Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News2  የነዳጅ ድጎማ ተግባራዊ በመደረጉ 29 ቢሊዮን ብር ወጪ ማዳን ተችሏል
News2

የነዳጅ ድጎማ ተግባራዊ በመደረጉ 29 ቢሊዮን ብር ወጪ ማዳን ተችሏል

Ethioreview newsEthioreview news—December 18, 2022
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ባለፉት አምስት ወራት የታለመ የነዳጅ ድጎማ ተግባራዊ በመደረጉ 29 ቢሊዮን ብር ወጪ ማዳን መቻሉን የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ገለጸ። በእነዚህ ወራትም መንግስት ለህዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ለነዳጅ ድጎማ ሶስት ቢሊዮን ብር ወጪ ማድረጉን አመልክቷል፡፡

በባለስልጣኑ የነዳጅ ውጤቶች የገበያ ጥናት ዳይሬክተር አቶ ለሜሳ ቱሉ እንደገለጹት፤ የታለመ የነዳጅ ድጎማን ተግባራዊ ማድረግ ያስፈለገበት ዋና ምክንያት የጅምላ ድጎማ ለማስቀረትና የነዳጅ ዕዳ ለመክፈል ታስቦ ነው።

በጥቅል ድጎማ በነበረ ወቅት በየወሩ መንግስት ከ10 እስከ 14 ቢሊዮን ብር አላስፈላጊ ወጪ ያወጣ እንደነበር ገልጸው፤ ለወጪው ትልቁ መንስኤ መንግስት በጅምላ ድጎማ ሲያደርግ ስለነበርና ነዳጅን ከውጭ ካስገባበት ዋጋ በከፍተኛ ቅናሽ ለገበያ በማቅረቡ ነው ብለዋል።

ባለፈው ዓመት 2014 ዓ.ም ሰኔ ወር ብቻ እስከ 14 ቢሊዮን ብር ኪሳራ ደርሶ ነበር ያሉት ዳይሬክተሩ፤ የነዳጅ ዋጋ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየጨመረ በመምጣቱ ነዳጅን እንደ ሀገር ማቅረብ የማይቻልበት ደረጃ ላይ ይደረስ እንደነበር አስታውሰዋል።

More stories

ጓደኛቸውን ገድለው  ሲያሽከረክረው የነበረውን መኪና ወስደው የተሰወሩ ሁለት ተጠርጣሪዎች ተያዙ

May 21, 2024

የብሪክስ ፕላስ የመረጃና እና የባህል ሚዲያ ማዕከል ተመሰረተ

October 15, 2024

” የሎንግ ኦነግ ሸኔን መክዳት ከዜና በላይ ነው” – የሸኔ የሎጂስቲክ መረጃ መንግስት እጅ ገባ

February 18, 2024

“የቴህራን የአየር ክልል በኛ ቁጥጥር ስር ሆኗል” እስራኤል

June 16, 2025

መንግስት የጅምላ የነዳጅ ድጎማን በማንሳት መክፈል የሚችለው በራሱ ገዝቶ እንዲጠቀምና አነስተኛ ገቢ ያለው ህብረተሰብ ክፍል ደግሞ የታለመ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ እንዲሆን ለህዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች የተለመለት የነዳጅ ድጎማ ስርዓት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረጉን ተናግረዋል።

የታለመ የነዳጅ ድጎማ ተግባራዊ በመሆኑም በየወሩ ከ10 እስከ 14 ቢሊዮን ብር በጅምላ የነዳጅ ድጎማ ሲደርስ የነበረውን አላስፈላጊ ወጪ አስቀርተናል ያሉት አቶ ለሜሳ፤ አሰራሩ ተግባራዊ ባይሆንና በጅምላ ድጎማ ብንቀጥል ባለፉት አምስት ወራት ብቻ እስከ 60 ቢሊዮን ብር ኪሰራ ይደርስ ነበር ብለዋል።

የታለመ የነዳጅ ድጎማ ተግባራዊ በመደረጉም ይደርስ የነበረውን ወርሃዊ ኪሳራ ከ14 ቢሊዮን ወደ 5 ቢሊዮን ዝቅ ማድረግ በመቻሉ ባለፉት አምስት ወራት የታለመ የነዳጅ ድጎማ ተግባራዊ በመደረጉ 29 ቢሊዮን ብር ወጪ ማዳን ተችሏል ብለዋል።

የታለመው የነዳጅ ድጎማ ስርዓት የመንግስት ወጪና ኪሳራን መቀነስ ብቻ ሳይሆን በዘርፉ የሚፈፀመው ኮንትሮባንድና ህገ ወጥ ንግድን ጨምሮ የነዳጅ ብክነትን መቀነሱን ገልጸዋል።

መንግስት ለታለመለት የነዳጅ ድጎማ ወጪ እስከ ህዳር 30 ቀን 2015 ዓ.ም 3 ቢሊዮን ብር ማውጣቱን ጠቅሰው፤ ገንዘቡ ህዝቡ ዘንድ የማይደርስና ህገወጦች ኪሳቸውን የሚሞሉበት ከሆነ ድጎማው ቀርቶ ገንዘቡ ወደ ሌላ አማራጭ መዞር አለበት ነው ያሉት።

በሌላ በኩል አቶ ለሜሳ ቱሉ እንደገለጹት፣ መንግስት የዝቅተኛ ገቢ ያለው ማህበረሰብ ክፍል የኑሮ ጫናን ለማቃለል መንግስት የታለመ ዓላማ ያለው የነዳጅ ድጎማ እያደረገ ነው። ከሀምሌ ወር ጀምሮ እስከ ህዳር 2015ዓም ድረስ ለታለመለት የነዳጅ ድጎማ ሶስት ቢሊዮን ብር ወጪ አድርጓል።

የታለመለት የነዳጅ ድጎማ ባይኖር ኖሮ ህብረተሰቡ በስድስት ብር የሚወስደውን መንገድ 15ብር፤ 15ብር የሚሄደውን 30 ብር ይጓዝ እንደነበር ተናግረዋል። ይህም የትራንስፖርት ወጪ በኑሮው ላይ የሚፈጥረው ጫና ቀላል አይሆንም ነበር ብለዋል።

በታለመለት የነዳጅ ድጎማ ህብረተሰቡ በተገቢው መልኩ ተጠቀመ ማለት አይቻልም ያሉት ዳይሬክተሩ፣ አዲስ አበባን ጨምሮ በከተሞች አልፎ አልፎ ከሚታዩ ችግሮች በስተቀር ድጎማ ተጠቃሚ የህዝብ ተሽከርካሪዎች በተቀመጠላቸው ታሪፍ እየሰሩ ቢሆንም በዞኖች፣ በወረዳዎች ግን ታሪፍ በአግባቡ እየተተገበረ አለመሆኑን ጠቅሰዋል።

ለአብነትም ከአዲስ አበባ አምቦ ታሪፉ 106 ብር ቢሆንም የድጎማ ነዳጅ ተጠቃሚ የህዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች 130 እስከ 150 ብር ድረስ እንደሚያስከፍሉ ተናግረዋል።ይህም የሆነው ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት ተናበው መስራት ባለመቻላቸው ነው ብለዋል ።

አነስተኛ ገቢ ያለው ህብረተሰብ ክፍል በነዳጅ ድጎማው በአግባቡ ተጠቃሚ እንዲሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት የትራንስፖርት ታሪፍ በትክክል ማስፈጸም ይኖርባቸዋል ብለዋል።

በኢትዮጵያ የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም የታለመው የነዳጅ ድጎማ አተገባበር እና በአፈፃፀም ሂደት ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን የዳሰሰ የጥናት ውጤት ይፋ ያደረጉት በተቋሙ የጥናት ቡድን መሪ አቶ ታደሰ ጣሰው፤ኅብረተሰቡ ከታለመለት የነዳጅ ድጎማ አሠራር ተጠቃሚ መሆኑን ለማረጋገጥ እና በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመለየት እንዲሁም ቀጣይ የመፍትሔ እርምጃ ለመውሰድ ያለመ ጥናት መካሄዱን ገልጸዋል።

የነዳጅ ድጎማው የመንግሥትን ወጪ ለመቀነስ፣ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ፣ዝቅተኛ ገቢ ያለውን ኅብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ ማድረግ፣ በነዳጅ ላይ የሚስተዋለውን ኮንትሮባንድ ንግድ እና ብክነትን ለማስወገድ ያለመ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

ይሁን እንጂ የታለመለት የነዳጅ ድጎማ አተገባበር ሰፊ ክፍተቶች እና ችግሮች የሚስተዋሉበት መሆኑን በጥናቱ አመልክተዋል። በተለይ የነዳጅ ማደያዎች እና ቸርቻሪዎች አካባቢ ሌብነት ፣ሕገ-ወጥነት እና ብክነት በስፋት የሚስተዋሉ መሆኑን ተናግረዋል።

ድጎማውን ከኅብረተሰቡ ይልቅ አሽከርካሪዎች ያላግባብ እየተጠቀሙበት እንደሆነ ጥናቱ ማመላከቱን ገልጸው፣ ድጎማ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች መደበኛ አገልግሎት መስጠት ትተው በኮንትራት ሥራ ላይ እንደሚሰማሩና ድጎማ የተደረገለትን ነዳጅ ቀድተው የተፈለገውን አገልግሎት የማይሰጡ መሆኑን ተናግረዋል።

የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ ሆነው የ90 ብር ታሪፍ እስከ 200 ብር እንዲሁም የ300 ብር ታሪፍ እስከ 600 ብር እያስከፈሉ መሆኑን ጥናቱ አሳይቷል ነው ያሉት።
ለዚህ ደግሞ በትራንስፖርት ስምሪት አካባቢ የተቀናጀ ስምሪት እና ቁጥጥር ያለመኖር፣ የንግድ እና የትራንስፖርት ዘርፉን የሚመሩ የሥራ ኃላፊዎች እና ሙያተኞች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ያለመወጣትና የተቀናጀ አሰራር ላይ ሰፊ ክፍተት መፈጠሩን ጠቅሰዋል።

ችግሮቹን ለመፍታት የባለድርሻ አካላት የተቀናጀ አሠራር ማጠናከር፣ ድጎማውን የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን በ’ጂፒ ኤስ’ ቴክኖሎጂ መቆጣጠር እንደሚገባ አመልክተው፤የታለመለት የነዳጅ ድጎማ ዓላማን መሠረት ያደረገ አሠራርና የፖሊሲ ማዕቀፍ ማዘጋጀት እንደሚገባም ጠቁመዋል።

በጌትነት ምህረቴ
አዲስ ዘመን ታህሳስ 9/2015

home
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ተንቀሳቃሽ ንብረትን ዋስትና በማስያዝ የብድር አገልግሎት ማግኘት የሚያስችለው አዋጅ በቅርቡ ይፋ ይደረጋል
ትህነግ መንግስትንና “ወራሪ ሃይል” ያለውን አማራን ከሰሰ፤ መንግስት ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News2

ብሔራዊ ጥቅምን አሳልፎ ለመስጠት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ባለድርሻ ሊሆኑ አይገባም – በለጠ ሞላ

March 8, 2026
News2

ለክቡር የኢፌዴሪ ማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኝና ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው የቀረበ ጥሪ

March 8, 2026
News2

ስምረት ፓርቲ የትግራይ ወጣት ለትህነግ ጀርባ መስጠቱን አስታወቀ

March 6, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2