Skip to content
  Saturday 16 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    የሠሜኑን ጦርነት ተከትሎ ወንጀሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ሥራ ዓለም አቀፍ መርሆዎችን ተከትሎ እየተከናወነነው

    June 1, 2022

    በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረው የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀመረ

    February 1, 2021

    በተዓምር የተረፈች ህይወት ህያው ምስክርነት – ‘አትሙቺ ያላት ነፍስ

    December 14, 2021

    የአጥንት ህመም መነሻ መንስኤዎችና መፍትሄው

    August 20, 2024

    ሞዐ ተዋሕዶ ምንድን ነው? [ሞነግ] “ነጻ አውጪ ግምባር” ወይስ ?

    August 13, 2025
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE
VOE
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE
  SOCIETY  የጦርነት ጠባሳ – ትግራይ በመድሃኒት እጥረት ሳቢያ ህይወት እያለፈ ነው፤
SOCIETY

የጦርነት ጠባሳ – ትግራይ በመድሃኒት እጥረት ሳቢያ ህይወት እያለፈ ነው፤

Ethioreview newsEthioreview news—August 24, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

ከትግራይ የሚወጡ ዜናዎች የሜብሹ ናቸው። የጦርነቱ ጠባሳ እያደር የሚያሰማው ዜና እረፍት የሚነሳ ቢሆንም ጦርነቱን ሲያጋግሉና “ግፋ በለው” ሲሉ የነበሩ ወገኖች ለመልሶ ማቋቋም ሲተጉ አልታየም። በርካቶች እንደሚሉት የፌደራል መንግስት በጀትና ቋሚ እገዝ እንዳለ ሆኖ በጦርነቱ ወቅት ሲደጋገፉ የነበሩ ዲያስፖራ የትግራይ ተወላጆች ወገኖቻቸውን መደገፍ ይገባቸዋል።

ሪፖርተር በመድሃኒት እጥረት ዜጎች በትግራይ መሞታቸውን ከዚህ በታች አስነብቧል። ሊንኩን ተጭነው ወይም ከስር የሪፖርተርን ዜና እንዳለ ያንብቡ

ባለፉት ሦስት ወራት በካንሰር መድኃኒት እጥረት ምክንያት ብቻ ከ100 የሚበልጡ ታካሚዎች ሕይወታቸው ማለፉን፣ የትግራይ ክልል የአይደር ሆስፒታል አስታወቀ፡፡

በሆስፒታሉ በተለይም የካንሰር ሕሙማን የቀዶ ሕክምና የሚጠባበቁ የታካሚዎች ቁጥር ከፍ ማለቱን፣ ከፍተኛ የሆነ የመድኃኒት እጥረት በመኖሩ በየጊዜው የሟቾች ቁጥር ከፍ እያለ መሆኑን፣ የአይደር ሆስፒታል የካንሰር ሕክምና ማዕከል ኃላፊ ዶ/ር ክብሮም ህሉፍ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡

More stories

ወገኛ ምርኮዎች !!

August 27, 2021

በዓለም ባንክና በኢትዮጵያ መንግሥት የሚተገበር የ550 ሚሊዮን ዶላር ፕሮጀክት ዛሬ በይፋ ይጀመራል

January 29, 2022

በድንገተኛ የሞተር ብልሽት የፖላንድ አውሮፕላን አዲስ አበባ አረፈ

September 18, 2021

ኤርትራዊያን ስደተኞች “አሸባሪው ወራሪሃይል ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ፈጽሞብናል” ሲሉ የዓለም ሕብረተሰብ ተማጸኑ

February 23, 2022

ምንም እንኳን ሆስፒታሉ በጦርነቱ ወቅት ከነበረው ሁኔታ አንፃር የመድኃኒት አቅርቦቱ እየተሻሻለ ቢሆንም፣ ከታካሚዎች ቁጥር አንፃር እዚህ ግባ የሚባል እንዳልሆነ አስረድተዋል፡፡

እጥረቱ ከተከሰተባቸው የሕመም ዓይነቶች የጡት ካንሰር መድኃኒት አቅርቦት እንደሌለ፣ በዚህ ሁኔታ እጥረቱ ከቀጠለ የሕመሙ ደረጃና የሟቾች ቁጥር ከተጠቀሰው በላይ ሊልቅ እንደሚችል ገልጸዋል፡፡  

በማዕከሉ ባለፈው አንድ ወር ውስጥ ከ500 በላይ ተመላላሽ ታካሚዎች እንደነበሩ ጠቁመው፣ በአጠቃላይ ከ1,200 እስከ 1,500 ታካሚዎች ወረፋ የሚጠባበቁ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡

በካንሰር መድኃኒት እጥረት ምክንያት ባለፉት አራትና አምስት ወራት ውስጥ በትንሹ 100 ሰዎች መሞታቸውን ነው ዶ/ር ክብሮም የገለጹት፡፡

የአይደር ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር አብርሃ ገብረ እግዚአብሔር በበኩላቸው፣ በሆስፒታሉ ከጦርነቱ በኋላ የመድኃኒት አቅርቦት መሻሻል አሳይቷል ብለዋል፡፡ ከእነዚህም መድኃኒቶች ውስጥ የፀረ ኤችአይቪ/ኤድስ፣ የቲቢና የኢንሱሊን አቅርቦት እየተሻሻለ መሆኑን አስረድተዋል፡፡  

‹‹ይሁን እንጂ በአጠቃላይ የመድኃኒት አቅርቦቱ ያለውን እንሰጣለን ከማለት ውጪ፣ ምን ያህል እንደሚቀርብ እንኳን አናውቅም፤›› ሲሉ ሜዲካል ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

ከጦርነቱ በፊት የመድኃኒቶች ዝርዝር ወጥቶ ለሁለትና ለሦስት ወራት የሚያስፈልገው የሚታወቅ መሆኑን፣ ይሁንና ከጦርነቱ በኋላ ምን ያህል እንደሚቀርብ እንደማይታወቅ አክለዋል፡፡

ለሰኔና ለሐምሌ  2015 ዓ.ም. የሚያስፈልጉ መድኃኒቶችና በሕክምና ግብዓቶች አስፈላጊዎቹ የትኞቹ ናቸው ብለው ቢጠይቁም መረጃ ማግኘት አለመቻላቸውን አስረድተዋል፡፡

ከዚያ ውጪ የሚቀርቡት መድኃኒቶች በሪፈራል ሆስፒታል ደረጃ በቂ አለመሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በተኝቶ መታከም አገልግሎት ፅኑ ሕክምና ክፍል (የአዋቂ፣ የሕፃናት) ውስጥ በአጠቃላይ 24 አልጋዎች እንዳሉ ያስረዱት ዶ/ር አብርሃ፣ 45 ጨቅላ ሕፃናት የሚታከሙባቸው 45 ክፍሎች በርካታ መድኃኒቶች የሚያስፈልጋቸው ናቸው ብለዋል፡፡

ድንገተኛ ክፍል በዓላትን ጨምሮ ለ24 ሰዓታት የሚሠራ በመሆኑ፣ ለእነዚህ ሁሉ ክፍሎች የሚያስፈልጉ መድኃኒቶች በበቂ ሁኔታ አሉ ተብሎ የሚኮራባቸው አይደሉም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በተያያዘም የጓንት እጥረት መኖሩን ገልጸው፣ ይህም ለባለሙያዎችም አስቸጋሪ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በደም ሥር የሚሰጡ መድኃኒቶች፣ የጨቅላ ሕፃናት፣ የእናቶችና ሌሎችም የመድኃኒት ዓይነቶች በከፍተኛ ሁኔታ እጥረት መኖሩን ተናግረዋል፡፡ በእንክብል የሚወሰዱ የስኳር፣ በአጠቃላይ የልብና የሚጥል በሽታ መድኃኒቶች ከፍተኛ እጥረት እንዳለም አስታውቀዋል፡፡

በተለይ ለቀዶ ሕክምና የሚያገለገሉ የሰመመን መድኃኒቶች እጥረት መኖሩን ገልጸው የጓንትና የሕመም ማስታገሻዎች የአቅርቦት ችግሮች የሚጠቀሱ ናቸው ብለዋል፡፡

ወላድ እናቶች መውሰድ ያለባቸው መድኃኒቶች ከዚህ ቀደም ሲቀርቡ እንደነበር፣ ከጊዜ በኋላ አቅርቦቱ እየሳሳ ሲመጣ ደም ለሚፈሳቸው ብቻ እየተሰጠ ለማብቃቃት እየተሞከረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ቫይታሚን ‹ኬ› ሁሉም ሕፃናት ከተወለዱ በኋላ መሰጠት ያለበት ቢሆንም፣ ባለው ከፍተኛ እጥረት ሳቢያ ማድረስ አለመቻሉም ተመላክቷል፡፡ የጭንቅላት ውስጥ ኢንፌክሽን ሲፈጠር፣ በአከርካሪ አጥንቶች የሚያጋጥሙ ኢንፌክሽኖች በእንክብልና በሽሮፕ የሚታከሙበት አማራጭ አለመኖሩን ገልጸው፣ ለእነዚህ ሕመሞች የሚሆኑ መድኃኒቶች ሲጠፉ ታካሚዎች እንደሚሞቱ ገልጸዋል፡፡

ለኩላሊት ዲያሌሲስ አገልግሎት ግብዓቶች ባለመኖራቸው ሕሙማን ለሕልፈተ ሕይወት መዳረጋቸውንም አክለዋል፡፡ በምሳሌነት ያነሱትም ከጦርነቱ በፊት ከነበረው ጋር ሲነፃፀር ከጦርነቱ በኋላ ያሉ ሦስት አራተኛ ታካሚዎች መሞታቸው ተገልጿል፡፡ ተኝቶ መታከምንና የፅኑ ታካሚዎች የሞት ምጣኔ በወሩ የሚሠላ መሆኑን፣ ከጦርነቱ በፊት ተኝቶ መታከም ስድስት በመቶ ያነሰ እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡

ከጦርነቱ በኋላ ግን ተኝቶ መታከሚያ ክፍል የሚሞቱ የታካሚዎች ቁጥር አሥር በመቶ በላይ ከፍ ማለቱን አስረድተዋል፡፡ የፅኑ ታካሚዎች ከጦርነቱ በፊት የነበረው የሞት ምጣኔ 22 በመቶ እንደነበር፣ ከጦርነቱ በኋላ ደግሞ 40 በመቶ እንዳለፈ ዶ/ር አብርሃ ገልጸዋል፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ የጨቅላ ሕፃናት ሕክምና በአብዛኛው ከጦርነቱ በፊት 11 በመቶ የሞት ምጣኔ እንደነበረ፣ ከጦርነቱ ወዲህ ደግሞ ወደ ከ20 በመቶ በላይ ከፍ ማለቱንም አስታውቀዋል፡፡  

SOCIETY
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ያዕቆብ ወልደ ማርያም – 57 ዓመታት ያገለገሉት አንጋፍው ጋዜጠኛ ስንብት ተፈጸመ
ብጉር | Acne vulgaris
Related posts
  • Related posts
  • More from author
SOCIETY

አስጨናቂዋን ሰዓት ወደ ደስታ የቀየረው የኢትዮጵያዊያን የሕክምና ባለሙያዎች ስኬት

August 23, 2025
News

በ2018 ጓደኞቼ ዩኒቨርስቲ ይገባሉ፤ በድህነት ከተማ ሄዶ መማር ይልቻለው ታዳጊ ለቅሶ!

August 22, 2025
SOCIETY

“በጠለምት ወረዳ በዝናብ እጥረት ሳቢያ እንስሳት እየሞቱ ነው፤ ሕዝብ እየተሰደደ ነው”

August 18, 2025
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2