለንም” በሚል በግልጽ አቋማቸውን የገለጹ የመኖራቸውን ያህል፣ ” አንፈልጋችሁም” የሚሉም ሚልዮኖች ናቸው። በዚህ ሁለት የከረረ መስመር ምስኪኖች ዋጋ እየከፈሉ ነው። የትግራይ ፖለቲካ ከቀድሞ ጀመሮ የጸዳና ጥርት ብሎ የሚሄድ ባለመሆኑ ከጥርጣሬ ርቆ አያውቅም። አሁንም አሁኑኑ ” እንለይ” በሚሉና ” ቆይ ትንሽ” የሚሉ ሁለት በጊዜ ገደብ የሚጣሉ፣ ግን ተመሳሳይ ፍላጎቶች ናቸው። ለሁሉም አቶ መሓሪ እንዳሉት፣ ከሌሎችም እንደሚሰማው ትግራይ ከገባችበት ቀውስ በላይ ትገንጠል” የሚለው ንትርክ መጨረሻው ምን ይሆን?

POLITICS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
በሰሜን ወሎ ትህነግ በተቆጣጠራቸው ቦታዎች የሚበላ የለም፤ ዜጎች ህይወታቸው እያለፈ ነው
በድንገተኛ የሞተር ብልሽት የፖላንድ አውሮፕላን አዲስ አበባ አረፈ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2