Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  SOCIETY  በዩክሬን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ወደ ፖላንድ እየተጓዙ ነው
SOCIETY

በዩክሬን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ወደ ፖላንድ እየተጓዙ ነው

Ethioreview newsEthioreview news—February 25, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ጦርነት በተቀሰቀባት ዩክሬን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ወደ ፖላንድ ጉዞ መጀመራቸውን በጀርመን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ለቢቢሲ አስታወቀ።

ኤምባሲው ኢትዮጵያውን ተማሪዎች ወደ ፓላንድ እንዲሻገሩ ከፖላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግባባት ላይ መደረሱን ተከትሎ ጉዞ የጀመሩ መሆኑንም በኤምባሲው ምክትል የሚሲዮን መሪ የሆኑት አምባሳደር ተፈሪ ታደሰ ተናግረዋል።

የሩሲያ ኃይሎች ወደ ዋና መዲናዋ ኪዬቭ ምገባታቸው እየተነገረ ካለችው ዩክሬን ወደ ፖላንድ ለመውጣት በሚደረገው ሙከራ ከፍተኛ የሆነ የትራፊክና የመኪና መጨናነቅ ስላለ መንገድ ላይ መሆናቸውን ነው አምባሳደሩ ጉዞ ከጀመሩ ተማሪዎች ተወካይ የተረዱት።

ጦርነቱ እየተጋጋለና ከ130 ሰዎች በላይ በተገደሉባት ዩክሬን ከጦርነቱ ጋር ተያይዞ ማንኛውም የመንገደኛ በረራዎች በመቋረጣቸውም ያለው አማራጭ በመኪና መጓዝ መሆኑን ገልጸው፣ ሆኖም ተማሪዎቹ በሰላም እየተጓዙ መሆኑንም አምባሳደሩ ተረድተዋል።

More stories

ወገኛ ምርኮዎች !!

August 27, 2021

በዓለም ባንክና በኢትዮጵያ መንግሥት የሚተገበር የ550 ሚሊዮን ዶላር ፕሮጀክት ዛሬ በይፋ ይጀመራል

January 29, 2022

በድንገተኛ የሞተር ብልሽት የፖላንድ አውሮፕላን አዲስ አበባ አረፈ

September 18, 2021

ኤርትራዊያን ስደተኞች “አሸባሪው ወራሪሃይል ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ፈጽሞብናል” ሲሉ የዓለም ሕብረተሰብ ተማጸኑ

February 23, 2022

በተለይም ወደ ፖላንድ ድንበር አካባቢ የሚገኙት ተማሪዎች እንቅስቃሴ የጀመሩ ሲሆን ሆኖም አንዳንድ በተዘጉ ስፍራዎች ላይ ያሉ ተማሪዎች መረጋጋት እስከሚፈጠር ድረስ የተወሰነ ጊዜ ሊቆዩ እንደሚችሉም አክለው ገልጸዋል።

አጠቃላይ በተደራጀ መልኩ መረጃቸውን ማግኘት አዳጋች በመሆኑ በዩክሬን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ቁጥር በትክክል ማግኘት እንዳልቻሉ የገለጹት አምባሳደሩ፣ እስካሁን ባለውም ከ40 አስከ 50 የሚሆኑት ተማሪዎች ፖላንድ ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።

አምባሳደሩ ከተማሪዎች ተወካዮች በተሰጣቸው መረጃ መሰረት ወደ አርባ የሚሆኑ ተማሪዎች ያሉ ሲሆን ሌሎች ተጨማሪ ተማሪዎች ከመጡ በድረገፃቸው አማካኝነት መረጃዎችን ወደ ፖላንድ ለማሳለጥ ኤምባሲያቸው ዝግጁ መሆኑንም ያስረዳሉ።

ተማሪዎቹ ፖላንድ ከደረሱም በኋላ በቀጥታ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱ የገለጹት አምባሳደር ተፈሪ ከፖላንድ መንግሥት ጋር የተደረገውም ስምምነት ይህንኑ ነው የሚመክረው።

ተማሪዎቹ ፖላንድ ከገቡ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ለሚያደርጉት ጉዞም ቲኬታቸውን ራሳቸው እንደሚገዙና ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ዝግጁ እንደሆኑም አምባሳደሩ ከተወካዮቻቸው መረዳት ችለዋል።

በአሁኑ ወቅት ዩክሬን ውስጥ ስላሉበት ሁኔታ ቢቢሲ ያናገራት በኪዬቭ ያለችው ተማሪ እሌኒ አብሮም እንደገለጸችው፣ ሁሉም ወዴት እንደሚሄዱ ግራ መጋባታቸውንና በጭንቀት ውስጥ መሆናቸውን ጠቁማ፤ የተወሰኑት ወደ ፖላንድ ድንበር መጓዛቸውን ተናግራለች።

አምባሳደሩም ተማሪዎቹ መጀመሪያ አካባቢ ላይ ከፍተኛ ጭንቀት ላይ እንደነበሩ ገልጸዋል።

“ጦርነቱ ያልተጠበቀና በዚህ ወቅት ይፈጠራል ያልተባለም ከመሆኑ አንፃር ቅድመ ዝግጅት አላደረጉም። መጀመሪያ ላይ ከፍተኛ ጭንቀት ነበር። ከኤምባሲው ጋር ከተገናኙ በኋላ በየጊዜው እየተከታተልን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እየመከርን ነው ያለነው” ብለዋል።

መጀመሪያ ላይ የተማሪዎቹ ስጋት የነበረው የፖላንድ መንግሥት ወደ አገሪቱ እንዲሻገሩ አይፈቀድም የሚል የነበረ ቢሆንም፣ በጀርመን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከፖላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር ሁኔታዎችን ካመቻቸ በኋላ በተወሰነ መልኩ መረጋጋት እንዳለ አምባሳደር ተፈሪ ገልጸዋል።

“እንደ ማንኛውም በጦርነት ውስጥ እንደሚኖር ሰው ያልተጠበቀ ስለነበር የድንጋጤ ስሜት መፈጠሩ የሚጠበቅ ነው” ብለዋል።

በዩክሬን ከተማሪዎች ውጪ በሥራ ወይም ኑሯቸውን በዩክሬን ያደረጉ ኢትዮጵያውያን ይኖሩ ይሆን ወይ? በሚል ቢቢሲ አምባሳደሩን ጥያቄ ያቀረበላቸው ሲሆን እሳቸውም “እኛ ባለንም መረጃ በአገሪቱ ውስጥ ያሉት ተማሪዎች ናቸው። ከእነሱም ጋር ግንኙነት አለን” ብለዋል።

ተማሪዎቹን በሰላም ወደ አገራቸው ለመመለስ ኤምባሲው ቡድን አቋቁሞ በትኩረት እየተከታተለ እንደሚገኝ የገለጹት አምባሳደሩ ተፈሪ ታደሰ፣ ተማሪዎችም ሆነ የተማሪ ቤተሰቦች በኤምባሲው ፌስቡክ ገፅ በተቀመጠው እንዲሁም በስልክ ማንኛውንም ጥያቄ ማቅረብ እንደሚችሉም ጠቁመዋል።

ከተለያዩ የአፍሪካ አገራት ለትምህርት ዩክሬን የሚኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ያሉ ሲሆን፣ ከፍተኛው ቁጥር የሞሮኮ ተማሪዎች ሲሆኑ (8,000)፣ ናይጄሪያ (4,000) እና ግብፅ (3,500) ሲሆኑ ጥቂት የማይባሉ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ዩክሬን ውስጥ እንደሚገኙ ቢቢሲ አረጋግጧል።

ጦርነቱ ከተቀሰቀሰ በኋላ ባለው ጊዜ አስካሁን አገራት ተማሪዎቻቸውን ማስወጣት አልቻሉም። በጀርመን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከፖላንድ መንግሥት ጋር በመተባበር ተማሪዎቹ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ በቅርበት እየተከታተለ ነው።

ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ በጀርመን በርሊን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዩክሬን ውስጥ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ደኅንነት ለመከታተል በስልክና በኢሜል ሪፖርት እንዲያደርጉለት ጠይቋል። ዘገባው የቢቢሲ ነው

SOCIETY
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
African Union calls for immediate ceasefire between Russia, Ukraine
ቻይና አስጠነነቀች !!!!
Related posts
  • Related posts
  • More from author
SOCIETY

አስጨናቂዋን ሰዓት ወደ ደስታ የቀየረው የኢትዮጵያዊያን የሕክምና ባለሙያዎች ስኬት

August 23, 2025
News

በ2018 ጓደኞቼ ዩኒቨርስቲ ይገባሉ፤ በድህነት ከተማ ሄዶ መማር ይልቻለው ታዳጊ ለቅሶ!

August 22, 2025
SOCIETY

“በጠለምት ወረዳ በዝናብ እጥረት ሳቢያ እንስሳት እየሞቱ ነው፤ ሕዝብ እየተሰደደ ነው”

August 18, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2