Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News2  የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በግል ባንኮች የከፈቷቸው የባንክ ሒሳቦች እንዲዘጉ ታዘዙ
News2

የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በግል ባንኮች የከፈቷቸው የባንክ ሒሳቦች እንዲዘጉ ታዘዙ

Ethioreview newsEthioreview news—April 10, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በግል ባንኮች የከፈቷቸው የባንክ ሒሳቦች በሙሉ እንዲዘጉ ታዘዙ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ቢዝነስ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በግል ባንኮች የከፈቷቸው የባንክ ሒሳቦች በሙሉ እንዲዘጉ ታዘዙ ትዕዛዙን ያልፈጸመ መሥሪያ ቤት በጀት አይለቀቅለትም።

የመንግሥት ባለበጀት መሥሪያ ቤቶች በተለያዩ የግል ባንኮች የከፈቷቸውን ሒሳቦች በአስቸኳይ እንዲዘጉ፣ ይህንንም ማድረጋቸውን የሚያረጋግጥ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ታዘዙ፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር በግል ባንኮች ውስጥ አካውንት ከፍተው ገንዘብ እያንቀሳቀሱ ነው ለተባሉ መሥሪያ ቤቶች በጻፈው ደብዳቤ፣ በግል ባንኮች ውስጥ ያላቸውን ሒሳብ ካልዘጉ ዕርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስጠንቅቋል፡፡

በገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታው ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) የተጻፈው ይኼው ደብዳቤ፣ በመንግሥት የፋይናንስ አስተዳደር አዋጅና የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባወጣው የፋይናንስ አስተዳደር ደንብ መሠረት፣ የመንግሥት ገንዘብ ወይም ገቢ የሚደረገው በብሔራዊ ባንክ ወይም ብሔራዊ ባንክ በሚወክለው ባንክ እንደሆነ አስታውቋል፡፡

More stories

ጓደኛቸውን ገድለው  ሲያሽከረክረው የነበረውን መኪና ወስደው የተሰወሩ ሁለት ተጠርጣሪዎች ተያዙ

May 21, 2024

የብሪክስ ፕላስ የመረጃና እና የባህል ሚዲያ ማዕከል ተመሰረተ

October 15, 2024

” የሎንግ ኦነግ ሸኔን መክዳት ከዜና በላይ ነው” – የሸኔ የሎጂስቲክ መረጃ መንግስት እጅ ገባ

February 18, 2024

“የቴህራን የአየር ክልል በኛ ቁጥጥር ስር ሆኗል” እስራኤል

June 16, 2025

በዚህ ድንጋጌ መሠረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለጊዜው የሰየመው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ብቻ መሆኑን የሚኒስትር ዴኤታው ደብዳቤ ያመለክታል፡፡

ሆኖም በአሁኑ ወቅት በርካታ የመንግሥት ባለበጀት መሥሪያ ቤቶች የመንግሥት ገንዘብ ለማንቀሳቀስ በግል ባንኮች ሒሳብ በመክፈት ላይ መሆናቸውንና ይህንን ማቋረጥ እንደሚኖርባቸው በመታመኑ ዕርምጃው እንደተወሰደ ታውቋል፡፡

በመሆኑም ይህንን ተግባር የፈጸሙ፣ እንዲሁም በዚህ በሒደት ላይ የሚገኙ መሥሪያ ቤቶች የከፈቱትን የባንክ ሒሳብ በመዝጋት ለገንዘብ ሚኒስቴር ሪፖርት እንዲያደርጉም አሳስቧቸዋል፡፡

መሥሪያ ቤቶቹ ይህንን ማድረግ ካልቻሉ ግን በሚደረገው ማጣራት፣ በግል ባንኮች ውስጥ የተከፈተ የባንክ የሒሳብ ቁጥር ከተገኘባቸው፣ ዕርምጃ እንደሚወስድባቸውም የሚኒስትር ዴኤታው ደብዳቤ አመልክቷል፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር እወስደዋለሁ ካለው ዕርምጃ ባሻገር፣ እነዚህ ባለበጀት መሥሪያ ቤቶች በግል ባንክ ያላቸውን አካውንት ዘግተው ማስረጃ ካላቀረቡ በጀታቸውን ማንቀሳቀስ የማይችሉ መሆኑን ጭምር አስታውቋል፡፡

ይህንን ትዕዛዝ ለማስፈጸም የገንዘብ ሚኒስቴር የትሬዠሪ ዳይሬክቶሬት ትዕዛዝ እንደተሰጠውም ለማወቅ ተችሏል፡፡ የሚኒስትር ዴኤታው ደብዳቤም ይህንን በተመለከተ፣ ‹‹የመሥሪያ ቤቶችን ትሬዠሪ ዳይሬክቶሬትም የባንክ ሒሳብ ቁጥር የከፈቱ ባለበጀት መሥሪያ ቤቶች የሒሳብ ቁጥሩን ዘግተው ማስረጃ ካላቀረቡ፣ ምንም ዓይነት ገንዘብ እንዳይተላለፍላቸው፣ እንዲሁም የኢንስፔክሽን ዳይሬክቶሬትም በውስጥ ኦዲት በኩል ክትትል አድርጎ ሪፖርት እንዲያቀርብ ታዟል፤›› ይላል፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር ሰሞኑን ያስተላለፈው ይህ ትዕዛዝ በተለይ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በግል ባንኮች የተከፈቱ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች አካውንቶች እንዳያንቀሳቀሱ የሚያደርግ ሲሆን፣ ገንዘባቸውን ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንዲያስተላልፉ እንደሚያስገድድ ሪፖርተር በጉዳዩ ላይ ያነጋገራቸው የግል ባንኮች የሥራ ኃላፊዎች አስረድተዋል፡፡

በዚህ ዕርምጃ ላይ ቅሬታ ያላቸው ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የግል ባንክ ኃላፊዎች፣ መንግሥት የሕዝብ ገንዘብ መንቀሳቀስ ያለበት በአንድ ባንክ ብቻ እንዲሆን መወሰኑ ተገቢ አለመሆኑንና በፋይናንስ ኢንዱስትሪ ውስጥ ያለውን የውድድር መንፈስ የሚያጠፋ ነው ብለውታል፡፡

በአንድ በኩል የውጭ ባንኮች ይግቡ እየተባለና መንግሥትም አገር በቀል ባንኮችን አበረታታለሁ ብሎ እየተናገረ፣ በተግባር ግን እንዲህ ያለውን ዕርምጃ መውሰዱ ግራ ያጋባል በማለት ዕርምጃው ተገቢ አይደለም ብለዋል፡፡

በፌዴራልም ሆነ በክልል ደረጃ ካሉ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ሒሳባቸውን ከንግድ ባንክ ወደ ተለያዩ የግል ባንኮች የሚያዘዋውሩ ቁጥራቸው እየጨመረ መምጣቱ እየተነገረ ሲሆን፣ መንግሥት አሁን የወሰደው ዕርምጃ ከዚህ ጋር ተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል፡፡

አንዳንድ መሥሪያ ቤቶች አካውንታቸውን ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደ ግል ባንኮች ሲያዛውሩ ለሠራተኞቻቸው ብድር ለማመቻቸት የተደረጉ ስምምነቶችን ታሳቢ በማድረግ ጭምር እንደሆነ የሚገለጽ ሲሆን፣ እንዲህ ያሉ ስምምነቶች ያሏቸው መሥሪያ ቤቶችም እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Source – reporter Amharic

home
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
“የህወሓት አመራሮች በዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት ቀርበው ሊጠየቁ ይገባል”
በ25 ሄክታር የባለሃብቶች አትክልትና ፍራፍሬ ማሳ ላይ ጉዳት ያደረሱ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News2

ብሔራዊ ጥቅምን አሳልፎ ለመስጠት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ባለድርሻ ሊሆኑ አይገባም – በለጠ ሞላ

March 8, 2026
News2

ለክቡር የኢፌዴሪ ማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኝና ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው የቀረበ ጥሪ

March 8, 2026
News2

ስምረት ፓርቲ የትግራይ ወጣት ለትህነግ ጀርባ መስጠቱን አስታወቀ

March 6, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2