Skip to content
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
  • News
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    በጦርነቱ ጉዳት ለደረሰባቸው ባለሀብቶች ብድር ከመስጠት አንስቶ ሌሎችም ድጋፎች እንደሚሰጥ ተገለፀ፡፡

    February 9, 20220

    ሹፌሮችን በመግደል ተሽከርካሪ ሲሰርቁ የነበሩ አራት ግለሰቦች የሞት ቅጣት ተወሰነባቸው

    October 21, 20240

    የአማራ ክልል ከትግራይ ጋር ሁሉንም ጉዳይ በውይይትና በሰላማዊ መንገድ ለመጨረስ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ

    March 31, 20230

    Sudan official: ‘Mediation between Khartoum and Addis Ababa faces obstacles’

    February 14, 20210
    Prev Next Showing 1 Of 1866
  • Design
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    መላው አማራ ከነገ ጀምሮ ለህልውና ዘመቻ እንዲነሳ ክተት ተጠራ

    July 25, 20210

    የጆ.ባይደን አስተዳደር የሰላም አማራጭ ንግግሩን ቀድሞ የትህነግን ፍላጎት አቋም አድርጎ አቀረበ

    November 1, 20220

    በሽረ አዲስ ተስፋ፤ ሕዝብ በነጻነት ስለቀጣዩ ዕጣው አየመከረ ነው

    December 26, 20220

    እውነትን ለሥልጣን መናገር ፣ ሳማንታ ፖወር ለኢትዮጵያ ዘር ፖለቲከኞች መከላከል አቁሚ!

    March 1, 20210

    በአዲስ አበባ ከ27ሺህ በላይ ወጣቶች ተደራጅተው ከተማዋን እየጠበቁ ነው

    November 11, 20210
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • Video
    video

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለፓርላማ የሰጡት ማብራሪያ

    July 4, 2024
    video

    የህብታቸውን ምንጭ የሚያውቁ አይሰጉም! ማብራሪያ

    June 22, 2024
    video

    የሀገር አቀፍ የምክክር ሂደት ይፋዊ የማስጀመሪያ ሥነ ስርዓት

    June 4, 2024
    video

    የምክክር ሂደት ይፋዊ ማስጀመሪያ ላይ ያደረጉት ሙሉ ንግግር

    June 4, 2024
    Prev Next Showing 1 Of 5
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • News
  • Design
  • Video
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  በጎንደር፣ በወራቤና በጂንካ አካባቢ በተከሰተው ግጭት የተፈጸሙ ወንጀሎች የምርመራ ግኝት ይፋ አደረገ

በጎንደር፣ በወራቤና በጂንካ አካባቢ በተከሰተው ግጭት የተፈጸሙ ወንጀሎች የምርመራ ግኝት ይፋ አደረገ

Ethioreview newsEthioreview news—July 14, 20220
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር ከፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ጋር በመተባበር በሚያዚያ ወር በጎንደር፣ በወራቤና በጂንካ አካባቢ በተከሰተው ግጭት የተፈጸሙ ወንጀሎችን የምርመራ ግኝት ይፋ ተደረገ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር ከፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ጋር በመተባበር በሚያዚያ ወር በጎንደር እና በወራቤ ሀይማኖትን መሰረት አድርጎ እንዲሁም በጂንካና አካባቢው ማንነትን መሰረት አድርጎ በተከሰተው ግጭት የተፈጸሙ ወንጀሎችን የምርመራ ግኝት ይፋ አደረገ፡፡

የምርመራ ግኝቱን በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴ የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ፍቃዱ ጸጋ እና በፌዴራል ፖሊስ በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የወንጀል ምርመራ ኦፕሬሽን መምሪያ ኃላፊ የሆኑት አቶ ሙልኢሳ አብዲሳ በጋራ በመሆን ለሚዲያዎች አብራርተዋል፡፡

በጎንደር ሚያዝያ 18/2014 ዓ.ም በአንድ የእስልምና ኃይማኖት አባት ስርዓተ-ቀብር ላይ ለቀብር የሚሆን ድንጋይን ሰበብ በማድረግ በተከሰተው ግጭት በ20 ሰዎች ላይ ሞት፣ በ100 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት እንዲሁም በ1 መስጊድ ላይ ሙሉ በሙሉ ውድመት እና በ8 መስጊዶች ላይ ከባድ ጉዳት እንዲሁም በ2 መስጊዶች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት መድረሱን አቶ ሙልኢሳ አብራርተዋል፡፡

More stories

በእነ ታደሰ ወረደ የክስ መዝገብ ስር የተከሰሱ የህውሐት ወታደራዊ አመራሮች የክስ መቃወሚያ በጽሁፍ ለችሎቱ አቅርበዋል

March 2, 2022

በጥቁር ገበያ ከ4.5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ኪሳራ ያደረሰው ሳሙኤል እጓላ ላይ ክስ ተመሰረተበት

December 16, 2022

ከሳኡዲ ተመላሾች መካከል ወንጀል የፈጸሙ ላይ ምርመራ ሊጀመር ነው- የሰው ንግድ አንዱ ነው

May 9, 2022

የሰብአዊ መብት ጥሰት ምርምርራና አጠቃላይ ሂደት ኢትዮጵያ ለተመድ ሪፖርትና ማብራሪያ አቀረበች

May 7, 2023

አቶ ሙሊሳ በማብራሪያቸው ፖሊስ የ250 ሰዎችን የምስክርነት ቃል ተቀብሏል፤ ሌሎች ከወንጀል አፈጻተሙን የሚያስረዱ የተለያዩ ማስረጃዎችን አሰባስቧል፡፡ በዚሁም መሰረትም 509 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል በወንጀል ድርጊቱ የተሳተፉ ሰዎችን የመለየት ሥራ ተሰርቷል፡፡ በዚህም መሰረት የተደራጀውን የምርመራ መዝገብ ለዐቃቤ ሕግ አስረክበናል ያሉ ሲሆን ዐቃቤ ሕግም የክስ መመስረት ሂደቱን ጀምሯል ብለዋል፡፡

በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ ጎንደር የተፈጸመውን የሀይማኖት ግጭት መነሻ በማድረግ ወንጀሉን ከህዝብ ጋር ሆኖ ከመከላከል ይልቅ፤ አንዳንድ ጽንፈኛ ኃይሎች በጎንደር መስጊድ ተቃጥሏል ውጡና የክርስቲያን ቤቶችን አቃጥሉ በማለት በከተማው ማይክራፎን ይዘው በመቀስቀስ በ4 የኦርቶዶክስ እንዲሁም በ3 የፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያኖች ላይ ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉ ሲሆን፤ ጉዳት አድራሾቹ የሞተር ሳይክልና ገጀራዎችን በመጠቀም በ2 ሰዎች ላይ ሞት፣ በ79 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት እንዲሁም 12 በሚሆኑ በግለሰብና በንግድ ቤቶች ላይ ከባድ ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል ሲሉ አቶ ሙልኢሳ በመግለጫቸው አመላክተዋል፡፡

ጂንካ ከተፈጠረው ችግር ጋር በተያያዘም የአሪ ብሄረሰብ ዞን እንሁን በሚል የከተማውን ከንቲባ ጨምሮ ሻንካ /ወጣት/ የሚል ቡድን በማደራጀት ቅስቀሳ በማድረግ ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት በአማራ ተወላጆች ላይ ፈጸመዋል ያሉት አቶ መልኢሳ፤ በተጨማሪም 247 ሚሊዮን ብር የሚገመት የንብረት ጉዳት ደርሷል፤ 1150 የሚሆኑ ሰዎች ደግሞ ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል ብለዋል፡፡
አቶ ሙልኢሳ አክለውም የህግ ማስከበር ሂደቱን የፌዴራል ፖሊስ ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር በመሆን እንደሚቀጥል ተናግረው፤ ህብረተሰቡም ወንጀል ፈጻሚዎችን ከመደበቅ ይልቅ በማጋለጥ ወንጀልን በመከላከሉ ረገድ ከህግ አካላት ጋር በመሆን በጋራ እንዲሰራ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የክስ ሂደቶችን እና ጥልቅ የሆኑ የምርመራ ስራዎችን በተመለከተም በፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ሚኒስቴር ዴኤታ የሆኑት አቶ ፍቃዱ ጸጋ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን በጂንካ ማንነትን መሰረት ያደረገው ጥቃት ሚያዚያ 1 ቀን መፈጸሙን አውስተው፤ ነገር ግን ጉዳዩ ከመጋቢት ወር ጀምሮ ዝግጅት ሲደረግበት መቆየቱን የምርመራ ግኝቱ እንደሚያመላክት ተናግረዋል፡፡
ሚኒስቴር ዴኤታው አክለውም በደቡብ ኦሞ ዞን የተፈጸመው የወንጀል ምርመራ መሰረት የሚያደርገው ጂንካና አራት የአሪ ብሄረሰብ ተወላጆች የሚኖሩባቸው ወረዳዎች ላይ የተፈጠረውን ግጭት መሆኑን አንስተዋል፡፡

በአሪኛ ሸከን ወይም ወጣት ተብሎ የተደራጀ ቡድን፤ በደቡብ ኦሞ ዞን ከሚኖሩ 16 የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦች ውስጥ እኛ ለብቻችን የጂንካን ከተማን ጨምሮ አራት ወረዳዎችን በመያዝ ዞን መሆን አለብን፤ የሚል ዓላማን በማንገብ ኢ-መደበኛ አደረጃጀት በመፍጠር በወረዳውም በዞኑም ያሉ የመንግስት ኃላፊዎች ጭምር ያደራጇቸው ወጣቶች፤ የዞን ጥያቄያችን የማይቀበለው የአማራ ብሄር ተወላጅ ነው ስለዚህ በመጀመሪያ የአማራ ተወላጅን ነው ከአካባቢው ማስወጣት ያለብን የሚል ይዘት ያለው ቅስቀሳ አድርገዋል ሲሉ አቶ ፍቃዱ ተናግረዋል፡፡
በተለይም ከመጋቢት 26/2014 ዓ.ም ጀምሮ የኑሮ ውድነትን ሰበብ በማድረግ የአማራ ነጋዴዎችን ሱቅና ቤት በመበርበር ተለያዩ ዕቃዎችን ወደ ማዘጋጃ ቤት ወስዶ በማከማቸት ሂደት ላይ ከቆዩ በኋላ በተለይ በወረዳዎች ላይ ሚያዚያ 21/2014 ዓ.ም የሸከር ዋነኛ አደራጅ የነበረው አቶ ማቲያስ በአማረው ተገድሏል በማለት ወሬ በማናፈስ በጂንካ ደግሞ ሰልፍ እንዲኖር በማድረግ አስቀድመው በለዩት የአማራ ተወላጆች ቤት ላይ ጥቃቶች መፈጸማቸውን የምርመራ ግኝታችን ያመላክታል ብለዋል፡፡
በዚህ ጊዜ ወደ 144 የአማራ ተወላጆች ቤት ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል 46 ቤቶች በድንጋይና በተለያዩ ቁሳቁሶች ጉዳት እንዲደርስባቸው መደረጉንም የገለጹት ሚኒስቴር ዴኤታው በተጨማሪም አንድ መስጊድ ተቃጥሏል፣ 232 የንግድ ድርጅቶች ተዘርፈዋል ጥቃቶቹም የተፈጸሙት በአማራ ብሄር ተወላጆችና በሌሎች የእነሱን መደራጀት አይደግፉም ያሏቸው ብሄሮች ላይ ነው ብለዋል፡፡

በሂደቱ 782 ተጠርጣሪዎችን ፖሊስ በቁጥጥር ስር ያዋለ ሲሆን ከ782 ተጠርጣሪዎች ውስጥ በፌዴራል መንግስቱ ስልጣን ስር ይወድቃሉ የተባሉ 142 ተከሳሾች ላይ በፍትህ ሚኒስቴር በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ ክስ ተመስርቶባቸዋለው፤ ሌሎቹ በዞን በወረዳ እንደየስልጣናቸው ክስ እንዲመሰረትባቸው መደረጉንም አቶ ፍቃዱ በመግለጫቸው አብራርተዋል፡፡
በወንጀሉም ላይ የጂንካ ማዘጋጃ ቤት ኃላፊ፣ የጂንካ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ፣ የጂንካ ከተማ ፋይናንስ ጽ/ቤት ኃላፊ፣ የደቡብ አሪ ወረዳ አስተዳደር፣ የጂንካ ዩኒቨርስቲ መምህርና የተለያዩ የመንግስት ሰራተኞች የተሳተፉበት ከመንግስት ፋይናንስ እየወጣ ለወጣቶቹ አበል በተለያየ መንገድ የተከፈለበት ሂደት እንደነበር የምርመራ ግኝታችን ያሳያል ብለዋል፡፡
ምርመራው በደረሰበት ልክም የመንግስት አስተዳደር ላይ ያሉ ሰዎች በወንጀሉ ውስጥ በመሳተፍ ትልቅ ሚና እንደነበራቸው ተረጋግጧል ያሉት ሚኒስቴር ዴኤታው እስከዛሬ ከመረመርናቸው በተለየ ከ8 ሰዎች ውጭ ሌሎቹ በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ በተጨማሪም ምንም የሰው ህይወት ሳይጠፋ 8 ሰዎች ላይ ብቻ የተለያያ ጉዳት ደርሷል፡፡ መከላከያ፣ የፌዴራል ፖሊስና ልዩ ኃይል በቶሎ መግባታቸው ከዚህ የከፋ ጉዳት እንዳይደርስ እንድንከላከልም አግዞናል፤ ያሉት ሚኒስቴር ዴኤታው ይህ ጉዳት የደረሰውም አንዳንድ ወረዳዎች ላይ ከአቅማችን በላይ የሆነ ነገር የለም በሚል አመራሮቹ በወንጀሉ ላይ በመሳተፋቸው የጸጥታ አካላት እንዳይገቡ በማድረጋቸው ነው ብለዋል፡፡

አጠቃላይ በነበረው ሂደት 142 ክስ የተመሰረተባቸው ሰዎች ላይ የፌዴራል አቃቤ ህግ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አርባ ምንጭና አካባቢው በሚያስችለው ችሎት ላይ ክስ መስርቷል፤ ተጠርጣሪዎቹ ካሉበት ቦታ ወደዚያ ተዛውረው ክሳቸውን የሚከታተሉ ይሆናል፡፡ በአጠቃላይ በዚህ አካባቢ ከተከሰተው ግጭት ጋር ተያይዞ 247 ሚሊዮን ብር የዋጋ ግምት ያለው ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡

ሚያዚያ 18 /2014 ዓ.ም በተፈጥሮ ሞት የሞቱትን ታላቅ የእምነት አባት ሸክ ከማል ለጋስ የቀብር ስርዓታቸውን ለመፈጸም በጎንደር ከተማ ቀበሌ 8 አካባቢ በሚገኘው ወደ ሀጅ ኤልያስ መካነ መቃብር የእስልምና እምነት ተከታዮች መካነ መቃብር ወደ ሆነው አስከሬናቸውን ለማኖር ወዳጅ ዘመዶቻቸው ወደ ቦታው በሄዱበት ከቀኑ 7ሰዓት30 ላይ በተለምዶ ቀሀ ወንዝ ከሚባለው ድንጋይ በማውጣ መቃብሩን ለማመቻቸት በሚደረግ ሂደት ውስጥ አስቀድሞ በአጎራባችነት የነበረ የኦርቶዶክስ አማኞች የሚያመልኩበት አበራ ጊዮርጊስ የሚባል ቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ የአብነት ተማሪዎች ከዚያ በፊት የድንበር ችግር በመኖሩ ድንጋዩን የሚወስዱት ድንበር ሊያካልሉ ነው በሚል ድንጋይ መወራወር ይጀምራሉ፤ በዚህ ሂደት አንደኛ ተከሳሽ የሆነው የቤተክርስቲያኑ ጥበቃ ጥይት ወደ ህዝቡ በመተኮስ ቦንብ እንዲወረወር በማድረጉ ምክንያት በዚያን ቅጽበት ብቻ ሶስት ሰዎች ሂይወታቸው አልፋል ብለዋል፡፡
ግጭቱ ተስፋፍቶ ወደ ከተማው በመሰራጨቱ በተከታታይ ቀናት የተለያዩ ግጭቶች መኖራቸውን የምርመራ መዝገባችን ያስረዳል ያሉት አቶ ፍቃዱ መጀመሪያ የጸጥታ ሀይሉ 509 ሰዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ 310 ወንጀል ውስጥ መሳተፋቸውን የሚያሳይ ማስረጃ ባለመገኘቱ ወዲያው እንደተለቀቁ ተናግረዋል፡፡

199 ቀድመው የተያዙና 17 ከዚያ በኋላ የተያዙ ሰዎችን አንድ ላይ በማድረግ በ216 ሰዎች ላይ የጊዜ ቀጠሮ እየተጠየቀ በአጭር ጊዜ ውስጥ 121ቹ ወንጀል ስለመፈጸማቸው ማስረጃ ባለመኖሩ እንዲለቀቁ ተደርጎ በአጠቃላይ 77 የተያዙ፣ 62 ያልተያዙ ሰዎች ላይ ምርመራ ሲጣራ ቆይቷል፡፡ መጨረሻ 250 የሰው ምስክሮች ከተሰበሰበቡ በኋላ በፍርድ ቤት ክስ ሊያስመሰርትባቸው በሚችል 103 ሰዎች ከሁለቱም ዕምነቶች ተለይተው ክስ ተመስርቶባቸዋል፤ 69 ተይዘው የታሰሩ 34 ደግሞ ተፈላጊዎች ሲሆኑ 24 የዕስልምና እምነት ተከታዮች፤ 79 ደግሞ የክርስትና ዕምነት ተከታዮች ናቸው፤ ከእነዚህም ውስጥ 3ቱ ሴቶች መሆናቸውን አቶ ፍቃዱ ተናግረዋል፡፡

ግጭቱ ባህሪው ቀድሞ ታስቦበት ያልነበረ በቀብር ስነ-ስርዓቱ ላይ የተፈጠረ ነገር ግን የሰፋ፤ የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታዮች የእስልምና ዕምነት ተከታዮችን የማምለኪያ ቦታ እና የንግድ እንዲሁም የመኖሪያ ቤቶችን በመምረጥ ጉዳት በማድረስ፤ የእስልምና ዕምነት ተከታዮችም ደግሞ አጸፋው የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታዮች የንግድ ቦታ ላይ ጉዳት ማድረሳቸውን የምርመራ ግኝታችን ያመለካክታልም ብለዋል ሚኒስትር ዴኤታው፡፡
አያይዘውም 20 ሰዎች ከሁለቱም ዕምነት በግጭቱ ለሞት ተዳርገዋል፣ ከ100 ሰዎች በላይ የአካል ጉዳት ደርሷል፣ 60 ሚሊዮን ግምት ያለው ንብረት ውድሟል፤ የዕስልምና ዕምነት ተከታች በዕምነቱ በኩል ያቋቋሟቸው ኮሚቴዎች ደግሞ ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ጉዳት ደርሷል ብሎ ያመጣ ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ በኩል ግን 60 ሚሊዮን የሚል እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

በስልጤ ዞን ከተፈጸመው ወንጀል ጋር በተያያዘ ወራቤ ሳንቁራ ወረዳ በአለም ገበያ ከተማና መንዝር ጦር በርበሬ ወረዳ በተባሉ አካባቢዎች የተፈጸመ ወንጀል በሚያዝያ 18 2ዐ14 ዓ.ም. ጎንደር የተከሰተውን ወንጀል ተከትሎ ማታ 2፡00 ሰዓት ከሰላት በኋላ አንድ አሰጋጅ እና አንድ ኡስታዝ ጎንደር የፈሰሰው ደም የናንተ ደም ነው፤ ጎንደር ሙስሊሙን የገደለው ክርስቲያን ነው ስለዚህ እንዲኖሩ መፍቀድ የለብንም ብለው የቀሰቀሱ በመሆኑ በማግስቱም ከቀኑ7፡00 ሰዓት ላይ በነበረው ሰላት ተመሳሳይ ቅስቀሳ በማድረጋቸው በትምህርት ቤቶችም በመቀስቀስ መስጊድ ተቃጥሏል ብሎ በማስወራት ወደ ብጥብጥ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡

በወራቤ ከተማ ቅዱስ ሩፋኤል በተባለ ቤተክርስቲያን ላይ ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ላይ በመሄድ ቤንዚል እና የተለያዩ ስለታማ ነገሮችን በመያዝ ውድመት መጀመራቸውን የወራቤ ዩኒቭርስቲ የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታዮች ቤተክርስቲያናችን ተቃጠለ ብለው በመምጣታቸው ብጥብጡ መባባሱን በአካባቢው ባለው መስጊድም ሊቃጠል ነው የሚል የአዛን ድምጽ በማሰማት የሰው ቁጥር እንዲመጣ ተደርጎ ቤተክርስቲያኑ መቃጠሉን የምርመራ መዝገቡ ያሳያል፡፡
ከላይ በተጠቀሱት ሌሎች ወረዳዎችም ጭምር 4 የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ቤተክርስቲያን ንዋየ ቅዱሳትን ጨምሮ እንዲሁም 3 የፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያናት መቃጠላቸውን እንዲሁም የዋጋ ግምቱ ወደ 46 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ንብረት መውደሙን የምርመራ ግኝቱ ያመላክታል፡፡
ሚኒስትር ዴዔታው እንደገለጹት ከሆነም የምርመራ መዛግብቱን መሰረት በማድረግ በ97 ሰዎች ላይ ክስ ተመስርቷል፡፡

በመጨረሻም ሚኒስቴር ዴኤታው በሁሉም ግጭት በተፈጸመባቸው ቦታዎች ውስጥ የጸጥታ መዋቀሩ ገብቶ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አንስተው፤ በቅርቡ በወለጋ ግንቢ አካባቢ የተፈጸመው ወንጀልን ጨምሮ መቻሬን እና ጋንቤላ የተፈጸመው ወንጀል ላይ ምርመራ እየተጣራ መሆኑን ተናግረው፤ ወንጀል ሀይማኖትንና ብሄርን የማይወክል መሆኑን በመገንዘብ በየደረጃ ያለው የመንግስት አደረጃጀትና ህብረተሰብ ትብብር ሊያደርግ ይገባል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

law
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

Ethioreview news

A journalist

አቶ ምትኩን በስኳር ያጠበው ኤልሻዳይ የትህነግ ድርጅት መሆኑ ተሰማ – የሚስጢር ምርመራ ይፋ ሆነ
የፌዴሬሽን ምክር ቤትየወልቃይት ጠገዴና የራያ የማንነት ጥያቄዎች መልስ እንዲያገኙ እየሠራ ነው
Related posts
  • Related posts
  • More from author
ART and CULTURE

አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ

May 17, 20260
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 20260
Load more
Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Read also
ART and CULTURE

አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ

May 17, 20260
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 20260
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 20260
Load more
Recent Posts
  • አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ May 17, 2026
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedbusinesshotarchivetips
    © Copyright 2026, All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2
    • Home Demo news