Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  SOCIETY  ኢሰመኮ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች የጸጥታ ሃይሎችን ጨምሮ ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታወቀ
SOCIETY

ኢሰመኮ ሁለት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች የጸጥታ ሃይሎችን ጨምሮ ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታወቀ

Ethioreview newsEthioreview news—June 1, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በሸገር ከተማ ከመስጊዶች መፍረስ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን እና የደረሰ ጉዳትን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በተለይም በአዲስ አበባ አንዋር መስጊድ ውስጥ እና በተወሰኑ አካባቢዎች በሸገር ከተማ በመንግሥት አካላት ከፈረሱ መስጊዶች ጉዳይ ጋር ተያይዞ የተነሱ ተቃውሞዎችን ተከትሎ የደረሰውን የሰዎች ሞት እና ጉዳቶችን በተመለከተ ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ ከመንግሥት የጸጥታ አካላት ኃላፊዎች፣ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች የሕክምና አገልግሎት ካገኙባቸው የጤና ተቋማት ኃላፊዎች፣ ዐይን እማኞች እና ከተጎጂዎች ማስረጃ በማሰባሰብ እና ክትትል በማድረግ ላይ ይገኛል።

ኢሰመኮ ይህ መግለጫ እስከወጣበት ጊዜ ባሰባሰበው መረጃና ማስረጃዎች መሠረት የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎችና የአድማ ብተና ኃይል ወደ ታላቁ አንዋር መስጊድ ግቢ ጭምር በመግባትና አስለቃሽ ጋዝ በመተኮስ ምእመናንን እና የተሰበሰበውን ሰው ለመበተን እንቅስቃሴ ማድረጋቸውን ተከትሎ በተፈጠረው ሁከት የ2 ሰዎች ሕይወት ማለፉን፣ በርካቶች ላይ አካላዊ ጉዳት መድረሱን፣ በጸጥታ ኃይል አባላት ላይም ጉዳት መድረሱን እና በወቅቱ ወደ 140 የሚሆኑ ሰዎች በጥፋት ተጠርጥረዋል በሚል በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉ መሆኑን ኢሰመኮ ለመረዳት ችሏል፡፡

በተጨማሪም ግንቦት 18 እና 19 ቀን 2015 ዓ.ም. በቁጥጥር ስር ውለው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ፣ በአውቶብስ ተራ እና በመርካቶ ፖሊስ ጣቢያ የተያዙ ሰዎችን በመጎብኘት ክትትል አድርጓል፤ ተጠርጣሪዎቹ በቤተሰባቸው ሲጎበኙ ተመልክቷል። ቅዳሜ ግንቦት 19 ቀን 2015 ዓ.ም. የተያዙት ተጠርጣሪዎች ደግሞ ሰኞ ግንቦት 21 ቀን 2015 ዓ.ም. በተመሳሳይ ችሎት ቀርበዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ለመርማሪ ፖሊስ 10 የምርመራ ቀናትን በመፍቀዱ ተጠርጣሪዎቹ ለግንቦት 29 ቀን 2015 ዓ.ም. ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ትዕዛዝ መሰጠቱን ኮሚሽኑ ተመልክቷል፡፡

ኮሚሽኑ ያነጋገራቸው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ኃላፊዎች ምክር ቤቱ የእራሱን ምርመራ በማድረግ ላይ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ የመንግሥት የጸጥታ ኃላፊዎች በበኩላቸው የደረሰውን ጉዳት በማጣራት እና ጉዳት ያደረሱ የጸጥታ አካላትን ለመለየት ምርመራ በማድረግ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተለይም በክስተቱ የሞቱ እና አካል ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች ጉዳይ በሚመለከት ከአዲስ አበባ እና ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽኖች የተውጣጣ የምርመራ ቡድን መቋቋሙን ኃላፊዎቹ አስረድተዋል፡፡

More stories

ወገኛ ምርኮዎች !!

August 27, 2021

በዓለም ባንክና በኢትዮጵያ መንግሥት የሚተገበር የ550 ሚሊዮን ዶላር ፕሮጀክት ዛሬ በይፋ ይጀመራል

January 29, 2022

በድንገተኛ የሞተር ብልሽት የፖላንድ አውሮፕላን አዲስ አበባ አረፈ

September 18, 2021

ኤርትራዊያን ስደተኞች “አሸባሪው ወራሪሃይል ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ፈጽሞብናል” ሲሉ የዓለም ሕብረተሰብ ተማጸኑ

February 23, 2022

ኢሰመኮ እነዚህን ማስረጃዎች እና ግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም. በመንግሥት አካላት በተወሰዱ እርምጃዎች ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎችንም ማስረጃ ጨምሮ የሚያደርገውን ክትትል የሚቀጥል ይሆናል። ይሁንና የመንግሥት የጸጥታ አካላት በማንኛውም ዓይነት ሰላማዊ ሕዝባዊ ሰልፎች፣ ሃይማኖታዊ እና ሌሎች ስብስቦችን አላስፈላጊና ተመጣጣኝ ካልሆነ እና ሞት ከሚያስከትል የኃይል እርምጃ ከመውሰድ እንዲቆጠቡ በድጋሚ ያሳስባል፣ ይህንን ዓይነት ኃይል መጠቀም በተመለከተም ግልጽ አመራር ሊሰጥ እንደሚገባ ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ያቀረበውን ጥሪ በድጋሚ ያስታውሳል።

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ አክለውም የመንግሥት የጸጥታ አካላት አላስፈላጊና ተመጣጣኝ ያልሆነ ኃይል የመጠቀም አዝማሚያ እየጨመረ መምጣቱን እና በዚህም ሳቢያ በሰዎች ላይ ሞት፣ የአካል እና የሥነ ልቦና ጉዳት እንዲሁም ሌሎች የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች እየደረሱ መሆናቸውን ኮሚሽኑ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጨምሮ በተለያየ ወቅት ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ማመልከቱን እና ውትወታ በማድረግ ላይ መሆኑን ገልጸዋል። “በተለይም ሰላማዊ የሆኑ ሃይማኖታዊ ስብስቦች ወቅት የሚወሰድ እርምጃ በተለይም የመንግሥት የጸጥታ አካላትን ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚጠይቅ መሆኑን በድጋሚ እናሳስባለን” ያሉት ዶ/ር ዳንኤል፣ ለሰው ሕይወት እልፈትና አካል ጉዳት ተጠያቂ የሆኑ የጸጥታ አካላት ተለይተው በሕግ እንዲጠየቁ፣ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎች ወንጀል ስለመፈጸማቸው በቂ ጥርጣሬ ከሌለ እና ተዓማኒ ክስ የማይቀርብ ከሆነ በአፋጣኝ እንዲለቀቁ ወይም በሕግ አግባብ በእስር ላይ ያሉ ሰዎች የዋስትና መብት ሊከበር ይገባል ብለዋል።

SOCIETY
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
አዲስ አበባና በሸገር ከተሞች የፈረሱትን ቤቶችና ማህበራዊ ቀውስ አስመልክቶ ኢሰመኮ መገለጫ አወጣ
ፌደራል ፖሊስ ሆን ብለው ሐሰተኛ መረጃ በሚያሰራጩ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል አለ
Related posts
  • Related posts
  • More from author
SOCIETY

አስጨናቂዋን ሰዓት ወደ ደስታ የቀየረው የኢትዮጵያዊያን የሕክምና ባለሙያዎች ስኬት

August 23, 2025
News

በ2018 ጓደኞቼ ዩኒቨርስቲ ይገባሉ፤ በድህነት ከተማ ሄዶ መማር ይልቻለው ታዳጊ ለቅሶ!

August 22, 2025
SOCIETY

“በጠለምት ወረዳ በዝናብ እጥረት ሳቢያ እንስሳት እየሞቱ ነው፤ ሕዝብ እየተሰደደ ነው”

August 18, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2