Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  OPINION  እየተገኘ ያለውን ወታደራዊ ድል በፖለቲካዊ ስራ ማፅናት ያስፈልጋል!
OPINION

እየተገኘ ያለውን ወታደራዊ ድል በፖለቲካዊ ስራ ማፅናት ያስፈልጋል!

Ethioreview newsEthioreview news—October 18, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

እኔና አንዳንድ በተለይም የአማራ ልጆች፤ በዚህ ጦርት ዙሪያ እንዲህ አይነት ምክረ-ሀሳቦችን ስንሰነዝር፤ የብልጽግና አመራ፤ ደጋፊ፤ ወይም ልዩ ተጠቃሚ ስለሆን አይደለም፡፡ በፍጹም አይደለንም፡፡ እኔና መሰሎቸ እንዲህ የምንብከነከነው፤ ወያኔ ተሳክቶለት በዚህ ጦርት አገራችን ከፈረሰች፤ ቲንሽም ብትሆን በየጃችን ያለው ነገር ሁሉ ከንቱ እንደሚቀር በደንብ ስለገባን ነው፡፡ ጦርነቱ የሚያስከትለው አሉታዊ ውጤት በፒፒ ላይ ብቻ ተወስኖ የሚቀር ቢሆን ኖሮ፤ ይሄንን ያክል ባልደከምን ነበር፡፡ ይሄንን የምለው አንዳንድ ወገኖች ለሀገር ሲባል የሚከፈልን ዋጋ ከቁስ ጥማትና ፍላጎት ጋር ለማያያዝ ስትሞክሩ ስለምታዘብ ነው፡፡ የቁስ ጥማትንም ቢሆን ማርካት የሚቻለው ኢትዮጵያ አገራችን በሰላም ውላ በሰላም ካደረች ብቻ ነው፡፡ ሁላችንም በዚህ መርህ እንመራ፡፡ የኢትዮጵያ ሰላም ውሎ ማደር ትርፍ ባናገኝ እንኳን ቢያንስ በእጃችን ያለውን ሁሉ አያሳጣንም፡፡

Chuchu Alebachew – ነጻ አስተያየት

1. ፈር መያዥያ

አሁን ጦርቱ በደረሰበት ደረጃ ሁነን ነገሮችን ስንገመግም የኃይል ሚዛኑ ተዛብቷል ብሎ መናገር ይቻላል፡፡ ይሄም ማለት ካሁን በፊት በተደጋገሚ ለማለት እደሞከርኩት፤ ባለፈው ጦርነቱ በቆመበት ጊዜ የመንግስትም ሆነ ወያኔ ወታደራዊ ቁመና ከሞላ ጎደል በአቻነት ደረጃ የሚታይ ነበር፡፡ ወያኔም እደዚህ አይነት ግምገማ ስለነበረው ነው 3ኛውን ዙር ወረራ በራያ በኩል የጀመረው፡፡ በነገራችን ላይ ወያኔ በዚይህ ግንባር ጦርነት የጀመረው የመንግስትን እና የህዝብን ትኩረት ለማዛበት እጅ፤ ዋነኛ ግቡ የነበረው ደባር ዘልቆ፤ ወደ ጎንደር አቅንቶ ወያኔ ሲዝት እንደከረመው ጎንደር ከተማን ወደ ታሪክነት ቀይሮ ወደ መተማ እና ወልቃይት በመጠምዘዝ የሁመራን ኮሪደር በማስከፈት ማእከላዊ መንግስቱን ለመጣል የሚያስችለውን ሁለንተናዊ አቅም መገንት ነበር፡፡ በህልም የቀረው እውነተኛው የወያኔ የ3ኛው ዙር የወረራ እቅድ ይህ ነው፡፡

More stories

“በነዉጥና በኃይል የበለፀገ ሀገር የለም”

May 2, 2023

ወያኔያዊ አማራነትን አማራ “አማራ ነኝ”

December 6, 2022

ሰውን “ሰው” የሚያደርገው ምንድነው? ከእኛ ይልቅ የጥንቶቹ ዘመናዊ ነበሩ

November 1, 2024

ወግ አጥባቂው የኦክላሆማ ሴናትር ማ’ናቸው?

October 6, 2022

ነገር ግን ወያኔ አንድ በውል ያልገመገመው እውነታ ነበር፡፡ ይሄውም መንግስትና ወያኔ በአቻነት ጦርነቱን አቁመው የየራሳቸውን አቅም ወደ መገንባት በተሸጋሩበት ወቅት፤ የኢትዮጵያ መንግስት መከላከያውንና ሎጅስቲኩን ከማጠናከር አንጻር ከወያኔ በብዙ እጥፍ የተሻለ ነበር፡፡ ሁላችንመ እንደምናስተውሰው፤ ጦርነቱ ቁሞ በቆየባቸው 5/6 ወራት ወያኔ በዘረኛ ፕሮፓጋንዳው አማካኝነት በርካታ የትራይ ወጣቶችን ለውትድርና መመልመልና ማሰልጠን ከመቻሉም በላይ፤ ከታሪካዊ ጠላቶቻችን በውል ያልታወቀ የመሳሪያና ትጥቅ ድጋፍ አከማችቶ ነበር፡፡ ይህ ሁኔታ የወያኔን ልብ አሳበጠው፤ የተሳሳተ ውሳኔ ላይ እንዲደርስም አደረገው፡፡ አንዳዴ ልብህ ሲደፈን አስቸጋሪ ነው፡፡ ወያኔ እሱ ይሄንን ያክል ሲዘጋጅ፤ ከሱ በብዙ እጥፍ የበለጠ የሰው ኃይልና ሪሶርስ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ መንግስት ከሱ የበለጠ ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚችል እንዴት ለመገምገም እንደተሳነው ይገርማል፡፡

በአንጻሩ በእነዚያ የእፎይታ ወራት፤ የኢትዮጵያ መንግሰት ከወያኔ በብዙ እጥፍ የበለጠ አቅም ስላለው፤ ከወያኔ የተሻለ ዝግጅት ሲያደርግ እንደከረመ ለመገመት አይከብድም፡፡ የፌደራሉ መንግስት ይሄንን ያደረገው ” ለሁሉም ፌጦ መድሀኒት ነው” በሚል መርህ ተመርቶ እንደሆነ እሙን ነው፡፡ ይሄም ሲሆን በሁለት ምክንያቶች እንደሆነ መገመት ይቻላል፡፡ የመጀመሪያው ጉዳይ ከወያኔ ጋር የተጀመረው የሰላ ድርድር ሊሳከ ባይችል ቀጣዩ መፍትሄ ጦርት ስለሚሆን የላቀ ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ ነው የሚል እምነት መያዙን መገንዘብ ይቻላል፡፡ ሁለተኛው ምክያት ደግሞ ከወያኔ ጋር የተጀመረው የሰላም ድርድር ቢሳካ እንኳን፤ ኢትዮጵያ ግዙፍና ጠንካራ የመከላከያ ኃይል እድትገነባ የሚያስገድዷት ውጫዊ ምክንያቶች ስላሉ፤ግዙፍና ጠንካራ ሰራዊት የመገንባቱ አጀንዳ የሚታለፍ አልነበረም፡፡ በመሆኑም ባለፉት የተኩስ አቁም ወራት ኢትዮጵያ ወያኔ ከጠበቀውና ካሰበው በላይ ግዙፍና ጠንካራ የመከላከያ ኃይል መገንት ቻለች፡፡ ወያኔ ይሄንን ጉዳይ በደንብ ሳያጤን በጀብድ ተነሳስቶ ጦርነት በክፈቱ እነሆ በአጭር ቀናት ጊዜ ውስጥ ብቻ ለዚህ በቃ፡፡ ወያኔ ይህ የተሳሳተና ያልተጠና ውሳኔው ምን ያክል ለፀፀት እንደዳረገው የሚያውቁት የውሳኔው ፊታውራዎቹ ጀኔራሎች ናቸው፡፡

ያም ሆነ ይህ ወያኔ የከፈተውን ጦርነት ሲከላከል የከረመው የሀገር መከላከያ ሰራዊት፤ ወደ ፀረ-ማጥቃት መሸጋገሩንና ትግራይ ውስጥ ድረስ ዘልቆ በመግባት ቢያንስ የፌደራል ወሳኝ ተቋማትን እንደሚጠብቅ ግልጽ አድርጓል፡፡ ይህ እርምጃ እዛው እንዳለ የትግራይን ህዝብ ከመከራ እደሚያላቅና የተቀላጠፈ ሰብኣዊ ድጋፍ ለማድረግም እንደሚያስችል መንግስት ግልጽ አድርጓል፡፡ በዚህም መሰረት ከወዲሁ በርካረታ በወራሪው ኃይል ተይዘው የነበሩ የአማራ አካባቢዎችና አንዳንድ የፕሮፐር ትራይ አካባቢዎች ነጻ መውጣት ጀምረዋል፡፡ ይህ ሁኔታም በቀጣዮቹ ቀናት/ወራት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ይጠበቃል፡፡

2. ወታደራዊ ድሉ በጠንካራ ፖቲካዊ ስራ መደገፍ አለበት፡-

ሁላችንም እደምናስተውሰው በህግ ማስከበር ዘመቻው ወቅት ትግራይ ውስጥ ከወያኔ ጋር የተካሄደውን ጦርነት በአጭር ቀናቶች ውስጥ ነበር ማጠናቀቅ የተቻለው፡፡ ነገርግን ሰራዊታችን ዋናውን ጦርነት በድል ካጠናቀቀ በኃለም ቢሆን ፤ ትራይ ውስጥ በቆየባቸው 8 ወራት ውስጥ ለአንድም ቀን እረፍት አላገኘም ነበር፡፡ ይህ የሆነው የትግራይን ህዝብ ከመንግስት ጎን ማሰለፍ ባለመቻሉ የመጣ ችግር ነበር፡፡ ይህ በመሆኑም ከ8 ወር በኃላ ሰራዊታችን ትግራይ ውስጥ የገጠመውን ፈተና ሁላችንም አይተናል፡፡ ከ መቶ ቢሊየን ብር በላይ በጀት ተመድቦ መሰረተ ልማቱን ለመጠገን፤ በመንግስት ድጋፍ የተደረገለት የትራይ ህዝብ፤ የመንግስትን በጎ ስራ ከምንም ሳይቆጥር አብዛኛው በወያኔ ዘረኛ ፕሮፓጋንዳ ተሰልቦ ፀረ-መንግሰት አቋም ወሰደ፡፡ በዚህም በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ትግራይ ውስጥ ለሁለተኛ ጊዘ ታሪክ ይቅር የማይለው ጥፋትና ክህደት በመከላከያ ሰራዊታችን ላይ ተፈጸመ፡፡

አሁን ላይ መንግሰት የግድ ህገ-መንግስታዊ ኃላፊነት አለብኝ በሚል መነሻነት ሰራዊቱን ወደ ትራይ ክልል ማስገባት ጀምሯል፡፡ እንደ አያያዙ ከሆነ ዳግም ትግራይን ለቆ ይወጣል ተብሎ አይገመትም፡፡ በእኔ እምነትም ቢሆን መንግሰት ወይ ሰራዊቱን ወደ ትግራይ ውስጥ ባላስገባ እንጅ፤ ካስገባ በኃላ ዳግም ትግራይን ለቆ መውጣት የሚታሰብ መሆን የለበትም ባይ ነኝ፡፡ አሁን ላይ ሁላችንም አንድ ተስፋ አለን ብየ አስባለሁ፡፡ ይሄውም መንግስትም ሆነ ሰራዊታችን ካለፈው የትግራይ ቆይታቸውና ከገጠማቸው ፈተና አንጻር ብዙ ትምህርት ወስደዋል፡፡ ለዚህ ነው ጦርነቱ የሰከነና የተረጋገ፤ ግረግርና ጩኸት የማይሰማበት ሁኖ እየቀጠለ ያለው፡፡ ስለሆነም አሁን ትግራይ ውስጥ የሚኖረው የመንግስትና የሰራዊታችን ቆይታ እጅግ የሰከነ፤ገርግርና ወከባ የማይታይበት፤ የተሻለ አመራር የሚሰጥበት፤ የትራይ መልሶ ግንባታ በፍጥነት የሚጀመርበት፤የትራይ ህዝብ እውነታውን እንዲረዳና ከመንግስት ጎን ለማሰለፍ ብርቱ ስራ የሚሰራበት፤ በአጠቃላይ ከባለፈው ስህተት ትምህርት ተወስዶ የሚከወን እንቅስቃሴ እንደሚሆን የብዙዎቻን ተስፋ ነው፡፡

ይሁን እንጅ መንግስትም ሆነ መከላከያ ሰራዊታችን ትግራይ ውስጥ ዘልቀው ሲገቡም ሆነ መሰረታቸውን እንደገና ሲያደላድሉ ፤ምንም ያክል በጎ ስራ ቢሰሩ ከብዙዎቹ የምዕራባዊ አገራትና አሜሪካ አንጻር በጎ ምላሽ አይኖርም፡፡ እነዚህ አገራት አላማቸው ሌላ ነው፤ ወያኔ በሂዎት እዲኖር ይፈልጋሉ፡፡ ስለሆነም ይህ ጦርት እንዲቆምና ወደ ድርድር እንዲገባ ብርቱ ግፊት ከማድረጋቸውም በላይ፤ ያልተጠበቁ እርምጃዎችን እስከመውሰድና ማስወሰድ ሊደርሱ ይችላሉ፡፡ ስለሆነም እኛ ኢትዮጵያዊያንም ይህ ሁኔታ ሊከሰት እንደሚችል አውቀን ከወዲሁ በዚህ ልክ መዘጋጀት ይኖርብናል፡፡ በተለይም አውዳሚ ክሶቻቸውን በማጋለጥና በመመከት፡፡

3. ከኛ ምን ይጠበቃል ?

ተደጋግሞ እንደተነገረው በዚህ ወቅት አገራችን የገባችበት ጦርት የህልውና ጦርት ነው፤ አገርን የማስቀጠል ወይም እንድትፈርስ የሚወስን ጦርነት፡፡ መቸም ቢሆን አንዳድ ፖለቲካዊ ልዩነቶች ያላቸው ወገኖች ቢኖሩም/ አሉም፤ ጤነኛ የሆነ አዕምሮ ያለው ኢትዮጵያዊ ዜጋ አገሩ እንደትፈርስ ይፈልጋልለዚህም ይተባራል ተብሎ አይታሰብም፡፡ ስለሆነም አገሩ እንዳትፈርስ የሚፈልግ ዜጋ ሁሉ ከሱ የሚጠበቀውን ሁሉ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከዚህ ተነስቸ ሁላችንም ኢትዮጵያዊያን ለሀገራችን ህልውና ስንል፤ በሚከተሉት ነጥቦች ዙሪያ አትኩረን የበኩላችንነ ድርሻ አጠናክረን ልንቀጥል ይገባል እላሁ፡-

1. የሎጅስቲክ ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል፡፡ በተለይም ካሁን በኋላ ትግራይ ውስጥ ህዝቡ ኢኮነሚያዊ አቅሙ እስኪያገግምና ወደ ቀልቡ ተመልሶ ለሰራዊታችን ደጀን እስከሚሆን ድረስ፤ የመሀል አገሩ ሰው ትግራይ ውስጥ ድረስ ዘልቆ በመግባት ሁለንተናዊ ድጋፉን አጠናክሮ መቀጠል አለበት፡፡ ይህ ለአፍታም ሊዘነጋ የማይገባው አጀንዳ ሊሆን ይገባል፡፡

2. የተሳሳቱና በሀገር ላይ የሚሰነዘሩ ውንጀላዎችን ማክሸፍ፡- ከሁሉ በፊት አንዳድ የውስጥም ሆኑ የውጭ አካት፤ከገባንበት የህልውና ጦርት ጋር አያይዘው በአገራችን ላይ የሚያነሷቸውን ወሳኝ ውንጀላዎች በውል መረዳት ያስፈልጋል፡፡ በእኔ እይታ ከገጠመን የህልውና ጦርነት ጋር በተያያዘ በመንግስት/ ሀገር ላይ የሚቀርቡት ክሶች በርካታ ቢሆኑም፤ ዋና ዋናዎቹ ክሶች ግን በሦስት ተከፍለው ሊታዩ የሚችሉ ናቸው እላለሁ፡፡ እነዚህም ትግራይ ውስጥ ”ጀኖሳይድ“ ተፈጽሟል፤ የፌደራሉ መንግስት ”ረሀብን እንደ ጦር መሳሪያ ጥቅም ላይ አውሏል/እያዋለ ነው” ፤ የፌደራሉ መንግስት የኤርትራን ጦር ወደ የኢትጵያ እንዲገባ በማድረግ የሀገሪቱን ሉዓላዊነት እንዲደፈር አድረጓል፤ስለሆነም፤ የኤርትራ ጦር ከትራይ ይውጣ የሚሉ ናቸው፡፡

በዚህ በኩል ከየራሰችን ግንዛቤ እየተነሳን ለክሶቹ መልስ መስጠት ያለብን መሆኑ እንዳለ ሁኖ፤ በተለይም በመንግስት ደረጃ ደግሞ በደንብ አርቲኩሌት ተደርገው የሚቀረጹ አጀንዳዎች ቢኖሩ የተናበበና የተሳካ አገራዊ ትግል ለማካሄድ ያመቻል ባይ ነኝ፡፡ የእነዚህ ክሶች ተጥዕኖ በገዥው ፓርቲ ፒፒ ላይ ብቻ ታጥረው የሚቀሩ አይደሉም፡፡ ውለው አድረው እንደ ሀገር ዋጋ የሚያስከፍሉ ናቸው፡፡ ስለሆነም ሀገራዊ ምለስ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ስለዚህ ከሁሉ በፊት የክሶቹን ባህሪና መነሻ በውል መመርመር ያስፈልጋል፡፡ ቀጥሎ የተናበበና ሀገራዊ ምለሽ መሰጠት ነው፡፡ ለምሳሌ፡-

1. ከጆኖሳይድ አንጻር ለሚቀርበው ውንጀላ፤ እንደ ሀገር መሰጠት ያለበት መልስ ምን መሆን/ መምሰል አለበት?

2. መንግስት ረሀብን እንደ ጦር መሳሪያ ተጠቅሞበታል/ እየተጠቀመበት ነው ለሚለው ክስ ምን አይነት ምላሽ ነው መሰጠት ያለበት?

3. ከኤርትራ ጋር ተያይዞ ስለሚነሳው ክስስ ምላሻችን ምንድን ነው መሆን ያለበት?

በአጠቃላይ በእኔ እምት እነዚህ ክሶች ወሳኝ፤ ከሀገር ህልውና እና ክብር ጋር የተያያዙ ስለሆነ፤ ምላሻችን የተደራጀና እንደ ሀገር ቢሆን ይሻላል እላለሁ፡፡

በመጨረሻም እኔና አንዳንድ በተለይም የአማራ ልጆች፤ በዚህ ጦርት ዙሪያ እንዲህ አይነት ምክረ-ሀሳቦችን ስንሰነዝር፤ የብልጽግና አመራ፤ ደጋፊ፤ ወይም ልዩ ተጠቃሚ ስለሆን አይደለም፡፡ በፍጹም አይደለንም፡፡ እኔና መሰሎቸ እንዲህ የምንብከነከነው፤ ወያኔ ተሳክቶለት በዚህ ጦርት አገራችን ከፈረሰች፤ ቲንሽም ብትሆን በየጃችን ያለው ነገር ሁሉ ከንቱ እንደሚቀር በደንብ ስለገባን ነው፡፡ ጦርነቱ የሚያስከትለው አሉታዊ ውጤት በፒፒ ላይ ብቻ ተወስኖ የሚቀር ቢሆን ኖሮ፤ ይሄንን ያክል ባልደከምን ነበር፡፡ ይሄንን የምለው አንዳንድ ወገኖች ለሀገር ሲባል የሚከፈልን ዋጋ ከቁስ ጥማትና ፍላጎት ጋር ለማያያዝ ስትሞክሩ ስለምታዘብ ነው፡፡ የቁስ ጥማትንም ቢሆን ማርካት የሚቻለው ኢትዮጵያ አገራችን በሰላም ውላ በሰላም ካደረች ብቻ ነው፡፡ ሁላችንም በዚህ መርህ እንመራ፡፡ የኢትዮጵያ ሰላም ውሎ ማደር ትርፍ ባናገኝ እንኳን ቢያንስ በእጃችን ያለውን ሁሉ አያሳጣንም፡፡

ድል ለመከላከያ ሰራዊታችን በሱ ስር ለሚመሩት ሁሉም የፀጥታ ኃይሎቻን!

OPINION
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
መንግስት በትግራይ የተቋረጠውን አገልግሎት ሊያስጀምርና ርዳታ ሊያቀርብ መሆኑን ይፋ አደረገ
ኢትዮጵያ የተሞከረባትን ከ1 ሺህ 600 በላይ የሳይበር ጥቃቶች አከሸፈች
Related posts
  • Related posts
  • More from author
OPINION

እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ…

April 8, 2026
OPINION

ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት!

April 8, 2026
OPINION

ሙስጠፌ ተረኛው ባለስልጣን – የሃሰት ትርክ ዘመቻ በደቦ

March 28, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2