ስማቸውን ካሰራጩት ደብዳቤ ግርጌ የዘረዘሩ ሰላሳ አምስት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በመጪው አዲስ ዓመት የ”ሰላም ጥሪ ” ሲሉ ባሰራጩት ጽሁፍ መንግስት ሁሉን አቀፍ መድረክ እንዲያመቻች ጠየቁ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ እርቅ ኮሚሽን ሲያሰባስብ የቆየውን ግብአት አደራጅቶ በመጪ አዲስ ዓመት ሁሉ አቀፍ የዕርቅ ማድረክ እንዲያዘጋጅ ማስታወቁን ተከትሎ የቀረበው ጥሪ ነው።
በሽግግር ፍትህ ፖሊሲ እንዲታዩ ዕቅድ ተይዞባቸው ከአራት ወረዳዎች፣ እንዲሁም በውልቃይት ጠገዴ ባለው የባልቤትነት ጥያቄ የተነሳ ከሃሜት ለመዳን ካለመከናወኑ በቀር በመላው አገሪቱ ግብዓት በመስብሰብ የትነተና ስራ ብቻ እንደቀረ ባለፈው ሳምት ኮሚቴው ማስታወቁ ይታወሳል። እርቅን ከፍትህ ጋር አስተሳስሮ አገሪቱን በየጊዜው ለውዝግብና እልቂት የሚዳርገውን ትርክት ለመቋጨት የተቋቋመው ኮሚሽን የተጋብር ስራውን በአዲሱ ዓመት ማግስት እንደሚያስጀምር የሚታወስ ነው።
ተጠያቂነትን ለማስፈን ፍትህ ሚኒስቴር
ኮሚቴው ” ለዘላቂ ሰላምና ለአገረ መንግስት ግንባታ የራሳቸዉ መሰረታዊ አስተዋፅኦ እንዳላቸዉና የሽግግር ፍትህ ዋነኛዉ ትኩረት ተፈፀሙ የሚባሉ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ላይ መሆኑንና በእነዚህ ሂደቶች ክስ የሚኖር መሆኑን በመግለፅ በአገራዊ ምክክር ላይ ግን በአብዛኛዉ ክስ የሌለ መሆኑ ልዩ ያደርጋቸዋል ሲሉ ከተቋማዊ አደረጃጀት አነፃርም የሽግግር ፍትህ በሁለት አይነት እንደሚደራጀና እነዚህም እዉነት ኮሚሽንና ፍርድ ቤት ላይ የሚተገበሩ ሲሆን አገራዊ ምክክር በአገራዊ ምክክር ኮሚቴ መሰል ቡድኖች እንደሚደራጅና በጥቅሉ አገራዊ ምክክር በሽግግር ፍትህ አማራጮች እንደ አንድ አማራጭ መካተቱንም አያይዘዉ አዉስተዋል” ሲል በጋዜጣ መግለጫው ወቅት መናገሩን ፍትህ ሚኒስቴር በገጹ አመልክቷል።
እነዚሁ ድርጅቶች ላቀረቡት ጥሪ የመንግስት ምላሽ ለጊዜው አልታወቀም። በኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም እንዲሰፍን መናፈቅ የእለት ተዕለት ስራው ሆኗል። የዚያኑ መጠን ሚዲያዎችና ማህበራዊ አውዶች ምንጩ ከማይታወቅ መረጃ በተጨማሪ በተቀነባበረና በተናበበ የፈጥራ ዜና የአገሪቱን ሰላም በስፋት እያወኩ እንደሆነ በተደጋጋሚ እየተገለጸ ነው።
ድርጅቶቹ የጥላቻ ንግግርና የተዛቡ መረጃዎችን ማሰራጨት እንዲቆም፣ ህዝብን በጅምላ መፈረጅ አግባብ እንዳልሆነ ጨምርው ካነሱዋቸው አሳቦች በተጨማሪ በዋናነት ያነሷቸውን አሳቦች ከስር የመለከቱ። መግለጫቸውንም ያንብቡ።
- አገር አቀፍ የሰላም መድረክ ይመቻች
- ገለልተኛ ምርመራና ተጠያቂነት ይስፈን
- ፆታዊ ጥቃቶች ተገቢው ትኩረት ይሰጣቸው
- የተጋላጭ እና ግፉአን ጥበቃ ማዕቀፍ ይዘርጋ
- ሕዝባዊ ተሳትፎ ይረጋገጥ
- የቅድመ ግጭት መጠቆሚያ እና መከላከያ ስርዓት (Early warning System) ይኑር
- የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት ሳይስተጓጎል ይቀጥል
- የጥላቻ ንግግር እና የተዛቡ መረጃዎች ስርጭት ይቁም
- የሲቪክ ምኅዳሩ ጥበቃ ይደረግለት
- ባለድርሻ አካላት ለሰላም ግንባታ የበኩላቸውን ይወጡ ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። ጥሪያቸውን ዛሬ በአዲስ አበባ ካፒታል ሆቴል በሰጡት መግለጫም አመልክተዋል።
ድርጅቶቹ በአሳብ ተመሳሳይ ይዘት ይዞ በስፋት ሲሰራ ከቆየው ከአገር አቀፍ የምክክር መድረክ በተለየ አዲስ የምክክር መድረክ እንዲመቻች የጠየቁበትን ምክንያት ይፋ አላደረጉም። ድርጅቶቹ አብዛኞቹ በስም መኖራቸው ጭምር የማይታወቅና ቀደም ሲል ተዘግተው ወይም በህግ ገለልተኛ አይደላችሁም በሚል በር የተዘጋባቸውና ከለውጡ በሁዋላ ህልውናቸውን ዳግም የገኙ ድርጅቶች ናቸው። ዛሬ የተሰጠውን ሙሉ መግለጫ ከላይ ያንብቡ።
- አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱበዙፋን ኡርጋ ደራሲነት የተጻፈውን ሌንጮ ለታ ትግል ሕይወቱ መጽሐፍን አነበብኩት። መጽሐፉ በ471 ገጾች እና በሦስት ክፍሎች ተቀንብቧል። የመጀመሪያው… Read more: አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደርበኢትዮጵያ ፖለቲካና የታሪክ ጥናት ውስጥ እጅግ አነጋጋሪ ሰው ናቸው። በሁለት ጽንፍ ተፈርጀው ይተቻሉ። በአንድ በኩል “ለኦሮሞ ሕዝብ ማንነትና… Read more: ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር
- የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙየአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ዶ/ር አኔት ዌበር Dr. Annette Weber ለኤርትራ መሪዎች ጣልቃ ገብነታቸውን እንዲያቆሙ አሳስበው… Read more: የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ











