Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News  ኢትዮጵያን ለማፍረስ ተዘጋጅቶ የመከነው ስትራቴጂ
News

ኢትዮጵያን ለማፍረስ ተዘጋጅቶ የመከነው ስትራቴጂ

Ethioreview newsEthioreview news—September 20, 2021
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአሸባሪነት የተፈረጀው ህወሓት አገር የማፍረስ ቅዠቱን እያጠናከረ የመጣው ከማዕከል ሸሽቶ መቀሌ ከከተተ በኋላ መሆኑን በተለያዩ ጊዜያት ሾልከው የሚወጡ ማስረጃዎች ዋቢ ናቸው። አሸባሪው ህወሃት ኢትዮጵያን በማተራመስ፣ ለእርሱ ትርፍ ሊያመጣለትና ወንጀሉን ለመሸሸግ በየአካባቢው ግጭቶችና ሁከት እንዲፈጠር በማድረግ፣ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የሀሰት ፕሮፓጋንዳ በመንዛት በህዝብ ላይ ሽብር በመፍጠር፣ ያልተፈጠረውን ተፈጥራል፣ ያልተከሰተውን ተከስቷል እያለ በማወናበድ የለውጥ ሃይሉን ለመጣል ስትራቴጂ ነድፎ መስራቱ ተጋልጧል። 

አሸባሪው ህወሃት አገር ለማተራመስ የነደፈው ባለ 80 ገጽ ስትራቴጂ ሾልኮ መውጣቱ የቡድኑን እኩይ ድርጊት ከስር መሰረቱ የሚያሳይና የክፋቱን ጥግ ለመረዳት የሚያስችል ነው። ይህ ሰነድ “የትግል ልዩ ምዕራፍ እድገቶች እና የምከታችን ቀጣይ ስትራቴጂዎች፣ ስልቶች እና አቅጣጫዎች (ቁጥር – ሁለት)” የሚል ርዕስ የተሰጠውና መስከረም 2013 ዓ.ም የተዘጋጀ ነው። ሰነዱ በጥብቅ የሚያዝ ስለመሆኑም ተገልጿል። ዋነኛ ትኩረቱ ቡድኑ የለውጥ መንግስት አስወግዶ ተመልሶ ስልጣን ላይ የሚቆናጠጥበትን መንገድ፤ አሊያም ሀገረ ትግራይን የሚመሰርትበትን ስትራቴጂ ላይ ነው።

ይህን ከግብ ለማድረስ በሃይል የዞት ከኖረው የመንግስት ሥልጣን ያሰወገደውን የለውጥ አመራር ፋታ እንዳያገኝ ለማድረግ በሚያስችል መልኩ የመንቀሳቀስን አሰፈላጊነት ይዘረዝራል። በተለይ በአገሪቷ ውስጥ በልዩ ልዩ አካባቢዎች ሁከትና ብጥብጥ እንዲቀጣጠል ማድረግ፣ በጸጥታ አካላት ላይ ጥቃት መፈጸም እንዲሁም የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመፍጠር ከውስጥና ከውጭ ሀይሎች ጋር በቅንጅት እየሰሩ ያለመረጋጋትን መፍጠር በአንድ አቅጣጫ ዘርዝሯል። የጦርነት አይቀሬነት በመዘርዘር ህዝቡ እንዲዘጋጅ ማድረግ ወሳኝ ስትራቴጂ አድርጎ አስቀምጧል።

በእጅጉ የሚገርመውና የአሸባሪ ሕወሃት እኩይ ተግባር በግልጽ የሚያስቀምጠውና ከወራት በኋላ ተግባራዊ ያደረገው የመከላከያ ሰራዊት የለውጥ ሃይሉ ደጀን እንዳይሆን ለማድረግ ያወጣው ስትራቴጂ ነው። የዚህ ስትራቴጂ አንኳር ነጥብ በሁሉም ገጽታዎች ጦርነት አይቀሬ መሆኑን በመጥቀስ ይህን ለመመከት ወታደራዊ ሚዛን አንገዳግዶ/አዛብቶ የመናድ አስፈላጊነትን አሰቀምጧል። አሸባሪው ሃይል የፌዴራል መንግስት (ጠላት ብሎ የፈርጆታል) የተጠናከረ አቅሙን አሰባስቦ “እኛን ለማጥፋት እስከሚመጣ ድረስ በመከላከል ስም የምንጠፋበትን እድል መፍጠር የለብንም” በሚል ገልጾ ወታደራዊ ሚዛን በማናጋት ወደ ጥቃት የመሸጋገር ስትራቴጂ መከተልና ወደ ሀገራዊ ጥቃት መግባት እንደሚገባ አስፍሯል። የትግራይ ህዝብ ለዚሁ ጦርነት መዘጋጀት እንዳለበትም ገልጿል፡፡ ይህን በግልጽ የሚያሳየውና የሚያረጋግጠው የሰሜን ዕዝ የመከላከያ ሰራዊትን ለመምታት፣ ትጥቁን ለመጠቅለል ስትራቴጂ ነድፎ መንቀሳቀሱን ነው። የአገር ሉዓላዊነትን ለመጠበቅ፣ በማንኛውም ወቅት ሊነሳ የሚችል ወራሪ ሃይልን በመመከት የትግራይ እናቶችን፣ አባቶችን፣ ወጣቶችን ለመታደግ ሌት ተቀን የሚለፋውን መከላከያ ሰራዊት ለመምታት የነደፈውን እስትራቴጂ ጥቅምት 24 ቀን 2014 ዓ.ም ፈጽሞታል። በዚህም ብዙዎች ዋጋ እነዲከፍሉ አድርጓል። የእርሱ ቃል አቀባይ የሆነው “መብረቃዊ እርምጃ” ወሰድን በማለት የገለጸው ጥቃት አድርሷል። በዚህም አሸባሪ ቡድኑ አገር የማፍረስ ዓላማውን በግልጽ አረጋግጧል።   

More stories

“ዛሬ እኛ ነን ነገ ደግሞ እናንተ ትሆናላችሁ” ቀዳማዊ ኀይለ ሥላሤ

May 5, 2023

ሰላም፣እርጋታና የዜጎች ደህንነት ለኢትዮጵያውያን ፍትሃዊ እድገት ወሳኝ ናቸው – በአሜሪካ የህዝብ ዲፕሎማሲ አማካሪ ምክር ቤት

May 17, 2021

ትግራይ በራሷ ልጅ አንደበት ምስክርነት

June 28, 2021

“ኑ ! የወልቃይት ምድር ነጻ ወጥቷል” በስደት የሽሽት ኑሮ ላይ የነበሩ አማሮች ወደ ወልቃይት ጠገዴን ሰቲት ሁመራ ተመለሱ

June 17, 2021

አሸባሪው ቡድን “የአብይ አስተዳደር” ከሪፎርሙ በኋላ የምእራባውያንን ተልዕኮ ተቀብሎ በተመኙት መንገድ ሊተገብርላቸው ባለመቻሉ እነርሱ ያስጀመሩት ሪፎርም አደጋ ላይ ወድቋል፤ ስለዚህም ሌላ አማራጭ ለማፈላለግ ተገደዋል በማለትም በወጣቶች ተጋድሎ የተገኘውን ለውጥ ይክዳል። የመላ ሕዝቡን ተጋድሎ በተለይም ቄሮ፣ ፋኖና የሌሎች አካባቢ ወጣቶች የተሰዉለትን ትግል ምዕራባዊያን ያመጡት አድርጎ በመሳል ከሀዲነቱን በተጨባጭ አረጋግጧል። ከአዲስ አበባ ሸሽቶ መቀሌ እንዲከትም ያደረጉትና ሪፎርሙን ያመጡት ምዕራባውያን በማሰመሰል በሰነዱ ውስጥ ሽንፈቱን ለመደበቅ ይውተረተራል።

ቀደም ሲል የትራምፕ አስተዳደር በህዳሴው ግድብ ዙሪያ የያዘውን አቋም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ ባለመቀበላቸው የአሜሪካን መንግስት የሚያዋርድ ተግባር እንደፈጸሙ ይገልጻል። በዚህ ምክንያት “ከትራምፕ አስተዳደር ጋር የነበረው ግንኙነት እና ተአማኒነት በእጅጉ እንዲበላሽ አድርጎታል” በማለት ክስተቱ ለአሸባሪው ቡድን ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረለት ያትታል። ከዚህ ባሻገር የጆ ባይደን አስተዳደር ለቡድኑ የተሻለ እድል እንደሚፈጥር አስቀምጧል። አሸባሪው ቡድን በሰነዱ ውስጥ እነዚህ ጉዳዮችን ሲጠቃቅስ ለእርሱ የተንበርካኪነትና የተላላኪነት ሚናው ይጠቅመኛል በማለት ነው። በሌላ በኩል ግን ሲጠና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የሚመሩት መንግስት ምዕራባዊያን በፈለጉት መንገድ ሊመሯቸው እንዳልቻሉ፣ ይህን አድርግ አታድርግ ለመባል ፈቃደኛ አለመሆናቸውን የሚያረጋግጥ ምስክርነት ሰጥቷል። ምንም እንኳን በአደባባይ ባይመሰክሩም ኢትዮጵያን ሊያስከብራት የሚችል የማይላላክ መሪ በመምጣቱ የትራፕም ሆነ የጆ ባይደን አስተዳደር መከፋታቸውን በሰነዱ ላይ አትቷል። የሚደነቅ ምስክር ነት ነው። እነርሱ ግን መላላክ አመላቸው በመሆኑ “የጆ ባይደን አስተዳደር” የተሻለ እድል እንደሚፈጥርላቸው ገልጿል። በርግጥም አሁን በተጨባጭ የሚታየው የኢትዮጵያን እውነት ያለመስማትና ጫና ማሰደር ለተላላኪው ቡድን የተለየ ምልከታ መኖሩን ያረጋግጣል።

በሱዳን በኩል መውጫ መግቢያ ለመፍጠርም እንደወሳኝ ስትራቴጂ መንቀሳቀስ እንደሚገባ በሰነዱ ላይ ተመላክቷል። የኤርትራ መንግስት ከስልጣን ማስወገድ ሌላኛው ወሳኝ ስትራቴጂ ተደርጓል። የሚገረበው በሌላ አገር የውስጥ ጉዳይ በመግባት መንግስት ለመገልበጥ ማሴራቸውን በሰነዳቸው አጋልጠዋል። የኤርትራ መንግስት ቅርብና አደገኛ ሁኔታ ተጋርጦብኛል በማለት ራሱን ለመከላከል እርምጃ ቢወስድ የትኛው የዓለም አቀፍ ህግ ይከለክለዋል?

አሸባሪው ህወሃት በክልሎች በተለያዩ ቦታዎች ሁከት እንዲፈጠር፣ ብጥብጥ እንዲከሰት፣ የውስጥ መፈናቀል እንዲባባስ፣ አንዱ በሌላው ላይ እንዲነሳ ማድረጋቸው የስትራቴጂው አንድ አካል ነው።

በሀገሪቱ ሰላም እና ፀጥታ የሚባል እንደሌለ በማስተጋባት እስከ ወዲያኛውም እንደማይኖር ፕሮፖጋንዳ በመስራት እንዲሁም ኢኮኖሚው ጠቅልሎ እየሞተ እንደሚገኝ፣ ህዝቦች እርስ በእርሳቸው እየተናከሱ እንደሚገኙ፣ ብቸኛው መፍትሄም ይህን ቡድን ማጥፋት መሆኑን በመግለጽ በአጭር ጊዜ መንግስትን ለማስወገድ መሰራት እንዳለበት በሰነዱ ላይ ተገልጿል። ይህን የተመለከቱ አገሮች ደግሞ አገር ትፈርሳለች የሚል ስጋት አደረባቸው። ሰነዱም ላይ አውሮፓውያን እንደሰጉ ተገለጸ።

በአውሮፓ አብዛኞቹ ሀገሮች “ሀገር እየፈረሰች ነው” የሚል ሰፊ ስጋት እንዳለባቸው ያትታል። ኢትዮጵያ ውስጥ ሊፈጠር በሚችል አለመረጋጋት ምክንያት “የአፍሪካ ቀንድ በአጠቃላይ ይታመሳል” የሚል ስጋት እንዳላቸው ይገልጻል። ከዚህ በመነሳትም ብዙ የአውሮፓ መንግስታትም ሆነ የሩቅ ምስራቅ ሀገራት ከኢትዮጵያ መንግስት ይልቅ ከቡድኑ ጋር የመገናኘት ፍላጎት እያሳዩ መሆኑንንም ያብራራል። በሌሎች አገሮች ዘንድ የዚህ ዓይነት ስሜት እንዲመጣ ነው ሲሰራ የቆየው።         

ሰነዱ በሁለት መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ያጠነጥናል። የመጀመሪያው ሁሉን አቀፍ ተቋማዊ አቅም የገነባች ትግራይን (ዲፋክቶ ትግራይ) መመስረት ነው። የሽብር ቡድኑ ከበረሃ ጀምሮ የያዘው ዓላማ ትግራይን ከኢትዮጵያ መገንጠል በመሆኑ አሁን ባዘጋጀው ሰነድ ላይ ይህን ለማሳካት ወሳኙ ጊዜ እንደደረሰ አስቀምጧል። በትግራይ ክልል ያካሄደው ህገ ወጥ ምርጫ አስመልክቶ በሰነዱ ላይ እንደገለጸው “ምርጫ በማካሄዳችውን ብቸኛው ህገ-መንግሥታዊ ክልል ሆነን በከፊል ሀገራዊነት (ዲፋክቶ) ክልል ውስጥ እንገኛለን” ሲል ምርጫ ማካሄዱ ያስገኘለትን ጥቅም ይገልጻል። ይህ እንግዲህ በህዝባዊ አመጽ ከማዕከል ተሽቀንጥሮ ሲወገድ ለራሱ የሚለው አገር ለመመስረት ህዝብን ምሽግ እንዳረጋ ያሳያል። ህዝብ የአሸባሪውን ድርጊትና ሴራ በጥንቃቄ ሳያጤን ከወንድሞቹ እየነጠለውና ወደ ጦርነት እየመራው መሆኑን ሳይገናዘብ ምርጫ በማካሄድ ለምሽግነት አመቻቸው። ከዚያም ራሱ ጦርነት አስጀምሮ “የመረጠከውን መንግስት ሊያፈርሱብህ፣ ራስህ በራስህ ማስተዳደር እንዳትችል ሊያደርጉህ ነው” በሚል የሀሰት ፐሮፓጋንዳ በማወናበድ ወንጀለኞችን ደብቆ ወንጀል ሲፈጽም ከረመ። 

በተጨማሪም  በክልሉ የሚፈጸሙ አደረጃጀቶች በሙሉ የዲፋክቶ ትግራይ ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲደራጁ እንደሚደረግ በሰነዱ ላይ በዝርዝር ተቀምጧል።  በተለይ በፀጥታ እና ምጣኔ ሀብታዊ ጉዳይ ዙሪያ ከቀረጥ እና ግብር መሰብሰብ፣ ከሶስተኛ ወገን ከሚሉት ጋር ግንኙነት እንዲሁም ንግድ እና ኢንቨስትመንት የሚሳለጥበት መንገድ አስቀምጧል። ከዚህ በተጨማሪ መገናኛ ብዙሃን እና የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን በማሟላት የትግራይ ህገ መንግስት የሚስተካከልበትን ሁኔታ እንደሚፈጠር ይገልጻል። “ህገ መንግስት መነካት የለበትም፤ ከተነካም በመቃብሬ ላይ ነው” የሚለው አሸባሪው ህወሃት ለራሱ ሲሆን ህገመንግስት እንደሚያሻሽል ግብ አስቀምጦ ሲሰራ ከርሟል። 

ሁለተኛው ጉዳይ በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት በፍጥነት በማስወገድ “የሽግግር መንግስት መመስረት” ነው። በሰነዱ ላይ በስፋት ትኩረት የተደረገው የሀገራዊ ለውጡ መሪ የሆኑትን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ ከስልጣን የሚወገዱበት ስትራቴጂዎችዎችን ነው። በስትራቴጂው ሰነድ ላይ “የአብይ ቡድን ሊወድቅ የሚችልበት በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ሰላም እና ደህንነት ማጣት፣ ዲፕሎማሲያዊ ሁኔታዎችም በመሰረቱ ከቦታው ተንገዳግዷል፡፡

ይህ በስልጣን ላይ ያለው ሀይል በሀገራዊ የአመራር ክፍተት (ሊደር ሺፕ ጋፕ) ምክንያት በተወሰነ የሰራዊት ገመድ ካልሆነ በስተቀር መቆም የሚችልበት ነገር የለም፡፡ በማንኛውም ወቅት የመውደቅ እድሉ እየጎላ እየወጣ ነው፡፡” በሚል ተገልጿል። እዚህ ላይ ነው “በተወሰነ የሰራዊት ገመድ ካልሆነ በስተቀር መቆም የሚችልበት ነገር የለም” በማለት ሰራዊቱ ለመንግስት ታማኝ መሆኑን በዘወርዋራ የሚገልጸው። ለዚህ ደግሞ የመንፈንቅለ መንግስት ሙከራው ጨምሮ ሰራዊቱ በመንግስት ላይ እንዲነሳ ለማድረግ ብዙ ርቀት ተሄዶ ቀይ መስመር መታለፉ የቅርብ ጊዜ እውነት ነው። አገር ማፍረስ ማለት ይህ አይደለምን?

በሰነዱ ላይ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዳጣና በተለይ “በኦሮሚያ፣ በቤንሻንጉል እና በጋምቤላ ተቃውሞ እየተጠናከረ መጥቷል” በሚል ትንተና የዐብይ መንግስት በ2013 ዓ.ም እንደሚያበቃለት ይገልጻል። ከዚህ በተጨማሪ “በምዕራባውያን ዘንድ የዐብይ አስተዳደር ተቀባይነት አጥቷል” በሚል ትንተና ላይ ተመስርቶ አዲስ መንግስት እንደሚመስረት በግልጽ አስቀምጧል። እዚህ ላይ አሸባሪው ህወሃት ከኢትዮጵያ ህዝብ ልብ ውስጥ የወጣና የተተፋ መሆኑን ይዘነጋዋል። ለለውጥ አመራሩ ያለውን አክብሮትና ወደፊት በመውሰድ ያሻገረኛል የሚለውነ እምነቱን ማየት አቅቶታል።

 ዶክተር አብይን የለውጥ አርአያና መሪው መሆናቸውን የሚገልጽበትን መንገድ በጭፍን ጥላቻ ሰለሚመለከተው እውነቱን መገንዘበ አልቻለም። ሕዝቡ አገሩን እንደሚወድ፣ አንድ እንደሚሆን በ27 ዓመት የገዥነት ዘመናቸው ለመረዳት ያለመቻላቸው ከትንታኔው መገንዘብ ቀላል ነው። ያሉት ሳይሆን ቀረ። ቀይ መስመሩን ሲያልፉ ህዝቡ አንድ ሆነ፤ በአንድነት ቆመ። መንግስት ከመውደቅ ይልቅ በህዝብ የተመረጠ መንግስት የመመስረቱ ጉዳይ እውን ሆነ።

ቡድኑ እንዳሰበው ባይሳካለትም ከመስከረም 25 ቀን 2013 ዓ.ም በኋላ መንግስት የሚባል እንደማይኖር የሚገልጸው የስትራቴጂ ሰነዱ በሁሉም ዘንድ ተጠናክሮ የወጣው ተቃውሞ እያስተባበረ የሚመራ ጠንካራ ሀገራዊ አመራር እንዳልተፈጠረ ይገልጻል። ስለሆነም የትግራይ ህዝብ እና ህወሃት ትግሉን እያስተባበሩ እንደሚመሩና ሀገራዊ አደረጃጀት በፍጥነት እንደሚፈጠር በሰነዱ ላይ ሰፍሯል።

ጦርነቱ ሀገራዊ ይዘት እንዲኖረው ማድረግ አሸባሪው ቡድን ስትራቴጂ አንዱ አቅጣጫ ሆኖ ተቀምጧል። ስለሆነም በተለያዩ አካባቢዎች ተበታትኖ የሚገኘው አቅሞቹን በሙሉ ማሰባሰብ እና ማቀናጀት የግድ እንደሚል አስፍሯል፡፡ በመጠነ ሰፊ የፕሮፖጋንዳ እና ቅስቀሳ ስራዎች መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ በማነሳሳት ይህ መንግስት በስልጣን ላይ እያለ የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት እንደማይኖር ማስገንዘብ እንደቁልፍ ተግባር ተወስዷል።

እነዚህንና ሌሎች እኩይ ተግባራትን በመቀየስ አገር ለማተራመስ የተነሳው ህወሃት ዛሬ ላይ ታሪክ ተቀይሮበት ከአሸባሪው ሸኔ ጋር በይፋ ተጋብቶ አገር ለማፍረስ ይሰራል። በግብጽ ቴሌቭዥን እየቀረበ ሀገር የማፍረስ ቅዥቱን ይደሰኩራል። ኢዜአ

POLITICS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለሰባት ኩባንያዎች የከፍተኛ ደረጃ የማዕድን ምርት ፈቃድ እንዲሰጥ ተጠየቀ
ሱዳን የቱርክን አደራዳሪነት መቀበሏን ይፋ አደረገች
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2