በ2012 ከነበሩት 46 ሺህ በላይ መምህራን አሁን ላይ ከ14ሺህ በላይ የሚሆኑት ከስራ ገበታቸው ውጪ መሆናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። የትምህርት ቢሮው ሀላፊ ዶ/ር ኪሮስ ግዑሽ በጦርነት ሳቢያ መምህራን ሞተዋል። ራሳቸውን ለማኖር ተሰደዋል። የኑሮ መመሳቀል ደርሶባቸዋል ብለዋል።
በጦርነቱ ምክንያት የተሰደዱ ፣ የተፈናቀሉ ፣ አካላቸው የጎደለ እንዲሁም የሞቱ መምህራን መኖራቸውን አንስተው፤ ከ 2 ዓመት በላይ ደሞዝ ስላልተከፈላቸው ህይወታቸውን ለማትረፍ የተለያዩ ስራዎች ውስጥ የተሰማሩ መኖራቸውንም ሃላፊውን ጠቅሶ የዘገበው ኢትዮኤፍ ኤም ነው።ሃላፊው የተቀሩት መምህራንም ቢሆኑ በጦርነቱ ምክንያት ብዙ የስነልቦና ጉዳትን ጨምሮ ኢኮኖሚያዊ ችግር እንደደረሰባቸው አመልክተዋል።
በክልሉ የነበረው ጦርነት በትምህርት ዙሪያ ሶስት መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷልም ነው ያሉት ሃላፊው። የት/ቤቶች መቃጠል ፣መፍረስ፣ መውደም አንደኛው ሲሆን ፤ በሰው ሃይሉ ላይ ያደረሰው ጉዳት ቀጥሎ የሚነሳ ጉዳይ ነው።
በሶስተኛነት የተነሳው ጉዳይ ደግሞ ስርዓተ ትምህርቱ ሲሆን ብዙ ተማሪዎች በእድሜያቸው ልክ ማግኘት ያለባቸውን ትምህርት ባለማግኘታቸው አሁን ላይ 5ኛ ክፍል እና ከዛ በላይ መሆን የነበረባቸው ልጆች ገና የ1ኛ ክፍል ተማሪዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። በ2012 የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ቢወስዱ ምናልባት አሁን ላይ የ4ኛ አመት የዩኒቨርስቲ ተማሪ የሚሆኑ ከ9ሺህ በላይ ተማሪዎች ከ4 አመታት በኋላ ባለፈው ሳምንት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መውሰዳቸው የሚታወስ ነው።
በሌላ ዜና በትግራይ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በክልሉ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ቁመና እንደሌለ ተገልጿል። ክልሉ በከፍተኛ ሁኔታ በተጎዳበትና ዜጎች ከቤት ንብረታቸዉ ተፈናቅለዉ በርካታ ቦታዎች በወራሪ ሀይሎች በተያዙበት ሁኔታ፣ ምርጫ ማካሄድ የማይታሰብ ነው ሲሉ መናገራቸውን ኢትዮ ኤፍ ኤም ዘግቧል። ዜናው “ወራሪ” ያላቸውን አላብራራም።
ክልሉን እየመራ የሚገኘዉ ግዚያዊ አስተዳደር ምርጫ ለማካሄድ ዝግጁነት የለዉም የሚሉት የዉድብ ናፅነት ትግራይ ዉናት ሊቀመንበር ዶክተር ደጀን መዝገቦ፣ አስተዳደሩ ወደ ምርጫ ገብቶ ለዉጥ እንዲመጣ ፍላጎትም ዝግጁነትም የለዉም ብለዋል።
በትግራይ ክልል በሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ጥሩ ቅርርብ መኖሩን የሚናገሩት የዓረና ሉአላዊነትና ዲሞክራሲ ሊቀመንበር አቶ አንዶም ገ/ስላሴ ፣ በሳልሳይ ወያኔ ትግራይ፣ውድብ ናፅነት ትግራይ እና ባይቶና አባይ ትግራይ ጥምረት ፈጥረዉ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፣ አረናም ጥሩ መቀራረብ ስላለዉ ምን አልባት መልካም ሁኔታ ተፈጥሮ ምርጫ ከተካሄደ በጋራ ለመወዳደር ዉይይት ላይ መሆናቸዉን ተናግረዋል።
ምርጫ ቦርድ ባለፈዉ ዓመት በ2016 ምርጫ ከሚካሄድባቸዉ አካባቢዎች አንደኛዉ የትግራይ ክልል መሆኑን ማስታወቁ አይዘነጋም። የትግራይ ክልልን ጨምሮ የስድስተኛው ዙር ቀሪ ምርጫዎችን በተለያዩ ጊዜያት ለማከናወን ዝርዝር ዕቅድና በጀት አዘጋጅቶ፣ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዳቀረበም አስታውቋል፡፡
- አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱበዙፋን ኡርጋ ደራሲነት የተጻፈውን ሌንጮ ለታ ትግል ሕይወቱ መጽሐፍን አነበብኩት። መጽሐፉ በ471 ገጾች እና በሦስት ክፍሎች ተቀንብቧል። የመጀመሪያው ክፍል ከልጅነት እስከ ትግል… Read more: አጭር ዳሰሳ ሌንጮ ለታ፤ ትግል ሕይወቱ
- ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?ዘፈኑ ገና ከመለቀቁ በፊት ጀምሮ በተከታታይ አየሩን የያዙት መረጃዎች ሁሉ በኦፊሳል ከቴድሮስ ካሳሁን፣ ከባለቤቱ ወይም በህግ የሚታወቁ ወኪሎቹና ተቋማትን ምንጭ ያደረጉ አልነበሩም።… Read more: ፖሊስ “ቴዎድሮስ በሚስቱ ሚዲያ ለምን ቤቱ ቅጭ ብሎ መግለጫ አይሰጥም ነበር?
- ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርትአዲስ ሪፖርተር ዜና – “ቅዳሜ ምሽት፤ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው ታዋቂው ሂልተን ሆቴል በደመቀ ድባብ ውስጥ ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጠኞች፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት… Read more: ቅዳሜ ምሽት በዋሽንግተን ዲሲ ሂልቶን፤ ሶስት ቀን የተደበቀው “ትኩላ” ዝርዝር ሪፖርት
- “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊለሶስት አስርት ዓመታት በማዕቀብ ተቆልፎባት የኖረችው ኤርትራ በኢትዮጵያ ለውጥ መምጣቱን ተከትሎ ሰንሰለቱ ተበጥሶላት ነበር። ጦርነትም፣ ሰላምም ባልነበረበት ሁኔታ ተዘግቶባት የነበረችው ኤርትራ ከኢትዮጵያ… Read more: “ኢሳያስ ከአሜሪካ ወዳጅነትን ይፈራሉ፤ ግንቡ ይፈርስባቸዋል” ቲቦር ናጊ
- አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነውቪኦኢ ዜና -በአውሮፓ ህብረት እና በሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) መካከል ያለው ግንኙነት ጥርጣሬ ውስጥ በወደቀበት በዚህ ወቅት፣ የአውሮፓ ህብረት አባል… Read more: አውሮፓ ህብረት የጋራ መከላከያ ለማቋቋም የስምምነት ረቂቅ ሊያዘጋጅ ነው







