Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  News2  በፓሪሱ ጉባኤ ለአፍሪካውያን የሚደረገው የልማት ፋይናንስ ድጋፍ እንዲጨምር ኢትዮጵያ ያቀረበችው ጥያቄ ተቀባይነት አገኘ
News2

በፓሪሱ ጉባኤ ለአፍሪካውያን የሚደረገው የልማት ፋይናንስ ድጋፍ እንዲጨምር ኢትዮጵያ ያቀረበችው ጥያቄ ተቀባይነት አገኘ

Ethioreview newsEthioreview news—June 25, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በፓሪሱ አዲስ የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስምምነት ጉባዔ ላይ ለአፍሪካውያን የሚደረገው የልማት ፋይናንስ ድጋፍ እንዲጨምር በአፅንኦት መጠየቃቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከልዑካን ቡድናቸው ጋር ለሁለት ቀናት በፈረንሳይ ፓሪስ በተካሄደው አዲስ የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስምምነት ጉባዔ ላይ ተሳትፈዋል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም፤ ኢትዮጵያ በጉባኤው ስለነበራት ተሳትፎና ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙኃን ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጉባኤው ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አማካይነት በዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ አቋሟን ያንጸባረቀችበት እንዲሁም የአፍሪካውያንና የታዳጊ ሀገራትን ድምፅ ያሰማችበት ነው ብለዋል፡፡

More stories

ጓደኛቸውን ገድለው  ሲያሽከረክረው የነበረውን መኪና ወስደው የተሰወሩ ሁለት ተጠርጣሪዎች ተያዙ

May 21, 2024

የብሪክስ ፕላስ የመረጃና እና የባህል ሚዲያ ማዕከል ተመሰረተ

October 15, 2024

” የሎንግ ኦነግ ሸኔን መክዳት ከዜና በላይ ነው” – የሸኔ የሎጂስቲክ መረጃ መንግስት እጅ ገባ

February 18, 2024

“የቴህራን የአየር ክልል በኛ ቁጥጥር ስር ሆኗል” እስራኤል

June 16, 2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር አፍሪካ ተደራራቢና ውስብስብ የሆኑ የፋይናንስ አቅርቦት እጥረት፣ የዕዳ ጫና እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥ ላመጣቸው ቀውሶች ተጋላጭ መሆኗን ማንሳታቸውንም ተናግረዋል።

የአፍሪካ ሀገራት ፍትሐዊ እና ዘላቂ ዕድገት እንዲኖራቸው የፋይናንስ አቅርቦቱ መሻሻል እና መጠናከር እንዳለበት የኢትዮጵያን ግልፅ ጥያቄ ማቅረባቸውንም ነው ያብራሩት።

በተለይም ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማትን የበለጠ ተራማጅ ማድረግ እንደሚገባ መጠቆማቸውንና ከዚህ ቀደም ቃል የተገቡ ስምምነቶችን መተግበር እንዳለባቸው መናገራቸውንም እንዲሁ።

በተለይ ለአፍሪካ አገራት ሊሰጡ የታሰቡ የልማት ፋይናንስ ድጋፎች በተጨባጭ ፈሰስ እንዲደረጉና አቅርቦቱም እንዲጨምር በአፅንኦት ጠይቀዋል ነው ያሉት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊዋ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ከፍተኛ ጥረት እያደረገች መሆኗን ለጉባኤው ማቅረባቸውን ያነሱት ቢልለኔ፤ ወደ አረንጓዴ ልማት ሽግግር ለሚያደርጉ አገራት የበለጠ የገንዘብ ድጋፍ መደረግ እንዳለበት መጠቆማቸውን ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በገለጻቸው ኢትዮጵያ በስንዴ ልማትና በአረንጓዴ አሻራ አመርቂ ውጤቶችን ማምጣቷንም ለጉባኤው አብራርተዋል ነው ያሉት።

ኢትዮጵያ በግብርናውና በሌሎችም መስኮች የጀመረቻቸው የልማት ስራዎች ስኬታማ እንዲሆኑ በራስ አቅም ከሚደረገው ጥረት ባሻገር ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት የፋይናንስ ድጋፋቸውን በማጠናከር የታሰበው ዕድገት በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲሳካ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ማቅረባቸውን አንስተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከጉባዔው ጎን ለጎን ከተለያዩ ሀገራት መሪዎች፣ ከአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የፋይናንስ ተቋማት ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽና በባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ስለመወያየታቸውም ቢልለኔ ገልጸዋል።

በዚህም ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ኃላፊ፣ ከአዲሱ የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት፣ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት፣ ከፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን፣ ከአፍሪካውያን መሪዎች ጋር በተደረጉ ውይይቶች ኢትዮጵያን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስምምነቶች ላይ መደረሱን ጠቁመዋል።

ይህም የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ በውጤታማነት እያደገ ለመምጣቱ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡

በፓሪሱ አዲስ የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስምምነት ጉባዔ ለታዳጊ ሀገራት የሚሰጠው የልማት ፋይናንስ እንዲጨምር ስምምነት ላይ ተደርሷል- የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ

ፓሪሱ አዲስ የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስምምነት ጉባዔ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለታዳጊ ሀገራት የሚሰጠው የልማት ፋይናንስ እንዲጨምር ስምምነት ላይ መደረሱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከጉባዔው ጎን ለጎን ከሀገራት መሪዎችና ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ኃላፊዎች ጋር ባደረጓቸው ውይይቶች የዕዳ ሽግሽግ እንዲደረግላትና አዲስ የማክሮ ኢኮኖሚ የልማት ፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ ስምምነት ላይ መደረሱንም ገልፀዋል።

አዲስ የዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስምምነት የመሪዎች ጉባዔ ባለፉት ሁለት ቀናት በፈረንሳይ ዋና ከተማ ፓሪስ ተካሂዷል።

ጉባዔውን በሚመለከት ማብራሪያ የሰጡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ፤ አፍሪካውያንን ጨምሮ ለታዳጊ ሀገራት የሚደረገው የልማት ፋይናንስ አቅርቦት በከፍተኛ ደረጃ እንዲጨምር በጉባዔው ስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል።

ለዚህም የዓለም ባንክና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ.ኤም.ኤፍ)ን ጨምሮ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ድርጅቶች ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት ድህነትን ለመቀነስ የሚደረጉ የልማት ፕሮግራሞች ከፍተኛ የፋይናንስ ፈሰስ እንዲያደርጉና ይህንን ያማከለ ሪፎርም እንዲያካሂዱ አቅጣጫ መቀመጡን ተናግረዋል።

በጉባኤው የአየር ንብረት ለውጥን በሚመለከት ከዚህ ቀደም የተደረሱ ስምምነቶች ወደ ተጨባጭ የተግባር ምዕራፍ እንዲገቡም ውሳኔ መተላለፉን ገልፀዋል።

በሌላ በኩል ብዙ ታዳጊ ሀገራት በኮቪድ ወረርሽኝ፣ በዩክሬንና ሩስያ ጦርነት እና በዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ መዋዠቅ ምክንያት ጫና ላይ በመውደቃቸው፤ የዕዳ ቅነሳ እና ሽግሽግ እንዲደረግላቸው መግባባት መፈጠሩን ሚኒስትሩ አብራርተዋል።

ኢትዮጵያም በዚህ የዕዳ ጫና ቅነሳና ሽግሽግ ውሳኔ በከፍተኛ ደረጃ ተጠቃሚ እንደምትሆን ነው የተናገሩት።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በመድረኩ ስለ ሀገራዊ ሪፎርሙ ስኬትና የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብርን አቅርበው አድናቆት ተችሯቸዋል ነው ያሉት።

በቀጣይ መርሃ-ግብሩ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ድጋፍ ከተደረገለት ኢትዮጵያ በቀጣናውና በአፍሪካ ለማስፋት የጀመረችውን ጥረት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን አንስተዋል ብለዋል።

በግብርናው መስክ ከውጭ የሚገባ ስንዴን ከማስቀረት ባሻገር ለጎረቤት ሀገራትና ለዓለም አቀፍ ድርጅቶች ኤክስፖርት ማድረግ መጀመሩም በመድረኩ አድናቆት ተችሮታል ነው ያሉት።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጉባዔው በተጓዳኝ ከተለያዩ ከሀገራትና ዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ጋር በመወያየት በልማት ፋይናንስ ድጋፍና ሌሎችም የሁለትዮሽና ባለብዙ ወገን ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ተናግረዋል።

ከፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር በተደረገው ውይይት፤ ፈረንሳይ ለኢትዮጵያ የዕዳ ሽግሽግ እንዲደረግ፣ የሚሰጣት የፋይናንስ ድጋፍ እንዲጨምር በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች እገዛ እንደምታደርግ አረጋግጠዋል ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከአዲሱ የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋስና ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ.ኤም.ኤፍ) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጄቫ ጋር ስኬታማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል።

አዲሱ የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት በቅርቡ ኢትዮጵያን እንደሚጎበኙ መግለጻቸውንና የኢትዮጵያ ሁለተኛው ምዕራፍ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያና ሰፋፊ የልማት ፕሮግራሞች እንዲሳኩ የዓለም ባንክ የፋይናንስ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል መግባባት ላይ መደረሱን ነው ያብራሩት።

በተያያዘም አይ ኤም ኤፍ ኢትዮጵያ ሰፊ ሕዝብ ያላትና ውጤታማ ልማት እያከናወነች መሆኗን እንደሚገነዘብ እንዲሁም የዕዳ ሽግሽግ እንዲደረግላትና የማክሮ ኢኮኖሚ ድጋፍ እንዲሰጣት ፍላጎት እንዳለው ክሪስታሊና ጆርጄቫ አረጋግጠዋል ብለዋል።

በዚህ ደረጃ ከተቋሙ ጋር የሚደረጉ የማክሮ ፕሮግራም ውይይቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና የፕሮግራም መጠኑና ይዘቱ በስምምነት እንዲጠናቀቅ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ማንሳታቸውን ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ በዓለም የአየር ንብረት፣ በግብርና ምርት፣ በቀጣናዊ የሰላምና ጸጥታ ጉዳዮች ያላት የመሪነት ሚና በጉባዔው ከፍተኛ ሥፍራ እንደተሰጠው የገንዘብ ሚኒስትሩ ገልፀዋል።

ኢትዮጵያ ሰላሟንና ውስጣዊ አንድነቷን በማጠናከር ፊቷን ወደ ልማት በማዞር ሁለተኛ ምዕራፍ የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ማዘጋጀቷ አድናቆት እንደተቸረው ጠቅሰው፤ በአጠቃላይ በጉባዔው በባለብዙ ወገን፣ በሁለትዮሽ ኢትዮጵያን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስምምነቶች ላይ መደረሱን ተናግረዋል። የዓለም ባንክ ሊቀመንበር በቅሩ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ አመልክተዋል።

ዜናው የኢዜአ ነው

home
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ከህገወጥ የወርቅ የቅብብሎሽ ድራማ ውስጥ ነበሩ የተባሉ 32 የመንግስት ሃላፊዎችና የጸጥታ መዋቅር አመራሮች ታሰሩ
Arsenal ‘verbally agree’ personal terms with £150m pair amid threat of ‘late hijack’ …
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News2

ብሔራዊ ጥቅምን አሳልፎ ለመስጠት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ባለድርሻ ሊሆኑ አይገባም – በለጠ ሞላ

March 8, 2026
News2

ለክቡር የኢፌዴሪ ማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ሀብታሙ ተገኝና ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው የቀረበ ጥሪ

March 8, 2026
News2

ስምረት ፓርቲ የትግራይ ወጣት ለትህነግ ጀርባ መስጠቱን አስታወቀ

March 6, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2