Skip to content
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  Sunday 17 May 2026
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
  • News
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    በጦርነቱ ጉዳት ለደረሰባቸው ባለሀብቶች ብድር ከመስጠት አንስቶ ሌሎችም ድጋፎች እንደሚሰጥ ተገለፀ፡፡

    February 9, 20220

    ሹፌሮችን በመግደል ተሽከርካሪ ሲሰርቁ የነበሩ አራት ግለሰቦች የሞት ቅጣት ተወሰነባቸው

    October 21, 20240

    የአማራ ክልል ከትግራይ ጋር ሁሉንም ጉዳይ በውይይትና በሰላማዊ መንገድ ለመጨረስ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ

    March 31, 20230

    Sudan official: ‘Mediation between Khartoum and Addis Ababa faces obstacles’

    February 14, 20210
    Prev Next Showing 1 Of 1866
  • Design
    • All
    • AFRICA
    • ART and CULTURE
    • BUSINESS
    • ECONOMY
    • EDITORIA
    • ENTERTAINMENT
    • ertips
    • Events
    • FEATURED
    • General
    • General
    • HOT
    • law
    • Media tips
    • News
    • News2
    • OPINION
    • POLITICS
    • Reaction
    • SOCIETY
    • SPORT
    • TIPS 1
    • TOP NEWS
    • VIDEO
    • WORLD
    • ማህደር
    • ያበደው

    መላው አማራ ከነገ ጀምሮ ለህልውና ዘመቻ እንዲነሳ ክተት ተጠራ

    July 25, 20210

    የጆ.ባይደን አስተዳደር የሰላም አማራጭ ንግግሩን ቀድሞ የትህነግን ፍላጎት አቋም አድርጎ አቀረበ

    November 1, 20220

    በሽረ አዲስ ተስፋ፤ ሕዝብ በነጻነት ስለቀጣዩ ዕጣው አየመከረ ነው

    December 26, 20220

    እውነትን ለሥልጣን መናገር ፣ ሳማንታ ፖወር ለኢትዮጵያ ዘር ፖለቲከኞች መከላከል አቁሚ!

    March 1, 20210

    በአዲስ አበባ ከ27ሺህ በላይ ወጣቶች ተደራጅተው ከተማዋን እየጠበቁ ነው

    November 11, 20210
    Prev Next Showing 1 Of 1493
  • Video
    video

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ለፓርላማ የሰጡት ማብራሪያ

    July 4, 2024
    video

    የህብታቸውን ምንጭ የሚያውቁ አይሰጉም! ማብራሪያ

    June 22, 2024
    video

    የሀገር አቀፍ የምክክር ሂደት ይፋዊ የማስጀመሪያ ሥነ ስርዓት

    June 4, 2024
    video

    የምክክር ሂደት ይፋዊ ማስጀመሪያ ላይ ያደረጉት ሙሉ ንግግር

    June 4, 2024
    Prev Next Showing 1 Of 5
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  • News
  • Design
  • Video
  • Categories
    • News
      • Europe
      • Politics
        • Reaction
          • Feedbacks
          • Opinions
            • Poeple
            • Reports
      • US
      • World
    • Design
      • Architecture
      • Devices
      • Inspiration
      • Trends
    • Events
      • Movies
      • Music
      • Social media
      • Stars
    • Featured
      • Lifestyle
      • Technology
      • Tourism
      • Travel
  • Home demo times
  • VOE VIDEO
  • ENGLISH PAGE
  • Home Demo default 2
  • News
  • Home Demo news
VOE - VOICES OF ETHIOPIA
  News  “አፈቀላጤው” ርዕሰ መስተዳድር በትግራይ የኩዴታ ስጋት ውስጥ
News

“አፈቀላጤው” ርዕሰ መስተዳድር በትግራይ የኩዴታ ስጋት ውስጥ

Ethioreview newsEthioreview news—September 6, 20230
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

የትግራይ ክልል አሁናዊ ቁመና አሳሳቢ ነው። ከጦርነቱ በሁዋላ የተከሰተው ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ስነልቦናዊ ቀውስ ሳያገግም ፖለቲካዊ ዳግም እየጦዘ ነው። ከፊታቸው “ንጻነት” የሚል ወይም “ወያኔ” የሚል መለያ የማያጡት የትግራይ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች “አዲስ” የሚባለው የክልሉ አስተዳደርም መከራውን እያበዙበት ነው። የዚሁ መገለጫ የሆነው ደግሞ ” አዲሱ አስተዳደር በቃው” የሚል አጀንዳ የተካተተበት ሰላማዊ ሰልፍ መጠራቱ ነው።

በስዊዲን የሚኖሩ የትግራይ ተወላጅ እናት ” ከጦርነቱ ወቅት ባልተናነሰ ጭንቀት ነው። ከዘመዶቼና ቤሰቦቼ የምሰማው ዕረፍት የሚነሳ ነው። ግድያ፣ ዝርፊያ፣ የተፈናቃዮች ችግር … ” እኙህ እናት የሚገርማቸውን ሲያክሉ ” ዛሬ ትግራይን መልሶ ማቋቋ የተቸገሩትን መርዳት በቀደመ ነበር። እጅ ለእጅ መያያዝ ልክ በጦርነቱ ወቅት የነበረው ዓይነት ቅስቀሳ ማድረግ መረባረብ ነበረብን። ጦርነቱን ሲቀሰቅሱ የነበሩ ሁሉ ተጸጽተው ማስተባበር ሲገባቸው ዛሬም የተማሩ አይመስሉም” ብለዋል።

በጦርነቱ ልጆቻቸውን ያጡና አካለ ጎደሎ የሆኑባቸውን የዘመዶቻቸውን ስም እየጠሩ በለቅሶ ” ሁሉም ረጋ ብለው ቢስማሙ ይበጃል” ሲሉ መክረዋል። የትግራይ ነፃነት ፓርቲ፣ ሳልሳይ ወያኔ (ሶስተኛ ወያኔ) ትግራይና የታላቋ ትግራይ ብሄራዊ ሸንጎ የተባሉ ሦስት ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ምላሽ ያላገኙ የትግራይ ህዝብ ወቅታዊ ችግሮች ለማሰማት በሚል የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚያደርጉ ማስታውቃቸውን ተከትሎ በትግራይ የፖለቲካውን መካረር የሚያመላክቱ መረጃዎች እየወጡ ነው።

“በትግራይ ኩዴታ ታስቧል” ሲሉ መላምታቸውን የሚያስቀምጡ ቢኖሩም ሰልፍ የጠሩት ወገኖች በፖለቲካ ቋንቋ ” ይህ መንግስት የሽግግር ጊዜውን ጨርሷል” ሲሉ የስልጣን ጥያቄያቸውን በገሃድ አንስተዋል።

More stories

ለመንግስት ሁሉ አቀፍ የሰላም አሳብ ቀረበለት፤ የእርቅ ኮሚሽን በመጪው ዓመት ህገ መንግስት እስከመቀየር የሚያደርሰውን ስራ ይጀምራል

September 6, 2023

አንድ መቶ አስራ አንድ አገሪቱን በብሄርና በሃይማኖት የሚንጡ ህገወጥ ድረ ገጾች ተለዩ፤ አስሩ ተያዙ

June 1, 2022

ኢትዮጵያ ፌስቡክንና ትዊተርን ሊተካ የሚችል የማህበራዊ ትስስር ገጽ ስራ ላይ ልታውል ነው

August 21, 2021

ኢትዮጵያ አንደ አገር ገናና በነበረችበት ዘመን አሜሪካ አትታወቅም ነበር

October 17, 2022

በትግራይ ብቻ ሳይሆን በመላው አገሪቱ በሚባል ደረጃ የሽግግር መንግስትና የክልልነት ጥያቄ አቋራጭ የስልጣን መያዣ ሆኗል። በተለይም የክልልነት ጥያቄ በምስኪኖች ደም የሚነገድበት የፖለቲካ ቁማር ነው። በትግራይ ያለው ከዚህ ቢለይም የሰላማዊ ሰልፉ ዓላማ ሲጠቃለል “አዲስ” የሚባለው የክልሉ መንግስት የማስወገድና “ምዕራብ ትግራይ” የሚባለውንና ቀደም ሲል በፖለቲካ ውሳኔ ወደ ትግራይ ክልል የገቡ የአማራ ክልል ይዞታዎች እንዲመለሱ መግፋት ነው።

ራሱን “የትግራይ የመጀመሪያ ተቀናቃኝ ፓርቲ” ሲል የሰየመው ” አረና ትግራይ” ጉባኤውን ካጠናቀቀ በሁዋላ የትግራይ ክልል በኢትዮጵያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት ባለቤት ለማድረግ ለመስራት ዕቅድ መያዙን ባስታወቀበት መግለጫው ሰልፉን ደግፏል። ለሰልፉ ድጋፍ ሲሰጥ ተሰልፎ አቋምን መግለጽ መብት እንደሆነ አመልክቶ ሁሉም ወገኖች ግን የሰው ህይወት እንዳይጠፋ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ሁሉንም ወገኖች አሳስቧል።

ዓረና ትግራይ ለሉአላዊነትና ዴሞክራሲ የኢትዮጵያ ሕገመንግሥትን በማሻሻል አዲስ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ውል ለመመስረት ከሌሎች በኢትዮጵያ ካሉ የፖለቲካ ፖርቲዎች ጋር በጋራ እንደሚሠራ አመልክቶ በፌዴሬሽን ምክር ቤት ድምጽን በድምጽ የመሻር መብት ባለቤት ለመሆን ይቻል ዘንድ ሌሎች ያላቸውን ፓርቲዎች እንደሚያስተባብር አመልክቷል። ድርጅቱን ጠቅሶ ዜናውን ያሰራጨው የጀርመን ድምጽ ዓረና ድምጽን በድምጽ የመሻር መብት ጥያቄን ቀዳሚ ለማድረግ ያሰበበትን ምክንያት አላብራራም። ምን አልባት ውዝግብ ባለባቸው አካባቢዎች ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የመጨረሻ ውሳኔ ሰጪ አካል ከመሆኑ ጋር ሊያያዝ እንደሚችል የገመቱ አሉ።

ዓረናም ሆነ ሌሎች የትግራይ ተቀናቃኝ ድርጅቶች በትግራይ ክልል ስልጣን የያዙ ግለሰቦች በተለይም ሴቶችን መግደል፣ ሀብት መውረስን ጨምሮ በተለያዩ ሕገወጥ ተግባራት ተሰማርተዋል ብለዋል ። ፓርቲዎቹ  “የማዕድናትና የሰዎች ሕገወጥ ዝውውር ላይ ከፍተኛ የፖለቲካና ወታደራዊ መሪዎች እጃቸው አለበት” ሲሉ ትህነግን ይከሱታል።

ሲጀመሩ ሶስት ቢሆኑም አምስት ሆነው ማለትም ሳልሳይ ወያነ ትግራይ ፣ ውድብ ናፅነት ትግራይ ፣ ባይቶና ዓባይ ትግራይ ፣ ዓረና ንሉኣላውነትን ንዴሞክራስን፣ ውድብ ዓሲምባ ከጳጉሜን 2 እስከ 4 /2015 ዓ.ም በጥምር ለሚያካሂዱት ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ በመቐለ ከተማ በመኪና በመዞር በድምፅ ማጉልያ በመታገዘ እየቀሰቀሱ መሆናቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብን ጠቅሶ አስታውቆ ነበር።

የመቐለ ከተማ አስተዳደር ከዚህ ቀደም የተቃውሞ ሰልፉን በተመለከተ ከፓርቲዎቹ በተላከለት ” የእወቁልኝ ” ደብደቤ በሰጠው ምላሽ ሰልፍ ማድረግ በኢፌዴሪ አዋጅ ቁጥር  3/1991 የተቀመጠ መብት ቢሆንም የተመረጠው ጊዜ አዲስ ዓመትና ሃይማኖታዊ በዓላት የሚበዙበት በመሆኑ ለማስተናገድ እንደሚቸገር ማሳወቁ ይታወሳል።

ለአሸንዳ በዓል መቀለ ደርሳ ወደ አውሮፓ የተመለሰች አንድ የትግራይ ተወላጅ እንዳለችው በበላዓሉ ዕለት ብቻ በሺህ የሚቆጠር ሞባይል በሌቦች ተዘርፏል። ነጠቃ ነው የሚመስለው። ህግና ስርዓት ያለ አይመስልም። የሚታየው ሁሉ ያሳዝናል” ስትል ትዝብቷን አጫውታናለች።

አቶ ጌታቸው የሚመሩት ጊዜያው አስተዳደር ለተጠራው የተቋውሞ ሰልፍ ፀጥታ የማስከበር ግዴታና ሃላፊነት እንዳለበትም አስታውሶ፣ በመጪው አዲስ ዓመት በዓል በሚኖረው ሰፊ እንቅስቃሴ ሳቢያ የስራ መደራረብና የጸጥታ ስራው አስቸጋሪ በመሆኑ ሰልፉን መፍቀድ ከደህንነት አንጻር አዳጋች እንደሚሆን አስታውቋል። ስለሆነም የቀረበውን የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ማስፈፀም እንደማይችል ይፋ አድርጓል።

የመቀለ ከተማ አስተዳደር የሰጠው ምላሽ አሳማኝና አጥጋቢ አይደለም በሚል ሰልፉን በተያዘው ጊዜ እንደሚያካሂዱ ዳግም ማረጋገጫ ሰጥተዋል። ይህንኑ ውሳኔያቸውን ተከትሎ ሰልፉን በተሽከርካሪ ማስተባበር ቀጥለው ነበር። ሰልፉ ሰላማዊ በመሆኑ ምንም ስጋት እንደሌለ በመጥቀስ ክልከላውን ወደ ጎን በማለት ቅስቀሳ ላይ የነበሩት መያዛቸውም ተሰምቷል።

” ኪዳን ሱር በቆስ ለውጢ ” በሚል ለተሰየመው ሰላማዊ የተቋውሞ ሰልፍ ሲያነሳሱ የነበሩት ሳልሳይ ወያነ ትግራይ ፣ ውድብ ናፅነት ትግራይ ፣ ባይቶና ዓባይ ትግራይ ፣ ዓረና ለሉኣላውነትና ለዴሞክራስና ፣  ዓሲምባ የተባሉ 5 ቱ የትግራይ ተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች ከጳጉሜን 2 እስከ 4 /2015 ዓ.ም በጥምር ለሚያካሂዱት ሰላማዊ የተቓውሞ ሰልፍ በመቐለ ከተማ በመኪና በመዞር በድምፅ ማጉልያ በመታገዘ እየቀሰቀሱ ሳሉ ነው አባላቱ መታሰራቸውን የተለያዩ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

ነገብረኣብ ወልዱና ብርሃነ ኣርኣያ ከሳልሳይ ወያነ  ፣ ብርሃነ ዘመን ዮሃንስና ገብሩ ከባይቶና ፣ ጠዓመ ሓጎስና ኣፅብሃ ተኽለ ከውድብ ናፅነት ትግራይና እንዲሁም የድምፅ ማጉልያና መኪና ያካራዩና ባለሙያዎች መሆናቸ የአይን አማኞች እንዳረጋገጡለት ቲክቨሃ አመልክቷል። ታሳሪዎቹ በቀዳማይ ወያነ ክፍለ ከተማ ፓሊስ ጣብያ እንደሚገኙም ታውቋል። 

የባይቶና ከፍተኛ አመራር አቶ ኪዳነ አመነ በማህበራዊ የትስስር ገፃቸው  “… ‘ኪዳን ንሱር ቦቆስ ለውጢ ‘ በሚል በወርሃ ጳጉሜን እንዲካሄድ ለጠራነው ሰላማዊ የተቋውሞ ሰልፍ ሲያነሳሱ የነበሩ አባሎቻችን መታሰራቸው ለክልሉ ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዚደንት ጌታቸው ረዳና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት አባሎቻችን ያለ ቅድመ ሁኔት በአንድ ሰዓት ውስጥ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ደብዳቤ ፅፈናል ። ” የሚል አሳብ አስፈረዋል። ምላሹ ግን አልታወቀም።

የከተማው አስተዳደር ለተጠራው የተቋውሞ ሰልፍ ፀጥታ የማስከበር  ግዴታና ሃላፊነት እንዳለበት በመጥቀስ ፤ ይሁን እንጂ በበዓሉ በሚኖረው የህዝብና የመኪና ሰፊ እንቅስቃሴ ምክንያት በሚፈጠር የስራ መደራረብ የተነሳ የቀረበውን ጥያቄ ማስፈፀም እነደማይችል በያዘው አቋም አሁን ድረስ እንደጸና ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ዓሲምባ ” ኪዳን ንሱር በቆስ ለውጢ ” በሚል መፈክር ጳጉሜን 2 /2015 ዓ.ም በ5 የፓለቲካ ፓርቲዎች በመቐለ እንዲካሄድ ከተጠራው ሰላማዊ የተቋውሞ ሰልፍ ራሱን እንዳገለለ ይፋ ሆኗል። ፓርቲው በሊቀመንበሩ አቶ ዶሪ አስገዶምና በኩል በፓርቲው በማህበራዊ የትስስር ገፅ ” የተጠራው ሰልፍ ህጋዊ አካሄድ ያልተከተለ እንደሆነ የሚመለከታቸው አካላት በማስረጃ አስደግፈው አስረድተውናል። ህግ ይከበር እያልን ህግ መጣስ ህዝባችንን ስለማይመጥን ከተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ራሳችን ለማግለል ወስነናል። ሁሉም ከህግ በታች ነው ” የሚል አቁማቸውን ከምክንያት ጋር አቅርበዋል።

ቲክቫህ ከትግራይ ቤተሰቦች እንዳገኘው ጠቅሶ እንዳለው

  • የሳልሳይ ወያነ ሊቀመንበር ሃያሉ ጎዲፋይ ፣
  • የውድብ ናፅነት ትግራይ ሊቀመንበር ዶ.ር ደጀን በርሀ ፣
  • የባይቶና ዓባይ ትግራይ ከፍተኛ አመራር አቶ ክብሮም በርሀ ጳጉሜን 1/2015 ዓ.ም ረፋድ 4:00 ሰዓት በቁጥጥር ስር መዋላቸው ታውቀዋል።

ሰላማዊ ሰልፉ ሌላ እንደምታ እንዳለው የሚገልጹ እንደሚሉት ጉዳዩ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን መብላት ነው። ይህ በተቃውሞ ሰልፍ ስም አስተዳደሩን ለመብላት የተደረጃው ስብስብ ከጀርባ የሚመራው ባኮረፉ የትህነግ ሰዎች እንደሆነም ተመልክቷል። ይህን መረጃ ያደረሱን እንደሚሉት የተቀናቃኝ ድርጅቶቹ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ትህነግ ስር ሆነው የተደራጁ በመሆናቸው ካኮረፉት ፈጣሪዎቻቸው ጋር አብሮ ለመስራት ችግር አይኖርባቸውም።

የፌደራሉ መንግስት በዶክተር ደብረጽዮን የሚመራውን የመጀመሪያውን የጊዜያዊ አስተዳደር ዝርዝር ከሰረዘ በሁዋላ ነው ኩርፊያው እያደገ የመጣው። የትግራይ መከላከያ ሃይል የተባለውን ታጣቂ ሃይል የሚመሩት ወገኖች ጦርነቱን ተከትሎ የበላይነት መያዛቸው የእነ ዶክተር ደብረጽዮንን ቡድን አቅም በልቶታል።

“አሁን እንደሚሰማው ከሆነ ይህ ሃይል በጦርነቱ የተጎዱትን ሳይቀር ለአመጽና ለተቃውሞ ያደራጃል። ራሱ ቆስቁሶና ሰብኮ ወደ ጦርነት የማገዳቸውን ወጣቶች ማልሶ ለኩርፊያው መጠቀሚያ እያደረገ ነው” የሚሉ ክፍሎች ” እውነቱ አንድ ነው። እሱም ኩዴታ ለማካሄድ ዝግጅት ነው” ሲሉ የባሰ ችግርና ነብስ መጠፋፋት እንዳይከሰት የመክራሉ።

“በሌላ በኩል ግን ትህነግና ከትግነግ ጋር ንክኪ ያያላቸው በሙሉ ለፍርድ እንዲቀርቡ መደረግ ነበረበት” የሚሉ ወገኖች ” ነገር የተበላሸው አሜሪካ አቶ ጌታቸውን ረዳን አበባ እየረጩ፣ ከበሮ እየደበደቡ በዕልልታ የተቀበሉት ቀን ነው” ሲሉ የትግራይ ተወላጆችን ይወቅሳሉ። እነዚህ ወገኖች እንደሚሉት ለትህነግ ሰዎችና አመራሮች በዚህ ደረጃ ሽብሸባና ዕልልታ ምክንያቱ አይገባቸውም። ” የትግራይን ወጣቶች ስላስጨፈጨፉ? አካለ ጎዶሎ ስላስደረጉ? የትግራይ ህዝብ ከጎረቤቶቹ ጋር ጠላት ሆኖ ተፈናቅሎ እንዲኖር ስለፈረዱ? በማይሆን ጦርነት ትግራይ እንዲወድም ምክንያት ስለሆኑ? ህዝቡን ለማኝ ስላደረጉ፣ የትግራይን ህዝብ ወደ ጨለማ ስለመለሱ?…” ሲሉ ይጠይቃሉ።

በማንኛውም መስፈረት ትህነግ የትግራይ ቀጣይ አስተዳድረ ሊሆን ይገባው እንዳልነበር የሚጠቅሱት ወገኖች አሁን የሚቀርበው የሰላማዊ ሰልፍ የተቃውሞ ጥያቄ ውስጥ ውስጡ ካኮረፉ የትህነግ ነባር ቅሪቶች ተላቆ በገሃድ በትግራይ ምርጫ እንዲካሄድ መጠየቅ መሆን እንደሚገባው ያምናሉ። በትግራይ ምርጫ እንዲካሄድና ትህነግ እስከወዲያኛው እንዲወገድ ራሳቸውን ችለው መስራት እየቻሉ ዛሬም የትህነግ አኩራፊዎች መገለገያ መሆናቸው ሌላ ዙር ሃፍረት እንደሚሆን ይጠቅሳሉ።


  • አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ
    በዙፋን ኡርጋ ደራሲነት የተጻፈውን ሌንጮ ለታ ትግል ሕይወቱ መጽሐፍን አነበብኩት። መጽሐፉ በ471 ገጾች እና በሦስት ክፍሎች ተቀንብቧል። የመጀመሪያው ክፍል ከልጅነት… Read more: አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
    ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
    አዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
    ለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
    ቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው
NEWS
FacebookX TwitterPinterestLinkedInTumblrRedditVKWhatsAppEmail

Ethioreview news

A journalist

ቻይናዊው የፀሃይ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ከ9 ግብረ አበሮቻቸው ጋር የውጭ አገር ብሮች በማተምና በጥቁር ገበያ ወንጀል ታስረው ፍ/ቤት ቀረቡ
ለመንግስት ሁሉ አቀፍ የሰላም አሳብ ቀረበለት፤ የእርቅ ኮሚሽን በመጪው ዓመት ህገ መንግስት እስከመቀየር የሚያደርሰውን ስራ ይጀምራል
Related posts
  • Related posts
  • More from author
ART and CULTURE

አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ

May 17, 20260
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
Load more
Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Read also
ART and CULTURE

አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ

May 17, 20260
News

ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?

April 26, 20260
WORLD

ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት

April 26, 20260
News

“ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ

April 26, 20260
WORLD

አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው

April 26, 20260
WORLD

የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች

April 26, 20260
Load more
Recent Posts
  • አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ May 17, 2026
  • ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር? April 26, 2026
  • ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት April 26, 2026
  • “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ April 26, 2026
  • አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው April 26, 2026
  • የኢልሀን ኦማር የ30 ሚሊዮን ዶላር የሀብት መዝገብ እየተመረመረ ነው “የሂሳብ ስህተት ነው” ብላለች April 26, 2026
  • የፔትሮ-ዶላር ግርዶሽ! ወደ ዘመን ዩዋና? April 26, 2026
  • ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን የፕሬዚዳንት ኢሳያስ የግል አምባሳደር April 13, 2026
  • Iran reneges on key point of ceasefire amid allegations of broken promises   April 8, 2026
  • Erdogan warns of ‘sabotage’ in Iran ceasefire during Trump call April 8, 2026
  • እዚህ ሀገር ያሉ የኤርዶኻን ወኪሎች እንዲያውም ቁርጣቸውን ቢያውቁ… April 8, 2026
  • የአውሮፓ ህብረት ሻዕቢያ ጣልቃ ገብነት እንዲያቆም አሳሰበ – ኤርትራዊያን ተቃውሞ አሰሙ April 8, 2026
  • ትዕይንተ ሕዝብ ወይስ ትዕይነተ ውድቀት? – መልማዮቹና ለኪዎቻቸው ዒላማ ያደረጉት ምን እንደሆነ አየንበት! April 8, 2026
  • ኢትዮጵያና የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም በሰላማዊ ኒውክሊየር ኃይል መርሃ ግብር በጋራ ለመስራት ተስማሙ March 29, 2026
  • ምርጫ ለማጨናገፍ ሻዕቢያ ያዘጋጀው የፕሮፓጋንዳ ማንዋል “ምርጫ ማክሸፍ የህልውና ጉዳይ ነው” ይላል March 29, 2026
Social networks
FacebookLikes
X TwitterFollowers
PinterestFollowers
InstagramFollowers
YoutubeSubscribers
VimeoSubscribers
    VOE - VOICES OF ETHIOPIA
    The VOICES OF ETHIOPIA/ VOE is free website provied news, information, opinions and analysis, from and to the public "በሰው ልጆች ዕልቂትና በብሄራዊ ጥቅም መነገድ ይቁም!"

    MENU

    NEWShomeMEDIAOPINIONtopnewswPOLITICSSOCIETYlawworldentertainmentECONOMYINTERVIEWeventsportOromiffafeaturedbusinesshotarchivetips
    © Copyright 2026, All Rights Reserved
    • CONTACT
    • INTERVIEW
    • law
    • ECONOMY
    • Home demo times
    • ያበደው
    • VOE VIDEO
    • ENGLISH PAGE
    • Home Demo default 2
    • Home Demo news