Skip to content
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • DESIGN
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    ታላቁ ህዳሴ ግድብ በመገባደጃ ምዕራፍ ላይ

    April 1, 2023

    የአሊባባ ግሩፕ በኢትዮጵያ የኢኮሜርስ ገበያ ለመጀመር የሚያስችል ስራ መጀመሩን ይፋ አደረገ

    August 22, 2024

    ዶናልድ ትራምፕ በቁጥጥር ሥር ውለው በቀረበባቸው ሰላሳ አራት ክሶች ጥፋተኛ አይደለሁም አሉ

    April 6, 2023

    የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰነድ የሌላቸው የኤርትራዊ ስደተኞች መታሰራቸውን ኮነን፤ “ያለ ህጋዊ ማስረጃ የትኛው አገር መኖር ይቻላል?”

    June 4, 2023

    ቻይናዊው የፀሃይ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ከ9 ግብረ አበሮቻቸው ጋር የውጭ አገር ብሮች በማተምና በጥቁር ገበያ ወንጀል ታስረው ፍ/ቤት ቀረቡ

    September 5, 2023
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • News
    • NEWS 2
  • AFRICA
    • WORLD
  • VIDEO
  • HOT
  • POLITICS
    • INTERVIEW
    • OPINION
    • SOCIETY
    • ENTERTAINMENT
    • ያበደው
    • SPORT
    • ማህደር
      • Travel
      • Social media
      • Stars
      • Technology
      • Tourism
      • Trends
    • Music
      • Movies
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  News  እንደ ሱዳን የመሆን ምኞትና ጥድፊያ – የነጻ አውጪ ጋጋታ
NewsOPINION

እንደ ሱዳን የመሆን ምኞትና ጥድፊያ – የነጻ አውጪ ጋጋታ

Ethioreview newsEthioreview news—September 18, 2023
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

በሱዳን ኮሽ ባለ ቁጥር ” መንግስት ይናድ” እያሉ አደባባይ ወጥተው ጎማ የሚያነዱ ዛሬ ከስመዋል። ኮሽ ባለ ቁጥር ተተኪ ሳይዘጋጅላቸው መንግስታቸውን የናጡና የነቀነቁ ዛሬ የጸጸት ጊዜ ማግነት አልቻሉም። ተሰደዋል። ወይም የመንደር ለመንደር ሌቦች ሆነዋል። ወይም አካላቸው ከጎደሉት ውስጥ ናቸው። ወይም ሞተዋል። ኮሽ ባለ ቁጥር በስሜት የሚነዱ ሁሉ ውጤቱን ከሱዳን እያዩ ነው። ሱዳን ውስጥ “አገር የሞተ አንደሁ ወዴት ይደረሳል?” የሚለው ዘፈን ተረስቷል።

ያለ ምንም ማጋነን ከሰባት ሚሊዮን የሚልቁ የሱዳን ዜጎች በአየርና በየብስ መኖሪያ መንደራቸውን፣ ቤታቸውን፣ ንብረታቸውን ጥለው እዛም እዚህም ተሰደዋል። ይህ የሆነው ደግሞ በጣምራ አገሪቱን ሲሟሯት የነበሩት ሁለት የጦር ጀነራሎች በስልጣን ጥማት በጀመሩት ጦርነት ሳቢያ የሆነ ነው። ኢመደበኛ ሃይል ገንብቶ ከውጭ ሃይሎች ጋር ተቧድኖ በማዕድን ንግድ ካዝናውን ያደለበው መሃይምና የአገሪቱን ሲቪል መንግስት ከበተነው የጦር መኮንን ጋር ለመበላላት በተጀመረው ጦርነት ያለቁትም ቁጥራቸው ንሯል። ኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየው የነጻ አውጪዎችና ግንባሮች ትንቅንቅም ሩጫው ሱዳንን የመሆን ምኞት መስሏል። በርካታ መመሳሰሎች እየታዩ ነው።

የሱዳን ጦር መሪ ጀነራል አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን እና የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ መሪ ጀነራል ሞሐመድ ሐምዳን ዳጋሎ ሱዳንን ተስማምቶ መጋጥ ተስኗቸው መፋለም ከጀመሩ ዛሬ ሰባት ወር አልፏቸዋል። በሰባት ወሩ የርስ በርስ ፍልሚያ እነዚህ ሁለት አልጠግብ ባዮች ባሰለፏቸው ሃይሎች አስር ሺህ የሚጠጉ ንጹሃን እንዳለቁ እየተገለጸ ነው። ከስድስት እስከ አስራ ሁለት ሺህ የሚሆኑ አካላቸው ጎድሏል። 4.1 ሚሊዮን በአገር ውስጥ ተፈናቅለዋል። 2.1 ሚሊዮን የሚሆኑ አገራቸውን ጥለው ነብስ አውጪኝ ስደት ላይ ናቸው። በውጭ ሃይሎች ግፊትና እርዳታ ነዳጅ የሚርከፈከፍበት የሱዳን ቀውስ አገሪቱን ትናንሽ ቦታ ሊቆራርሳት እንደሆነም እየተሰማ ነው።

ሲያስቡት ጨለማ የሚሆነው የሱዳን ጉዳይ ከሞት፣ ስደትና አካለ ጎዶሎነት በተጨማሪ ችጋር፣ በሽታ ጥማት የከፋ አደጋ አንግሶባታል። ሴቶች፣ አረጋዊያና ህጻናት በያሉበት ጠኔ እየጠበሳቸው እንደሆነ መረጃዎች እየወጡ ነው። ጎን ለጎን ደግሞ ወዴት ወስደው እንደሚሸጡት ባይታወቅም የቤት ለቤት ዘረፋው የሚከናውነው ያለማንም ከልካይ ነው። ዘረፋው እንዴት እንደሚከናወን የሚገልጹ ሚዲያዎች እንደሚሉት ከሆነ ሱዳን ሁሉም ነገር ሊመለስ በማይችልበት ደረጃ ፈር ለቋል። በመጋዘኖች ላይ ዝርፊያ ከተፈጸመ በሁዋላ መጋዘኑንን በእሳት ማጋየትና አመድ ማድረግ ወግ ሆኗል።

More stories

“በተካድኩ” ስሜት መከላከያ አማራ ክልልን ለቆ ሊወጣ ነው?

April 10, 2023

” ከሩስያ ጋር በዩክሬን ምድር አንዋጋም፣ የኔቶ አባል አገራትን ግን ኢንች እንዳይነኩ እንከላከላለን ” አሜሪካ

February 25, 2022

ኮንስበርግ አምስት ገድሎ ሁለት ያቆሰለው ዴንማርካዊ ሃይማኖት ከአክራሪነት ጋር እየተያያዘ ነው

October 14, 2021

ጦርነቱ ገና አልተጀመረም!የትግላችንን መዳረሻ እንዳንዘነጋ!

August 26, 2021

As of 15 August 2023, between 4,000 and 10,000 people had been killed and 6,000 to 12,000 others injured,[8][9][12][11] while as of 12 September 2023, over 4.1 million were internally displaced and more than 1.1 million others had fled the country as refugees.

ዝርፊያ ከተከናወናባቸው መጋዘኖች መካከል የሽቶ ማከማቻ መጋዘን ይገኛል። ይህ መጋዘን ሲዘረፍ አንድ ጨለማ አላሳይ ያለው ላይተር ለኩሶ በተፈጠረ እሳት ከመቶ ሃይ የሚልቁ ሰዎች ነደዋል። አመድ ሆነው መለየት እንዳልተቻለ የቢቢሲ ዘጋቢ ጽፋለች። በሱዳን

ጦርነቱን ተከትሎ በሱዳን መንግሥት ፈርሷል። የፖሊስ ኃይል የለም። እስር ቤቶች እየተሰበሩ ወንጀለኞች በነጻ ተለቀዋል። በጥቅሉ ህግ በአፍጢሙ ተደፍቷል። ስለ ህግ፣ ፍትህና ርትዕ ማሰብ ብሎ ነገር የለም። ከዚሁ ጋር ተያያዞ የክላሽንኮቭ ጠብ መንጃ ዋጋ በግማሽ መቀነሱ ተሰምቷል። ቢቢሲ እንዳለው ከሆነ በሱዳን ከሚማረኩና ከሚያዙ የሰራዊት አባላት የሚማረከው መሳሪያ የሚሸጠው በጦር መሪዎች ነው። ይህም በመሆኑ አቅርቦቱ ከፍተኛ ሆኖ ዋጋው ቀንሷል። 830 ዶላር ግድም የሚከፍል የካላሽ ባለቤት ይሆናል።

ሱዳን ከሶማሊያ ቀጥላ እየፈረሰች ያለች አገር ስትሆን፣ አሁን ላይ በጎሳ የመከፋፈል አብዮት እየተፋፋመባት እንደሆነ እየተገለጸ ነው። የሱዳን ፈጥኖ ደረሻ ሃይል መሪ ሕምዳን ዳጋሎ መንግስት እንደሚመሰርቱ ካስታወቁ በሁዋላ፣ ቤተመንግስታቸውን የተነጠቁት ጀነራል አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን ጨምሮ ሱዳን ለጊዜው ሶስት ቦታ መበለቷ ፣ የንግግርና ድርድር ጉዳይ ተረት እንደሆነ እየተገለጸ ነው።

ሱዳን ከተሞቿን እየበላች ነው። ሱዳን ነዋሪዎቿ እየተበሉ ነው። ቤተሰብን፣ ዘመድን፣ ወዳጅን፣ ጎረቤትን በወጉ መቅበርና ሃዘን መቀመጥ ቅንጦት ሆኗል። የሱዳን አንጋቾች ለማንና ለምን ምክንያት እንደሚዋጉ የሱዳንን ህዝብ ወቅታዊ አቋቋም ያዩ የሚረዱት እውነት ነው። የሱዳን ህዝብ መከራው ልክ አልፎእ ግልብጥ ብሎ ወደሚችልበት ስፍራ እየጎረፈ ነው። መሰደድ ያልቻሉት አቅም ያጡ ብቻ ናቸው። ሱዳን በየትኛውም የተስፋ ሚዛን የማይለካ ውድቀት ውስጥ ተነክራለች። እዛም እዚህም የተደራጁና መሳሪያ በገፍ ያታጠቁ የሚፈነጩባት የድም መሬት ሆናለች።

ሱዳን ማሰብ የተሳናቸው ልጆቿ ልክ እንደ እሳተ ጎሞራ፣ ጎርፍና የመሬት መንቀጥቀጥ አይነት አደጋ ሆነውባታል። በስደት ኖርዌይ የምትኖር ሱዳናዊ ” ሱዳን ፈርሳለች። ተስፋ ቆርጫለሁ። ተዓምር ካልተፈጠረ በቀር የሱዳን ነገር አክትሟል” ስትል አገር አልባ የመሆን ስብራቷን ገልጻለች።

በኢትዮጵያ ለውጡን ተከትሎ የፈነዳው አዲሱ እሳቤ ስልጣን፣ ወንበር፣ ክልልነት፣ ዞንነት፣ የከተማነት ጥያቄ፣ ህገወጥነት፣ ወረራ፣ ዝርፊያ፣ ወዘተ የሚጠቀሱ ሲሆኑ ” እኔ የለውጡ ጌታ ነኝ” በሚል የሚታየው ኩርፊያ ከሁሉም ይልቃል።

ያኮረፉ የሚዲያ ሰዎች፣ የኮረፉ ፖለቲከኞች፣ ያኮረፉ ደጋፊዎች ወዘተ ብሄር እየፈለጉ ነገር ማጦዝና ህዝብን ቁጣ ውስጥ የሚከት መረጃ ማሰራጨት የትግል ስልታቸው ከሆነ ሰነባብቷል። እንደውም አንዱ ከከሸፈው ልምድ የሚቀስምምበት የቢዝነስ አውድ ሆኗል። ደምና የህዝብ ስቃይ ንግድ የሆነላቸው የድርጅት መሪ መስለው በግፋ በለው የጎ ፈንድ ሚ ተዋንያኖች ሆነዋል።

ዜጎች ተደራጅተው፣ በሰከነ መንገድ ጥያቄያቸውን ከማቅረብ ይልቅ በብስጭት እንዲነሱ “ሰበር” እያለ የሚጮኸው የንግድ ሚዲያ፣ አንድ ኪስና ቋት አልበቃ ብሎቸው ሁለትና ከዛም በላይ ሚዲያ ከፍተው የኢትጵያን ፖለቲካ እያቦኩት ነው።

ትህነግ ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ በዘር ባቡር ሲከንፍ ኖሮ ዛሬ እንደሚታየው ስምና ታሪክ አልባ ሆነ። ህዝቡን ለድህነት፣ ረሃብ፣ ውርደትና ኪሳራ ዳርጎ በውርደት ሸማ ተጆብኖ የሞት ጣር ላይ ነው።

ኦነግ በተመሳሳይ ሃምሳ ዓመት በተመሳሳይ መንገድ እየዳከረ ነው። የኦሮሞ ጥያቄዎች በሙሉ ተመልሰው ፋይላቸው ተዘግቶ ሳለ አሁን ደረስ የተመለሱ ጥያቄዎች ለማስፈጸም በሚል ብረት አንስቶ ይገላል። እንደ ወለጋ አይነት የጥጋብ መሬት፣ ሃብታም ገበሬ ለማኝ አድርጎ ይፎክራል። ደግሞ ደጋግሞ ስርቻ ከወረወረው ትህነግ የሚኮርጀው ኦነግ መሳሪያውን ወርውሮ በምርጫ የፖለቲካ ስልጣን ለመያዝ ከመታገል ይልቅ ባረጀ እሳቤ ላይ ተቸክሎ የተዋለደ ህዝብ ሊበትን በየጥሻው እየተሹለከለከ ንጽሃንን ይገድላል።

አማራ ክልል የተለያዩ አካላት ከውስጥና ከውጭ መሪ እንደሆኑ የሚናገሩለት ትግል በርካቶችን ግራ አጋብቷል። አማራ ላይ የተፈጸመውን መፈናቀልና ግድያ ለማቆም አልሞ ተጀመረ የተባለው ትግል ስክነት የጎደለው፣ ወጥ ያልሆነ፣ ሌሎችንም የትግሉ አጋዥ የማይደርግ እንደሆነ ቢገልጽም አድናቆት የሚቸሩት አሉ።

እየዋለ ሲያድር አዳዲስ መረጃ የሚቀርብበት የአማራ ክልል እንቅስቃሴ አሁን ላይ “ፋኖ ለህልውና ለፍትህና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ (ፋ.ህ.ፍ.ዴ.ን) የሚል አዲስ ስም እንደያዘም እየተገለጸ ነው። የአማራ ህዝባዊ ሃይል ግንባር በሚል ከሚታወቀውና በአገር ውስጥ እስክንድር ነጋ፣ በውጭ ሻለቃ ዳዊት የሚመሩት ይህ ንቅናቄ እያለ የተቋቋመው አዲስ ንቅናቄ በይፋ ማን እንደሚመራው አልተመለከተም። እንደሚባለው ከሆነ እነ አቶ አንዳርጋቸው በዚህ ምድብ ከነመሳይና መኮንን ጋር ተሰልፈዋል።

ስለ ድርጅቶቹ አሳብ መስጠት የጽሁፌ አላማ ባይሆንም የአማራ ክልልን እንቅስቃሴ አስመልክቶ የአመራር ሚና እንደሚጫወት የሚገልጸው የጀርመኑ አቶ ዘመድኩን (ዘመዴ) በጅምላ ሙስሊም ጠል፣ ኦሮሞ ጠል፣ መረጃዎችን በስፋት እያሰራጨ መሆኑን በርካቶች አልወደዱትም። በግል አደገኛ አካሄድ መስሎ ይታየኛል። የአማራ ህዝብ ክርስቲያን፣ ሙስሊም፣ ዋህቢያ፣ ወንጌላዊ ወዘተ ብሎ የሚከፋፈል ባለመሆኑ ይህ አካሄድ ሌላ ቀውስ የመጥመቅ አጀንዳ ሆኖ ይሰማኛል።

በተለይም አሁን የተጀመረውን ውጊያ የአማራና ኦሮሞ አድርጎ የሚያቀርቡ ዘመዴን ጨምረው አደብ ቢገዙ፣ ተከታዮቻቸውም ይህን ቢያስገነዝቧቸው፣ መሪ ነን የሚሉ በይፋ ወጥተው ቢያወግዙ ወይም በዚህ ደረጃ ህዝብን ከህዝብ በሃይማኖት ለማጫረስ የሚሰሩ አካላት የትግሉ ተባባሪ እንዳልሆኑ ማስታወቅ አስፈልጊ ይምስለኛል።

“የግራኝ መሐመድ ወረራ” በሚል ኦሮሞን እንደ ማህበረሰብ ወራሪ አድርጎ መሳል ኢትዮጵያን የማፍረስ አጀንዳ ያላቸው ሽብር ጠማቂዎችና ስፖንሰር አድራጊዎች ሴራ ነውና “ቢቀርብን” ለማለት እወዳለሁ።

አማራና ኦሮሞን የማጋደል. የማጫረስና ወደ ለየለት ጦነት የማስገባት አጀንዳ የማን አጀንዳ እንደነበር የሚታወቅ ሆኖ ሳለ የአማራ ጥያቄ ላይ አስታኮ ይህንኑ አጀንዳ መስበክ በሰላም እየኖረ ላለው “ወገን” የሚባል ህዝብም አይጠቅምምና በአስቸኳይ እርምት ይወሰድበት። በዘር ፖለቲካ እየላመች ያለቸው ኢትዮጵያ የሃይማኖት ግጭት ከተነሳባት እዛና እዚህ ሳይባል በሁሉም መንደር እሳቱ እንደሚነድ ለአፍታም ጥርጥር የለውም። ይህ የአንድም ፍትህ ጠያቂ አማራ አጅንዳ አይደለም።

አማራ “ተነፈግሁ” ፍትህ ጠየቀ እንጂ “ኦሮሞ፣ ሙስሊምና ዋቄፈታ ልዩ ጠላቶቼ ናቸው ” ብሎ በጅምላ ሲከስ አልተሰማም። አማራ በሁሉም የአገሪቱ ክፍል አሁንም ከሁለኡም ጋር እምነትና ዘር ሳይለየው እየኖረ ነው። የተወሰኑ ሴረኞች የዘል ዕልቂት እንዲነሳ በሚፈጽሙት ወነጀል ሳቢያ አማራን ከሁሉም ወገኖቹ የሚያቅቅሩ አካሄዶች ባስቸኳይ ሊቆሙ እንደሚገባ የማሳስበው ሱዳን ላይ እየሆነ ያለው በኢትዮጵያ ሊሆን የማይችልበት አንድም ምድራዊ ምክንያት ስለሌለ ነው።

መንግስትም ቢሆን ቢያንስ በክልል ደረጃ አማራ ክልል ላይ ሁሉም ወገኖች ተቀምጠው በውይይት ችግራቸውን የሚፈቱበት እግባብ እንዲመቻች ቢያደርግ የተሻለ ይሆናል።

አብዱል ከሪም አህመድ / ነጻ አሳብ


  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም። ይህ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
    ቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች
    ቪኦኢ ዜና -በአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኢልሀን ኦማር የሀብት መግለጫ ላይ ታይቶ የነበረውና ከፍተኛ ውዝግብ አስነስተው የነበረው የ30 ሚሊዮን ዶላር ሃብት “የሂሳብ ባለሙያዎች… Read more: የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች
NEWSOPINION
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail
ኦቪድ ግሩፕ በአገር ውስጥ፣ አሜሪካ፣ ጀርመንና እስራኤል ስሜን አጠፉ ባላቸው ሚዲያና ግለሰቦች ላይ ክስ መሰረትኩ አለ
የመጸዳጃ ቤት ጽሁፎችና … ለመረጃነት አይበቁም
Related posts
  • Related posts
  • More from author
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
News

ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር

April 13, 2026
Load more
Read also
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 2026
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 2026
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 2026
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 2026
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 2026
WORLD

የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና?

April 26, 2026
Load more
Recent Posts
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
  • ስብሰቡን “ሸፍጥ ይመስላል” ያሉት ዶ.ር ሚኒሊክ ከመጪው ቅዳሜ የአመጽ ጥሪ ምድብ ውጪ ሆኑ፤ የፋኖ ጉዳይ አስፈርቷል March 28, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedhotbusinessarchivetips
    © Copyright 2026,voicesofethiopia All Rights Reserved
    • CONTACT
    • law
    • INTERVIEW
    • ያበደው
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2