በደራሼ አካባቢ ተፈጥሮ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንት በጥፋተኝነት የተጠረጠሩ ከ450 በላይ ግለሰቦችና 17 አመራሮችና የፀጥታ አካላት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን እንዲሁም በደቡብ ኦሞ ዞን አካባቢ ደግሞ 650 የሚሆኑ ግለሰቦችና 11 አመራሮች በሕግ እንዲጠየቁ መደረጉ ተገለጸ።ክልሉን የግጭት ማዕከል ለማድረግ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ርዕሰ መስተዳድር ርስቱ ይርዳው አመለከቱ።
ግንቦት 19 ቀን 2014 (ኢዜአ) በብሔር ስም እየነገዱ ክልሉን የግጭት ማዕከል ለማድረግ የሚንቀሳቀሱ ፀረ-ሠላም ኃይሎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ርስቱ ይርዳው አስታወቁ።
የደቡብ ክልል የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ ክልላዊ የፀጥታ ሁኔታ እንዲሁም የክልሉን ሠላምና ደህንነት በማስመልከት የተከናወኑ ተግባራትና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ውይይት መድረክ በወላይታ ሶደ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በዚህ ወቅት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው እንዳሉት በሀገራዊ ለውጡ ማግስት ያለፈው ሥርዐት ብልሹና ከፋፋይ አስተሳሰብ መሠረት ያደረጉ ግጭቶች መከሰታቸውን አስታውሰው በዚህም በርካታ ጥፋት ደርሷል ብለዋል።
ይህንን ጥፋት ለማስቆም በተለይ በክልሉ ክህዝቦች ጋር በቅርበት በተከናወኑ ስራዎች ባለፉት ሁለት አመታት በክልሉ አንፃራዊ ሠላም ማስፈን መቻሉንና በተገኘው ሠላም ወደ ልማት በመዞር ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየቱን ጠቅሰዋል።
ሆኖም በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ላይ የተራዘሙ ግጭቶች እየተስተዋሉ ነው ያሉት አቶ ርስቱ በቅርቡ በደራሼ ልዩ ወረዳ አካባቢ የተከሰተው ግጭት የፀጥታ አካላትንም ጭምር ለአሰቃቂ መስዋዕትነት የዳረገ መሆኑን አውስተዋል።
በተለይም በደራሼ ፣ ኮንሶ ፣ ኧሌ እና አካባቢው ላይ ግጭቶችን ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱ አካላት ቀጠናውን እያወኩ ፣ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እየገቱ እንደሚገኙ ገልጸው እነዚህ አካላት በብሔር ስም የሚነግዱና ክልሉን የግጭት ማዕከል የማድረግ ዓላማ ያነገቡ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
የክልሉ መንግስት ባለፈው አንድ ወር እነዚህን አካባቢዎች ከማረጋጋት ባለፈ ሕግን የማስከበር ሥራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ጠቁመው አሁንም በፀረ ህዝብ በሆኑት ኃይሎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በደራሼ አካባቢ ተፈጥሮ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንት በጥፋተኝነት የተጠረጠሩ ከ450 በላይ ግለሰቦችና 17 አመራሮችና የፀጥታ አካላት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን እንዲሁም በደቡብ ኦሞ ዞን አካባቢ ደግሞ 650 የሚሆኑ ግለሰቦችና 11 አመራሮች በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል ብለዋል።
በኮንሶና ኧሌ በነበረው ግጭት እንዲሁም በስልጤ ዞን ለመቀስቀስ ተሞክሮ በነበረው የሐይማኖት ግጭት ምክንያት የተጠረጠሩ ግለሰቦችም በቁጥጥር ሥር የማዋል ሥራም እንዲሁ እየተከናወነ እንደሚገኝ አመላክተዋል።
በክልሉ በየአካባቢው ህዝቦች የሚነሱ የአደረጃጀት ጥያቄዎች ለግጭት መንስኤ ሊሆኑ አይገባም ያሉት አቶ ርስቱ እነዚህን አጀንዳዎች ተጠቅመው ክልሉን ለማወክ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ላይ የማያዳግም እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል ብለዋል። ለዚህም የፀጥታ አካላት ብቻ ሳይሆኑ የፖለቲካ አመራሩም በቁርጠኝነት መታገልና ህዝቡን የማንቃት ሥራ መስራት አለበት ማለታቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።
- President Taye champions Africa’s dev’t and regional transformation with GERD at UNGA 80In a comprehensive address to the 80th session of the United Nations General Assembly in New York, President Taye Atske-Selassie of Ethiopia underscored Africa’s development achievements, called for urgent global action to tackle the continent’s debt crisis,… Read more: President Taye champions Africa’s dev’t and regional transformation with GERD at UNGA 80
- Two African countries refuse to recognise Palestine. Here’s whyAt the United Nations General Assembly this week, one country after another rose to declare its recognition of a Palestinian state. Britain, Canada, Australia, France and Malta joined the growing chorus, bringing the total number of UN… Read more: Two African countries refuse to recognise Palestine. Here’s why
- UN Chief Stresses Need for Countries to Adopt Climate-smart Food Policies to Reduce Reliance on Food ImportsUN Secretary-General Antonio Guterres stressed the need for countries to adopt climate-smart food policies and enhance private sector participation to reduce reliance on food imports. The second UN Food Systems Summit is taking place in Ethiopia’s capital… Read more: UN Chief Stresses Need for Countries to Adopt Climate-smart Food Policies to Reduce Reliance on Food Imports
- Puntland Intercepts Cargo Ship Carrying Weapons To MogadishuByMI News Network Authorities in Somalia’s semi-autonomous Puntland region have intercepted a cargo vessel which was carrying a massive consignment of military vehicles and weapons to Mogadishu. The vessel, per reports, is of foreign origin and was… Read more: Puntland Intercepts Cargo Ship Carrying Weapons To Mogadishu





